TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ደቡብ ክልል‼️

በደቡብ ክልል ኢትዮጵያን ከኬንያ ጋር የሚያዋስነውን ድንበር በህገ ወጥ መንገድ ሊሻገሩ ነበር የተባሉ 25 ኤርትራውያንን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ። ወጣቶቹ በኬንያ አቋርጠው #ኡጋንዳ የመግባት እቅድ እንደነበራቸው ፖሊስ ገልጿል።

ኤርትራውያኑ ሐሙስ ዕለት የተያዙት በክልሉ በደቡብ ኦሞ ዞን፤ ሐመር ወረዳ ውስጥ ቱርሚ በተባለች አነስተኛ የጠረፍ ከተማ ላይ መሆኑን የዞኑ ፖሊስ ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር #ካሳ_ካውዛ ለDW ተናግረዋል፡፡ ኤርትራውያኑ በወጣትነት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ
መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።

“የተያዙበት ምክንያት ባልተለመደ ሁኔታ ወደዚያ በህዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ከደረሱ በኋላ ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ወደ ጭነት መኪና ተዛውረው ሊጓዙ ሲሉ በፖሊስ ጥርጣሬ ተይዘዋል። ሲታዩ ያው በኬንያ በኩል ወደ ኡጋንዳ ካምፓላ መድረስ እንፈልጋለን የሚሉ ወጣቶች
ነበሩ። ወጣቶቹ እነርሱ እንደሚሉት የኤርትራ ዜጎች ነን ነው። በእጃቸው ላይ የያዙት አንዳንድ መታወቂያዎችም ከኤርትራ ትምህርት ቤት የተነሱ መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው። አሁን ወደ ዞናችን ፖሊስ መምሪያ አስመጥተን ወጣቶቹን በዚያው በዞናችን ፖሊስ መምሪያ ግቢ ውስጥ ይገኛሉ” ሲሉ የዞኑ የፖሊስ ኃላፊ ወጣቶቹ እንዴት ሊያዙ እንደቻሉ አስረድተዋል።

ዋና ኢንስፔክተር ካሳ ወጣቶቹን በተመለከተ በቀጣይነት ምን ማድረግ እንዳለባቸው ከክልሉ መንግስት ጋር እየተነጋገሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የኤርትራ ኤምባሲ እስከአሁን በፖሊስ እጅ በሚገኙት ኤርትራዊያን ጉዳይ ላይ ያለው ነገር አለመኖሩን ተዘግቧል።

ምንጭ፦ DW አማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸አቶ ገዱ፣ አቶ ለማና ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ #ኡጋንዳ

በውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የሚመራውና የመከላከያ ሚኒስትር ክቡር አቶ ለማ መገርሳና እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ የሚገኙበት የልዑካን ቡድን በዛሬው ዕለት ከክቡር የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት የዎሪ ካጉታ ሙሲቪኒ ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡

በውይይቱ ፕሬዝዳንት ሙሴቪኒ ኢትዮጵያና ኡጋንዳ ያላቸውን ታሪካዊ ግንኙነት በማስታወስ ይህ ግንኙነት ይበልጥ ሊጠናከር በሚችልበት ሁኔታ ላይ ጠንክሮ መስራት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡ በነገው ዕለት የሚከፈተው ሶስተኛው የኢትዮ-ዩጋንዳ የሚኒስትሮች የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ ሁለቱ አገሮች ግንኙነታቸው የበለጠ እንዲጠናከር ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል፡፡

Via የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኡጋንዳ

የውጭ ጉዳይ እና የመከላከያ ሚንስትሮች #በኡጋንዳ ከሚኖሩ #ኢትዮጵያውያን ጋር ተወያዩ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ በኡጋንዳ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሚንስትሮቹ ከኢትዮጵያዊያኑ ጋር የተወያዩት በሀገሪቱ እየተካሄደ ባለው ለውጥ ዙሪያ ነው ተብሏል፡፡ ውይይቱ ከ3ኛው የኢትዮ ኡጋንዳ የሚኒስትሮች ስብሰባ ጎን ለጎን የተካሄደ ነው።

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
" ሁለቱም ወገኖች ሰላም፣ ጸጥታና የኢትዮጵያ መረጋጋት ምኞታቸው መሆኑን ገልፀውልኛል " - ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ

በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ የመንግስትን እና የህወሃትን አመራሮችን ማነጋገራቸውን ካስታወቁ በኋላ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

ኦባሳንጆ ሁሉም ወገኖች ወታደራዊ ፍልሚያውን እንዲያቆሙ ጠይቀዋል፡፡

ከመንግስትም ሆነ ሽብርተኛ ተብሎ ከተፈረጀው ህወሃት በኩል የሰላም ፍላጎቶች መኖራቸውን የገለጹት ከፍተኛ ተወካዩ ‘የሰላም መንገዱ ምን ይሁን’ የሚለው ግን ልዩነታቸው እንደሆነ ጠቅሰዋል።

የአፍሪካ መሪዎችና ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ሕብረቱ የጀመረውን የማሸማገል ጥረት እንዲደፉ እና ግጭቱን ሊያባብሱ ከሚችሉ ነገሮች እንዲቆጠብም ኦባሳንጆ ጥሪ አቅርበዋል።

ኦባሳንጆ፥ "ሆን ተብሎም ይሁን ባለማወቅ ግጭቱን የሚባብሱና ወደከፋ ደረጃ ከሚያደርሱ ንግግሮች መቆጠብ ያስፈልጋል" ብለዋል ።

ኦባሳንጆ፤ ውጊያው ከቆመ የንግግር ዕድል እንደሚኖር የገለጹ ሲሆን አሁን ባለው ሁኔታ ውጊያ እየተደረገ ግን ለመነጋጋር የሚመች እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡

ኦባሳንጆ ፥ የኦሮሚያ እና አማራ ክልል አመራሮችን ማግኘታቸውን በመግለጫቸው ላይ የገለፁ ሲሆን በቀጣይ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የአፋር ክልል አመራሮችን እንደሚያገኙ አሳውቀዋል።

ኦባሳንጂ ይህ የማሸማገል ስራ እንዲሳካ ቁርጠኛ እንደሆኑ የገለጹ ሲሆን ፦
- #የኬንያ
- #ኡጋንዳ
- #ጅቡቲ
- #ደቡብ_ሱዳን
- #ሶማሊያ እና ሱዳን መሪዎችን ማግኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡

ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አስማሚ ሁኔታ ይፈጠራል ብዬ አስባለሁ ያሉት ኦባሳንጆ ሁለቱም ወገኖች ሰላም፣ ጸጥታና የኢትዮጵያ መረጋጋት ምኞታቸው መሆኑን እንደገለጹላቸው አሳውቀዋል።

Credit : #Al_AIN
Pic : AU

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኡጋንዳ ፓርላማ በአገሪቱ ውስጥ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ #ወንጀል እንዲሆን የሚያደርገውን ረቂቅ ሕግ አጸደቀ። ሕጉ ምን ይዟል ? - ማንኛውንም ራሱን በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አፍቃሪነት የመደበ፣ ወይም የጾታ ለውጥ ያስደረገ እንዲሁም በእንግሊዝኛ ምሕጻራቸው ኤል-ጂ-ቢ-ቲ-ኪው ዝርዝር ውስጥ የሚካተት የጾታ ዝንባሌ ያለው ዜጋን ሁሉ ወንጀለኛ ያደርጋል። - በጸደቀው…
#ኡጋንዳ

ምዕራባውያኑ በተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ጉዳይ የኡጋንዳ ፓርላማ ያሳለፈውን ውሳኔ #እየተቃወሙ ናቸው።

የኡጋንዳ ፓርላማ ትላንት ከተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ጋር በተገናኘ አዲስ ህግ አውጥቷል።

ይኸው ህግ በኡጋንዳ ምንድር ማንም ሰው የተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪ ነኝ በሚል ማንነቱን ቢገልፅ ህይወቱን ሙሉ / ለበርካታ አመታ እስር ቤት ውስጥ እንዲያሳልፍ የሚያደርግ ነው።

በአንዳንድ ሁኔታዎች ደግሞ #ሞትም ያስፈርዳል።

ይህ ህግ ትላንት ማክሰኞ በፓርላማ በከፍተኛ ድምፅ ነው የፀደቀው።

ይህንን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና ምዕራባውያኑ ውሳኔውን መቃወም ጀምረዋል።

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች የሆነው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ህጉን " #አፋኝ " ሲል ነው የተቃወመው። ተቋሙ ህጉን " አደንጋጭ ህግ " ሲልም ገልጾ " መድሎ እና ጥላቻን ያበረታታል ስለሆነም ሀገሪቱ እንደገና ህጉን ትፈትሽ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር #አንቶኒ_ብሊንከን እንዲሁም የዩናይትድ ኪንግደም የአፍሪካ ሚኒስትር #አንድሪው_ሚቼል አዲሱን ህግ ስለማውገዛቸው ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።

አዲሱ ህግ የኡጋንዳ ፕሬዜዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ በፈረሙ ቅፅበት ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።

ከቀናት በፊት ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ #ምዕራባውያን አገራት የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎችን መብቶች #በአፍሪካ አገራት ላይ በኃይል ለመጫን እየጣሩ ነው ሲሉ ተናግረው ነበር።

ፕሬዝዳንቱ በአገሪቱ ፓርላማ ቀርበው ንግግር ሲያደርጉ " እንግዳ የሆነ ባህል / ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት እንድንፈቅድ ምዕራባዊያኑ #ማዕቀብ በመጣል ጫና ያሳድራሉ " ብለዋል።

" ምዕራባውያን የራሳቸውን አሠራር በሌሎች ላይ ለመጫን የሚያባክኑትን ጊዜ ማቆም አለባቸው "  ሲሉም ፕሬዜዳንት ሙሴቬኒ አሳስበው ነበር።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኡጋንዳ

" ፕሬዜዳንት ሙሴቬኒ #አይፈርሙ " - ተመድ

" ህጉ ኤችአይቪ/ኤድስን በመዋጋት ረገድ የተገኘውን ውጤት ሊቀለበስ ይችላል " - አንቶኒ ብሊንከን (የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ከቀናት በፊት ከተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት / አፍቃሪዎች ጋር በተያያዘ የኡጋንዳ ፓርላማ ያሳለፈውን ውሳኔ ተቃወመ።

የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ የዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ በሕግ አውጭዎች ማክሰኞ የፀደቀውን ህግ እንዳይፈርሙ በይፋ ጥያቄ አቅርበዋል።

ኮሚሽነሩ ህጉን " ጨካኝ ህግ " ሲሉ ጠርተው በአጠቃላይ በህብረተሰቡ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያሳድር እና የሀገሪቱን ህገ መንግስት እንደሚጥስ ገልጸዋል።

እኚሁ የተመድ ባለስልጣን ፤ ፓርላማው ያሳለፈው ይኸው ህግ አድሎአዊ ነው ብለው " ምናልባትም በዓለም ላይ ካሉት እጅግ በጣም አስከፊው ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ፕሬዜዳት ሙሴቬኒ በህጉ ላይ እንዳይፈርሙም ጠይቀዋል።

የኡጋንዳ ፓርላማ ያሳለፈውን ውሳኔ የተለያዩ ምዕራባውያን ሀገራት እየተቃወሙ መሆናቸው ይታወቃል።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ውሳኔውን ተቃውመው ያሰራጩት መልዕክት በብዙሃን ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል።

ብሊንከን ህጉን " የኡጋንዳውያንን መሰረታዊ ሰብአዊ መብቶች የሚገታ እና ኤችአይቪ/ኤድስን በመዋጋት ረገድ የተገኘውን ውጤት ሊቀለበስ ይችላል። " ሲሉ ነው የገለፁት።

" የኡጋንዳ መንግስት የዚህን ህግ ተግባራዊነት እንደገና እንዲያጤነው #እናሳስባለን" ም ብለዋል።

የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሞሴቬኒ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ሀገሪቱ ለተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪዎች ምንም አይነት ቦታ እንደሌላት ገልፀዋል።

ከቀናት በፊትም በፓርላማ ባሰሙት ንግግር #ምዕራባውያን አገራት የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎችን መብቶች #በአፍሪካ አገራት ላይ በኃይል ለመጫን እየጣሩ ነው ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ  " እንግዳ የሆነ ባህል / ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት እንድንፈቅድ ምዕራባዊያኑ ማዕቀብ በመጣል ጫና ያሳድራሉ " ሲሉም ነው የገለፁት።

ፕሬዜዳንቱ ፓርላማው ባፀደቀው አዲሱ ህግ ላይ ፊርማቸውን ይኖራሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው ፤ ልክ ፊርማቸው እንዳረፈ በቅፅበት #ተግባራዊ ይሆናል።

በአዲሱ የኡጋንዳ ህግ ፦

- በኡጋንዳ ምድር ማንም ሰው የተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪ ነኝ በሚል ማንነቱን ቢገልፅ ህይወቱን ሙሉ / ለበርካታ አመታ እስር ቤት ውስጥ እንዲያሳልፍ ይሆናል።

- በአንዳንድ ሁኔታዎች #ሞት ያስፈርዳል።

- የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎችን በጉያው ያቀፈ ፣ በቤተሰብ ደረጃ #ያስጠለለ ፣ ወዳጃቸው የሆነ ወይም አብሯቸው ያለ ሰው “እከሌ እና እከሌ” ብሎ ለሕግ አካላት ማንነታቸውን የማጋለጥ ግዴታን ይጥላል።

- ልጆችን ለዚሁ ለተመሳሳይ ጸታ ያጨ ወይም ያስተላለፈ #የእድሜ_ይፍታህ ፍርድ ይፀናበታል።

- " በተመሳሳይ ጸታ መብት " ዙርያ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ግንኙነቱን የሚያበረታታ ማንኛውንም የሕትመት ውጤት ማተም አልያም በሌሎች የመገናኛ ብዙኃን ማሠራጨት አይችሉም። ይህን ካደረጉ በሕግ ተጠያቂ ይሆናሉ።

@tikvahethiopia