TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#US

አሜሪካ መላ ዜጎቿን ለመግደል በቂ የሆነ " ፌንታሊን " የተሰኘ አደንዛዥ ዕፅ ማያዟን አስታወቀች።

የአሜሪካ የዕጽ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን እየተጠናቀቀ ባለው 2022 መላውን የአሜሪካ ዜጋ ለመግደል በቂ የሆነ " ፌንታሊን " የተሰኘ አደገኛ አደንዛዥ ዕጽ መያዙን አሳውቋል።

ባለስልጣኑ፤ በአንዴ እንዲወሰዱ ተደርገው የተዘጋጁ እያንዳንዳቸው ሁለት ሚሊግራም የሚመዝኑ ገዳይ የሆኑ 379 ሚሊዮን ፌንታሊን የተሰኘ ዕጾችን ይዣለሁ ብሏል።

ይህ አደንዛዥ ዕጽ ከሄሮይን 50 እጥፍ በላይ ገዳይ እንደሆነ የገለፀ ሲሆን "ፌንታኒል አሜሪካ በአሁኑ ወቅት የገጠማት ገዳይ ስጋት ነው " ሲል ገልጾታል።

ይኸው የዕፅ ተቆጣጣሪ መ/ቤት እንደሚለው፤ ከፍተኛ መጠን ያለው ፌንታሊን ወደ አሜሪካ የሚገባው #ከሜክሲኮ ሲሆን ከ4 ሺ 500 ኪግ በላይ ፌንታሊንና 50.6 ሚሊዮን በእንክብል መልክ የተዘጋጁ ዕጾች ተይዘዋል።

በእንክብል መልክ የተዘጋጁት ዕጾች ህመም ማስታገሻ መድኃኒቶች እንዲመስሉ መደረጋቸውን ተገልጿል።

እየተጠናቀቀ ባለው በዚህ የፈረንጆቹ ዓመት የተያዘው የዕጽ መጠን ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በእጥፍ ጨምሯል።

አንደ ባለስልጣኑ መረጃ፤ በአሜሪካ የሚያዙት ዕጾች " በሲናሎዋ እና ጃሊስኮ " ዕጽ አዘዋዋሪ ቡድኖች አማካይነት ሜክሲኮ ውስጥ በምስጢራዊ ስፍራ በሚገኙ ፋብሪካዎች ይመረታሉ።

"ፌንታሊን" እጅግ አደገኛ የሆነ ዕጽ ሲሆን የእርሳስ ጫፍ ላይ ልትቀመጥ የምትችል ትንሽ መጠን እንኳን የመግደል አቅም አላት።

ማጠቃለያ፦

- ባለፈው ዓመት 100 ሺ አሜሪካውያን ከመጠን በላይ ዕጽ ወስደው ሕይወታቸው አልፏል። ከዚህ ውስጥ ሁለት ሦስተኛው ሞት ከፌንታሊን ጋር የተገናኘ ነው።

- በዚህ ዓመት የተያዘው ፌንታሊን መጠን 330 ሚሊዮን የአሜሪካ ነዋሪዎች መግደል የሚችል ነው።

#BBC

@tikvahethiopia
#USA #Election

" ስደተኞች የሀገራችንን ደም እየበከሉ ነው " - ዶናልድ ትራምፕ

ሪፐብሊካንን በመወከል ለፕሬዝዳንትነት የሚወዳደሩት ዶናልድ ትራምፕ ስደተኞች " የሀገራችንን ደም እየበከሉ ነው " በማለት ተናገሩ።

ትራምፕ ይህ ያሉት #ከሜክሲኮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች በሚገቡበት " ኒው ሃምሻየር " ግዛት ባደረጉት የምርጫ ቅስቀሳ ላይ ነው።

ትራምፕ ለ4 አመት የስልጣን ዘመን በድጋሚ የሚመረጡ ከሆነ ህገወጥ ስደትን እንደሚያስቆሙ እና በህጋዊ ሰደተኞች ላይ ደግሞ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚያደርጉ ተናገረዋል።

ትራምፕ ለደጋፊዎቻቸው ስደተኞች ከደቡብ አሜሪካ በተጨማሪ #ከአፍሪካ፣ ከእስያ እየመጡ ነው ሲሉም ተናግረዋል።

" ከሁሉም የዓለም ክፍል ወደ ሀገራችን የፈሰሱ ነው " ሲሉ አክለዋል።

ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው መስከረም ወር " ናሽናል ፐልስ " ከተባለው የቀኝ ዘመም ዌብሳይት ባደረጉት ቃለ ምልልስ ስደተኞች " ደማችንን እየበከሉት ነው " የሚል ተመሳሳይ ንግግር አሰምተው ነበር።

በወቅቱ ይህ የትራምፕ ንግግር " ዘረኝነት እና ጥላቻ " የሚያንጸባርቅ ነው የሚል ትችት አስነስቶ ነበር።

የያሌ ፕሮፌሰር እና በዘረኝነት ጉዳይ መጸሀፍ ያሳተሙት ጆናታን ስታንሊ ትራምፕ ቋንቋውን አሁንም ደግመው መጠቀማቸው አደገኛ ነው ብለዋል።

ፕሮሬሰሩ እንደተናገሩት ትራምፕ " የጀርመኖች ደም በጅዊሾች እየተበከለ ነው " የሚለውን የሂትለር ንግግር ያስተጋባ ነው ሲሉ ተችተውታል።

ስታሊ" ትራሞፕ ይህ ቃል በሁሉም የድጋፍ ሰልፎች ላይ እየደገሙት ነው። አደገኛ  የሆኑ ንግግሮችን መደጋገም እንዲለመዱ ያደረጋል " ብለዋል።

ፕሮፌሰሩ እንደተናገሩት ይህ በአሜሪካ የሚኖሩ ስደተኞችን ስጋት ላይ እንዲወድቁ ያደርጋል።

ባለፈው ጥቅምት ወር የትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳ ቃል አቀባይ ስቴቨን ቹንግ እንዲህ አይነት ቃላት በመጽሀፍ፣ በዜና እና በቴሌቪዥን የተለመድ ናቸው በማለት በትራምፕ የቀረበውን ትችት " ትርጉም የለሽ " ሲሉ አጣጥለውት ነበር።

Credit - AL AIN News

@tikvahethiopia