TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ድርድርን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምን አሉ ? ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦ " እስካሁን የተደረገ ድርድር የለም፤ እስከዚህ ደቂቃ ድረስ ፤ ስለድርድር ብዙ ሲወራ ሰማለሁ ግን እስካሁን ድርድር አላደረግንም፤ አላደረግንም ማለት እስከነአካቴው ድርድር የሚባል ነገር አይኖርም ማለት አይደለም። ድርድር ፣ ውይይት ማለት ችግር ተወግዷል ማለት ሳይሆን ችግር ለማስወገድ አማራጭ Alternative መንገድ አለው…
#ተጨማሪ

ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ስለ ድርድር የተናገሩት ፦

" ... አንድ የእስራኤል ፕሬዜዳንት በአንድ ወቅት ያሉትን ማስታወስ ፈልጋለሁ፤ እኚህ ፕሬዜዳንይ እስራኤል እየተዋጉ ከሀማሶች ጋር ከሂዝቦላህ ጋር ይደራደራሉ።

በነገራችን ላይ TPLF ከኦነግ ጋር ይደራደር ነበር፣ ደርግ ከሻዕቢያ እና TPLF ጋር ይደራደር ነበር ድርድር ማለት እርቅ ማለት አይደለም። ድርድር ውስጥ ብዙ የሚገኙ ነገሮች አሉ። ከምሳሌ ... ምሳሌው ይቅርብኝ ግን አሉ ጥቅሞች።

እናም እኚህ የእስራኤል ፕሬዜዳንት በጦርነት ጊዜ ምንም የሰላም ጫላንጭል እንደሌለ ሰላም ተስፋ እንደሌለው አስበን ጨክነን እንዋጋለን ፤ በድርድር ጊዜ ተጋጭተን እንደማናውቅ ጦርነት የሚባል እንዳልነበር በሰከነ መንፈስ እንደራደራለን ሁለቱንም የምናደርገው ለእስራኤል ጥቅም ነው ብለዋል።

እኛ በውጊያው ጊዜ የነበረን አቋም እና ሂደት ለምክር ቤት መግለፅ አይጠበቅብኝም አቋማችን ግልፅ ነው። በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ምንም የማንደራደር መሆኑ ግልፅ ነው።

አሁንም የምናደርገው የዛ ተገላቢጦሽ ሆኖ መታየት አለበት። ታስታውሳላችሁ በዝግ ስንወያይ ኢትዮጵያን አፍርሰው እነዚህ ሰዎች አዲስ አበባ አይገቡም ብያቹ ነበር በቲቪ አልተላለፈም ያ ውይይት ነበራችሁ ብዙዎቻችሁ ያኔ የተወያየነው ነገር ነው ተፈፅሞ ያየነው።

አሁንም #በድርድር የሚባል ነገር ካለ በዛው sprint ማየት ጥሩ ነው። የሰላም አማራጭ ካለ ፤ TPLF ቀልብ ከገዛ በጦርነት እንደማያዋጣው እንደማያሸንፍ ከተገነዘበ እኛ በደስታ ነው የምናየው። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba📍 በአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ፤ የቦሌ ክ/ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ሃላፊ በህገ ወጥ ንግድ ምክንያት የታሽገን የንግድ ቤት እከፍትልሃለሁ በሚል 100 ሺ ብር #ጉቦ ሲቀበል እጅ ከፍንጅ መያዙን የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታወቀ። የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ፤ የንግድ ፅ/ቤት ሃላፊው አቶ አለማየሁ ዋንዴቦ ታሽጎ የነበረን የንግድ ቤት በህገ ወጥ መንገድ ለመክፈት ተስማምቶ…
#ተጨማሪ

የቦሌ ክ/ ከተማ ንግድ ቢሮ ኃላፊው አቶ አለማየሁ ዋንዴቦ 100 ሺህ ብር ጉቦውን የተቀበሉት ታሽጎ የነበረውን " አቤኔዘር የተሽከርካሪ እጥበት አገልግሎት ድርጅት " ን አስከፍታለሁ ፤ የንግድ ፈቃዱንም እንዲታደስ አደርጋለሁ በማለት ነው።

የቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ እንዳለው ከሆነ፤ የድርጅቱ ባለንብረት በወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ታሽጎ የነበረው ድርጅታቸው እንዲከፈትና ንግድ ፈቃድ እንዲታደስላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ መነሻ በማድረግ የስራ ኃላፊው 100,000 ብር ጉቦ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

በኃላም 22 ጎላጎል ህንጻ በሚገኘው ካፌ ውስጥ ብሩን ሲቀበሉ #እጅ_ከፍንጅ ተይዘዋል ፤ አሁን ላይም ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ፖሊስ አስረድቷል።

#AMN

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #Tigray, #Mekelle 📍 ትላንትና በጉዞ ላይ እንደነበሩ የተነገረላቸው አስፈላጊ የሆኑ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦቶችን የጫኑት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ተሸከርካሪዎች የትግራይ ክልል መዲና መቐለ ደርሰዋል። ሁሉም (50ውም) ተሸከርካሪዎች በሰላም ነው መቐለ የደረሱት። ምን ይዘዋል ? ➡️ 1,000 ሜትሪክ ቶን ስንዴ እና ጥራጥሬ ፤ ➡️ 700 ሜትሪክ ቶን የጤና ፣ የተመጣጠነ ምግብ…
#WFP #USA #Ethiopia #TigrayRegion

የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ወደ ትግራይ ክልል #ተጨማሪ ኮንቮይዎችን ለመላክ ዝግጁ መሆኑና ፍቃድም እንዳለው ገልጿል።

ቀጣዩ የሰብዓዊ እርደታ ኮንቮይ በተቻለ ፍጥነት በሰላም እንዲሄድ በአፋር ክልል ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ድርጅቱ ገልጿል።

በሌላ በኩል ፥ አሜሪካ ትላንት በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ ፤ ከ1,700 ሜትሪክ ቶን በላይ ነፍስ አድን ሰብአዊ እርዳታ ትግራይ መግባቱ መልካም ዜና ነው ብላለች።

የእርዳታው እንዲደስ ትብብር ያደረጉትን የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የትግራይ ክልል አስተዳዳሪዎች እና የአፋር ክልል አስተዳዳሪዎችን እንደምታደንቅም ገልፃለች።

በተጨማሪም ፤ አሜሪካ የትግራይ ኃይሎች ከአፋር ክልል ኤሬብቲ መውጣታቸውን እንደምትደግፍ ገልፃ ከሌሎችም የአፋር አካባቢዎች የትግራይ ኃይሎች ቢወጡ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብላለች።

አሜሪካ በትላንት መግለጫዋ የኢትዮጵያ መንግስት እና የትግራይ ባለስልጣናት አሁን በታየው ለውጥ ቀጥለው ግጭቱን በድርድር፣ በዘላቂነት መፍታት የሚችሉበት መንገድ ማግኘት አለባቸው ብላለች።

ይህ እንዲሆንም በትግራይ ክልል መሠረታዊ አገልግሎቶች መመለስ እንዳለባቸው እና አካታች ፖለቲካዊ አካሄድ መተግበር እንዳለበት ገልጻለች።

የአሜሪካ መግለጫ : https://www.state.gov/delivery-of-humanitarian-assistance-in-tigray/

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የኮቪድ - 19 ወረርሽኝ እጅግ አስከፊ በነበረበት ወቅት በኮንትራንት ተቀጥረው ሀገራቸውን እና ህዝባቸውን ሲያገለግሉ የነበሩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት የጤና ባለሞያዎች ፦ " እኛ በጤና ሚኒስትር በኩል በኮቪድ ላይ በኮንትራት ተቀጥረን የምንሰራ ባለሙያዎች ነን። ኮቪድ ከጀመረ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ በተለያዩ ሆስፒታሎች ስናገለግል ቆይተናል። የጤና ሚኒሰትር እና ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በቋሚነት…
#ተጨማሪ

" የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በሃገራችን ከተከሠተበት ጊዜ ጀምሮ ወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በኮንትራት የተቀጠርን ባለሙያዎች ተፈላጊውን ውጤት አስመዝግበናል።

ወረርሽኙን በሚገ’ባ ተቆጣጥረን ጉዳቱን ቀንሰናል።

የኮንትራት ጊዜያችን ሰኔ 30 ቀን 2013 ዓ.ም ሲያበቃ ማሠናበቱ አስቸጋሪነቱን በማመን (ወረርሽኙ ስላልተገታ እና የባለሙያዎችን ሞራል ለመጠበቅ) ጤና ሚኒስቴር አምኖበት ሐምሌ 21 ቀን 2013 ዓ.ም ለየክልል ጤና ቢሮዎች በጻፈው ደብዳቤ በ2014 በጀት ዓመት ቋሚ ቅጥር እንዲያዝልን ገልጾ ነበር።

ነገር ግን ላለፉት 11 ወራት የክልል ጤና ቢሮዎች ወደ ቋሚ ቅጥር አላዛወሩንም። ከሥራ ያሠናበቱም ክልሎች አሉ። ለምንጠይቀው የመብት ጥያቄም ተገቢ መልስ አልተሠጠንም።

አሁንም አበርክቶታችን ታይቶ በ2015 በጀት ዓመት የቋሚ ቅጥር በጀት ተይዞልን ቅጥር ይፈጸምልን ዘንድ እንጠይቃለን! "

[ በኮቪድ19 መከላከል በኮንትራት የተቀጠርን ባለሙያዎች ]

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ገንዘባችንን ተበላን " ገንዘባችንን ተበላን ያሉ እጅግ በርካታ ወጣቶች የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የመልዕክት መቀበያን @tikvahethiopiaBOT አጨናንቀዋል። እኚሁ አባላት ገንዘባችን ተበላን ያሉት እራሱን ' FIAS 777 ' እያለ በሚጠራው ድርጅት ነው። ይሄ FIAS 777 የሚባለው " በኮሚሽን የሚሰራ ስራ " በማለት የበርካቶችን ገንዘብ ሲቀበል ነበር። ስለዚህ FIAS 777 ከዚህ በፊት…
#ተጨማሪ

በ " FIAS 777 " በሚል የሚንቀሳቀሱ አካላት አጭበረበሩን ካሉት መካከል እጅግ በጣም በጥቂቱ ፦

📩 " 40000 ብር ተበልቻለሁ "

📩 " በFIAS እኔም 30 ሺህ ብር ተብልቻለሁ "

📩 " እኔም ገንዘቤን ተበልቻለሁ ፤ ተበድሬ ነበር የገባሁት በሰዎች ጉትጎታ ኤጀንቶቹም አድራሻቸውን አጥፍተዋል "

📩 " በFIAS 777 የተዘረፉ በሚያውቋቸው ኤጀንቶች ላይ ክስ ለመስረት እያተዘጋጁ ነው "

📩 " ዘንድሮ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነኝ የምመረቅ ዘንድሮ ነበር ነገርግን ከቤተሰብ ለመመረቂያ ልብስ ብር አስልኬ fias777 ለተባለ አጭበርባሪ platform ልኬ ምንም ብር ሳይገባልኝ በሉት። ከተቻለ እርምጃ እንዲወሰድበት አሳስባለሁ። በተጨማሪ ሌሎች የማጭበርበሪያ መንገዶችን ለምሳሌ ፦ HDU, DH አና የመሳሰሉ platform እየተጠቀሙ ስለሆነ ማንም እንዳይጭበረበር "

📩 " የመንግስት ያለህ እኛ የFIAS ተጠቃሚወች ድርጅቱ ሀገረ መንግስቱ እውቅና የሰጠው ነው ተብለን ነው የገባንበት ሊንኩ ከተዘጋ ጀምሮ ገንዘብ ገቢና ወጭ እሚያደርጉልን ኤጀንቶች ቴሌግራም አካውንታቸውን ድሌት አርገው ከኛ ጋ የተጻጻፋትን አጥፍተው ነው ውሀ ሽታ የሆኑት በመቶ ሽወች የሚቆጠር ገንዘብ vIP Upgrade ያደረጉ ልጆች እያበዱ ነው። "

📩 " እዚህ ኢትዮጵያ ሲያስተባብሩ የነበሩት ይታወቃሉ ፤ ልብስ ለብሰው በአደባባይ ሲታዩም ነበር ፤ እንዴት እና ገንዘቡን የት እንዳደረሱት ይጠየቁ "

📩 " 30 ሽህ ብር አንድ ብር ሳላወጣ ተበልቻለው ባንክ የከፈልኩበትን ደረሰኝ ማቅረብ እችላለሁ "

📩 " በሰው በሰው ገብቼ 30 ሺህ ብር ተበልቻለሁ ፤ ስለድርጅቱ አንዳች ነገር አላውቅም "

📩 " እሄ website በ internet ነው እሚሰራው ግባ ብሎ በማላቀዉ ነገር fias 777 lay ኣስገብተዉ አሁን ላይ እስከ100 ሺህ ሚገመት ብር ከሰዉ ኣስበድረው ኣስበልተውኛል:: የ bank full መረጃ አለኝ "

📩 " ህጋዊ በመምሰል በጦርነት እና በዚህ በኑሮ ውድነት የሚሠቃየውን ሚስኪኑን ማህበረሰባችንን ዘርፎ ስለጠፋው fias777 ስለሚባል ድርጅት መናገር ፈልጋለሁ። አብዛኛው ሰው ትርፋ አገኛለሁ በሚል መንፈስ ከሰው በመበዴር፣ መሬት በመሸጥ፣ ቋሚ ንብረቶቹን ሳይቀር በመሸጥ ለዚህ ድርጂት መጀመሪያ አካባቢ ከ1000 እስከ 30,000 ብር ገቢ ያዴረጉ ሲሆን አሁን በቅርቡ ሊዘጉት አካባቢ ዴግሞ እስከ 180,000 ብር ድረስ ለዚህ ድርጅት ገንዘባቸውን ገቢ በማድረግ ገንዘባቸው የውሀ ሽታ ሁንዋል "

(ውድ ቤተሰቦቻችን ፦ ይህ ከብዙ በጥቂቱ ከተላኩት ውስጥ የቀረበ ሲሆን አብዛኛው ሰው በሰው በሰው መግባቱን እና አሁን ስራውን እንሰራለን የሚሉ አካላት መጥፋታቸውን የሚጠቁም ነው ፤ ተበላ የተባለው ገንዘብም እጅግ በጣም ከፍተኛ ነው። የሚመለከተው አካል ገንዘብ ገቢ በተደረገባቸው አካውንቶች መሰረት ሰዎችን ተጠያቂ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።)

ከዚህ በፊት በኦንላይን በሚሰራ ስራ በርካታ ትርፍ እናስገኛለን እያሉ ስለሚንቀሳቀሱ አከላት ጥንቃቄ እንዲደረግ መልዕክት መተላለፉ የሚዘነጋ አይደለም ፤ አሁንም በሌላ ስም የሚንቀሳቀሱ አሉ ጥንቃቄ ይደረግ።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
#EthiopianAirlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሠረታዊ የሰራተኛ ማህበር አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ማካሄዱን ገለፀ። ጉባኤው ትናንትና እና ዛሬ ነው የተካሄደው። ትላንህ ጉባኤው በማህበሩ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኪያ ለማ፣ በአየርመንገዱ የሰዉ ሀብት ም ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ዘነበወርቅ ገ/ጻድቅ የመክፈቻ ንግግር የተጀመረ ሲሆን የማህበሩ የስራና የኦዲት ሪፓርቶች፣ የማህበሩ የ2022/2023…
#ተጨማሪ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሰረታዊ የሰራተኛ ማህበር አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤን በሚመለከት ቲክቫህ ኢትዮጵያ አንድ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ መመልከት ችሏል።

ይኸው የፍርድ ቤት ትዕዛዝ በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የተሰጠ ነው።

ትዕዛዙም ፤ " በኢትዮጵያ አየር መንግድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሰረታዊ ሰራተኛ ማህበር ሊቀመንበር በሆኑት በተጠሪ ጥሪ ተደርጎ በስካይ ላይት ሆቴል እየተከናወነ ያለ ጠቅላላ ጉባኤ ካለ ከዛሬ 8/11/2014 ዓ/ም 6:05 ጀምሮ ከዚህ ፍርድ ቤት ተለዋጭ ትዕዛዝ እስከሚሰጥ ድረስ ጠቅላላ ጉባኤው እንዳይከናወን ታዟል። የእግድ ትዕዛዝ ትዕዛዙ ለሚመለከታቸው ይድረስ " ይላል።

ትዕዛዙ የተሰጠው 4 የማህበሩ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ፤ በተጠሪ የማህበሩ ሊቀመንበር ኢ/ር ተሊላ ደሬሳ ላይ ባቀረቡት አቤቱታ አማካኝነት ነው።

የማህበሩ ዋና ፀሀፊ ትላንት እና ዛሬ ጠቅላላ ጉባኤውን በስኬት መጠናቀቁን ያሳወቁ ሲሆን ዛሬ ምንም አይነት የእግድ ደበዳቤ እንዳልደረሳቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ጉባኤው ታግዷል፣ አልተካሄደም በሚል የሚሰራጨው መረጃ ውሸት ነው ብለዋል።

ግለሰቦቹ የማህበሩን ንብረቶች በመበዝበዝ ላልተገባ ጥቅም በማዋላቸው የማህበሩ ምክር ቤት እና ጠቅላላ ጉባኤ ያባረራቸው እና ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ ያሉ ናቸው ሲሉ ገልፀዋል።

4 ስራ አስፈጻሚ አባላት ጠቅላላ ጉባኤን ማገድ አይችልም ያለው ማህበሩ ፤ የማህበሩ ከፍተኛ ባለስልጣን ጠቅላላ ጉባኤው እንደሆነ መታወቅ አለበት፤ በዚህም መነሻነት ነው የሚመለከታቸው ከፍተኛ የድርጀቱ መሪዎች በጉባኤው ላይ የተገኙት ፤ ጉባኤው ስኬታማ ነበር ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የጉራጌ ዞን ምክር ቤት #በክላስተር_ለመደራጀት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ አድርጓል። የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ፤ ዛሬ ሐሙስ ባካሄደው አስቸካይ ጉባኤ ከሌሎች የአስተዳደር መዋቅሮች ጋር በክላስተር ለመደራጀት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ በአብላጫ ድምጽ ውድቅ አደርጓል። የጉራጌ ዞንን በደቡብ ክልል ስር ከሚገኙ ሌሎች 4 ዞኖች እና አንድ ልዩ ወረዳ ጋር በማዳመር የጋራ ክልል ለመመስረት የቀረበው…
#ተጨማሪ

" መንግስት የዞኑ ህዝብ በም/ቤት ያፀደቀውን ህገመንግስታዊ ጥያቄ #በድጋሚ ሊያይ ይገባል " - የጉራጌ ዞን ም/ቤት

የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ በጉራጌ ዞን ዋና አስተዳደር የቀረበውን #በክላስተር የመደራጀት ምክረ ሐሳብ በአብልጫ ድምፅ #ውድቅ አድርጎታል።

የዞኑ ህዝብ በም/ቤቱ ያፀደቀው ህገመንግስታዊ ጥያቄ መንግስት በድጋሚ ሊያይ ይገባል በሚል ነው ምክር ቤቱ በአብላጫ ድምፅ የክላስተር ውሳኔውን ምክረ ሀሳብን ውድቅ ያደረገው።

የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ህዳር 17/2011 ዓ.ም. ባደረገው ጉባኤ ዞኑ ራሱን ችሎ ክልል ለመሆን ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል።

የደቡብ ክልልን ለሁለት የሚከፍለውን የክልልነት አደረጃጀት በም/ቤቱ ባለማጽደቅ የጉራጌ ዞን #ብቸኛው ሆኗል።

ቀሪዎች የደቡብ ክልል 10 ዞኖች እና ስድስት ልዩ ወረዳዎች በአንድ ላይ ሁለት ክልል የመመስረት ውሳኔን በምክር ቤቶቻቸው ማጽደቃቸው ይታወሳል። 

ፎቶ ፦ የጉራጌ ዞን መንግሥት ኮሚኒኬሽን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል መፈፀሙን ፖሊስ ገልጿል። በአዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ቦሌ አራብሳ ኮምዶሚኒየም በሁለት ህፃናት ላይ እጅግ አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል። የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ሲሆን ፤ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ የምትሰራ አንዲት ግለሰብ ክርስቲያን መላኩና ወንጌላዊት መላኩ የተባሉ…
የፖሊስ መልዕክት !

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ የሰጡት ቃል ፦

" ምንም በማያውቁት ጉዳይ በህጻናቱ ላይ የተፈጸመው ይህ አሰቃቂ ወንጀል ሁሉንም በእጅጉ አሳዝኗል።

ወላጆች የሚቀጥሯቸው የቤት ሠራተኞችን ማንነት ጠንቅቀው ማወቅ ይገባቸዋል።

እንደ ቤተሰብ ሆነው የሚኖሩ የቤት ሠራተኞች እንዳሉ ሁሉ እንደዚህ አይነት አሰቃቂ ወንጀል የሚፈጽሙም ስላሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት። "

#ተጨማሪ_መረጃ

• በአንድ ቀን በአሰቃቂ ሁኔታ ሁለት ታዳጊ ልጆቻቸውን ያጡት ወላጆች በከባድ ሐዘን ውስጥ ይገኛሉ።

• ወንጀሉ በተፈጸመበት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎችም በእጅጉ ተረብሸው ነው የሚገኙት።

• ፖሊስ በወንጀሉ ዙሪያ ተጨማሪ ምርመራ እያደረገ ነው።

- ተጠርጣሪዋ ህጻናቱን አንቃ እና ስለት ተጠቅማ በአስቃቂ ሁኔታ መግድሏ የሚያመላክቱ መላምቶች አሉ።

- ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳት ለማወቅ ምርመራዎች እየተካሄዱ ነው።

- በወንጀሉ የተጠርጠረችው ግለሰብ በቤት ሠራተኛነት ግድያው ለተፈጸመበት ቤተሰብ ስታገለግል ቆይታለች።

• ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን የፈጸመችው ወላጆች የሌሉበትን ሰዓት ጠብቃ ነው።

መረጃው ም/ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ የአማርኛ አገልግሎት ከሰጡት ቃል የተወሰደ ነው።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

በነገው ዕለት የ2015 የትምህርት ዘመን ይጀምራል።

በዚሁ ዕለት ትምህርት ሚኒስቴር 5 ዓመታት ሲያዘጋጅ የቆየው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መተግበር ይጀምራል፡፡

በሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ወደ ሙሉ ትግበራ የሚገባው የአዲሱ የትምህርት ስርዓት ከነገ ጀምሮ በኢትዮጵያ በሚገኙ 80 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በሙከራ ደረጃ ይሰጣል።

#ለማስታወሻ - የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ፦

- ከኢንተርናሽናል እና የማህበረሰብ  ትምህርት ቤቶች ውጭ ስርዓተ ትምህርቱ በሁሉም የአገሪቱ ክፍል ባሉ የግል እና  የመንግስት ትምህርት ቤቶች ይተገበራል።

- ግብረ ገብ ፣ አገር በቀል ዕውቀት ፣ ሙያና የቀለም ትምህርት፣ ቴክኖሎጂ፣ ምርትና ተግባር፣ ጥናት እና ምርምር ትኩረት ተደርጎባቸው ይሰጣሉ።

- ከ1ኛ - 6ኛ ክፍል የግብረ ገብ ትምህርት ይሰጣል።

- ለ7ኛ እና ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ራሳቸውን የቻሉ የትምህርት ዓይነቶች ሆነው ይሰጡ የነበሩት ኬሚስትሪ ፣ ባዮሎጂ እና ፊዚክስ " ጄኔራል ሳይንስ " ተብለው ይሰጣሉ። ጆግራፊና ሂስትሪም ተቀናጅተው የሚሰጡ ይሆናል።

- ከ1ኛ - 6ኛ ክፍል ላሉ የክፍል ደረጃዎች ትምህርት በአፍ መፍቻ ቋንቋ ይሰጣል፤ ከ7ኛ ክፍል -12ኛ ክፍል ያሉት ደግሞ ሁሉም ተማሪ በእንግሊዘኛ ቋንቋ ይማራል።

- ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ያሉት ተማሪዎች የእንግሊዘኛ ቋንቋን እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ይወስዳሉ።

- 3ኛ ክፍል ላይ ተጨማሪ ቋንቋዎችን መስጠት ይጀመራል፤ በክልሎቹ ውስጥ በስፋት የሚነገረውን #ተጨማሪ_ቋንቋ በመምረጥ ተማሪዎቹ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲወስዱት ይደረጋል።

-  አጠቃላይ ፈተና በክልል ደረጃ 6ኛ ክፍል ላይ እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ 8ኛ እና 12ኛ ክፍል ላይ ይሰጣል።

- የ7ኛና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች " ኬሪየር ኤንድ ቴክኒካል ኤጁኬሽን " የተባለ ትምህርት ይሰጣቸዋል። የእርሻ ትምህርት፣ አካውንቲንግ፣ ቢዝነስና ጀነራል የሆነውን የሥራና ክህሎት ትምህርት በሙያ ትምህርት ተካቶላቸው ይሰጣቸዋል።

- 11ኛ እና 12ኛ ክፍሎች ላይ ጤና ፣ ግብርና፣ የእርሻ ትምህርት፣ ማኒፋክቸሪንግ፣ ኮንስትራክሽን ፣ ቢዝነስ ፣ አካውንቲንግ የመሳሰሉት የሙያ ትምህርትነቶችን እንዲማሩ ይደረጋል። 11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከእነዚህ የሙያ ትምህርቶች ውስጥ የመረጡትን ይወስዳሉ።

- የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍልን እንዲሁም ከ1ኛ - 8ኛ ክፍል ያሉ የተመረጡ 5 የትምህርት አይነቶችን መጸሐፍት ዝግጅት ትምህርት ሚኒስቴር ያከናውነዋል ፤ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ያለውን የትምህርት መፀሐፍት ክልሎች በራሳቸው ባህልና አካባቢያዊ ሁኔታ ቃኝተው ያዘጋጁታል።

መረጃው ከትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ / ኢፕድ የተወሰደ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Oromia የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ም/ ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ በኦሮሚያ ያለው ጦርነት በዜጎች ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል አሉ። አቶ ጃዋር ፤ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በጮቢ እና በሜታ ወልቂጤ (ምዕራብ ሸዋ)፣ በነቀምቴ (ምስራቅ ወላጋ)፣ ቢላ፣ ናጆ፣ ማንዲ (ምዕራብ ወለጋ) በመቶዎች የሚቆጠሩ ንፁሀን ዜጎች ተገድለዋል ብለዋል። ንፁሃን በሚደረገው የተኩስ…
#ተጨማሪ

አቶ ጃዋር መሀመድ ከኢትዮጵያ ቀውስ ጋር በተያያዘ ‘ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ’ ተአማኒነት ጥያቄ ውስጥ እንዲገባ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ እየመረጡ መጮሃቸው ነው ብለዋል።

" ባለፉት አራት አመታት በኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ የጦር ወንጀሎች እና የዓለም አቀፍ የሰብአዊ ህግ ጥሰቶች በተደጋጋሚ ተፈጽመዋል " ያሉት አቶ ጃዋር ፤ በዓለም አቀፉ ህበረሰብ ምንም አይነት ትኩረት አልተሰጠም ፤ ሌላው ቀርቶ የተለመደውን ‘ በጣም ያሳስበናል ’ የሚሉ ነገሮችን አይሉም " ሲሉ ነቅፈዋል።

" አልፎ አልፎ ሽፋን ይሰጡ የነበሩትም አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና ሂውማን ራይትስ ዎች እንኳን ተስፋ የቆረጡ ይመስላሉ " ሲሉ ገልፀዋል።

" እየመረጡ መጮህ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም አያመጣም። " ያሉት አቶ ጃዋር መሀመድ " ወይ ለአጠቃላይ ሀገራዊ የሰላም ሂደት እንሰራለን ወይም ነገሮች ከቁጥጥር ውጪ ሆነው ሲቀጥሉ እንመለከታለን። " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba ነገ የሚወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ... የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ታምራት የተናገሩት ፦ " በእጣው ብቁ የሚሆኑት የ20/80 (ስቱዲዮ ፣ ባለ 1 እና ባለ 2) ነባር ተመዝጋቢዎች (1997) በመመሪያው መሠረት ዝቅተኛውን የ60 ወራት ቁጠባ መጠን እንዲሁም የባለ 3 መኝታ ነባርና አዲስ ተመዝጋቢዎች (2005) ዝቅተኛውን የ84 ወራት ቁጠባ መጠን ያሟሉ።…
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ20/80 14ኛ ዙር እና የ40/60 3ኛ ዙር የጋራ መኖርያ ቤት ዕጣ #ዛሬ_ከሰዓት ይወጣል።

ይኸው እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአዲስ አበባ ነዋሪ የሚጠብቀው የዕጣ አወጣጥ ስነ ስርዓት በቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት ለህዝብ ይተላለፋል ።

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ/Addis TV የጋራ መኖሪያ ቤቶቹን የዕጣ አወጣጥ ስነ ስርዓት በቀጥታ ስርጭት እንደሚያስተለልፈው ቀደም ብሎ አሳውቋል።

እንደ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገለፃ ፤ ዛሬ ዕጣ የሚወጣባቸው በ20/80 18,930 ቤቶች እና በ40/60 6,843 ቤቶች በድምሩ 25, 791 ቤቶች ሲሆኑ ከፍተኛ ጥያቄ ሲቀርብበት የነበረው የባለ ሶስት መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎችን ጉዳይ ምላሽ ለመስጠት #ተጨማሪ 300 (ሶስት መቶ) ቤቶችን ቀሪ ስራዎችን በማከናወን ለነባርና ለአዲሰ ተመዝጋቢዎች በዕጣ ለማስተላለፍ ዝግጁ ተደርጓል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ከደቂቃዎች በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የዕጣ ማውጣት ስነስርዓት በይፋ ይካሄዳል።

ይኸው የዕጣ ማውጣት ስነስርዓት በቀጥታ ስርጭት ለህዝብ ይሰራጫል።

ዛሬ ዕጣ የሚወጣባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፦

👉 በ20/80 18,930 ቤቶች
👉 በ40/60 6,843 ቤቶች
👉 አጠቃላይ 25, 791 ቤቶች

እንደ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገለፃ #ተጨማሪ 300 (ሶስት መቶ) ቤቶችን ቀሪ ስራዎችን በማከናወን ለነባርና ለአዲሰ ተመዝጋቢዎች በዕጣ ለማስተላለፍ ዝግጁ ተደርጓል።

ውድ ቤተሰቦቻችን ፤ የዕጣውን አወጣጥ ሥነሥርዓት ተከታትለን የምናሳውቅ ሲሆን የሚመቻችሁ በአዲስ ቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት መከታተል እንደምትችሉ ለመጠቆም እንወዳለን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ተጨማሪ : ከዛሬው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ላይ ከቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት የተወሰዱና ከላይኛው የቀሩ የጥቂት ባለዕድለኞች ስም ከላይ አያይዘናል።

ዛሬ የወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ፖስት ኦዲት ከተደረገ በኃላ በአዲስ ልሳን ጋዜጣ ታትሞ እንደሚወጣ ነው የሚጠበቀው ፤ ሙሉ ዝርዝሩን እንዳገኘን የምናጋራችሁ ይሆናል።

(ከላይ ያያዝናቸው ምስሎች ከቀጥታ ቴሌቪዥን የተወሰዱ በመሆኑ ጥራት ይጎድላቸው ፤ ለዚህም ይቅርታ እንጠይቃለን)

@tikvahethiopi
TIKVAH-ETHIOPIA
#ባጃጅ • " ገደቡ ከነገ ጀምሮ ይነሳል " • " በየትኛውም ርቀት ከ5 ብር በላይ ማስከፈል አይቻልም " በአዲስ አበባ በባጃጅ አገልግሎት ላይ የተጣለው እግድ ከነገ ጀምሮ እንደሚነሳ የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል። ቢሮው ዛሬ በሰጠው መግለጫ የባጃጅ አገልግሎት ላይ የተጣለው እግድ ከነገ ቅዳሜ መጋቢት 8/2015 ጀምሮ እንደሚነሳ አስታውቋል። የባጃጅ ተሽከርካሪዎች በየትኛውም ርቀት ከ5 ብር በላይ…
#ተጨማሪ

" የስራ ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰአት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ብቻ ነው " - የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ

ተቋርጦ የነበረው የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ከነገ ጀምሮ ባጃጆቹ በተመደቡላቸው መስመሮች ብቻ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

በመግለጫው ምን ተባለ ?

- ከአገልግሎቱ ጋር በተያያዘ ለተፈጠሩ ችግሮች መንስኤ ናቸው የተባሉት ፦
• ህግን አክብሮ አገልግሎት አለመስጠት፣
• በአብዛኛው አሽከርካሪ ዘንድ ደረጃውን የሚመጥን መንጃ ፍቃድ አለመያዝ
• የታሪፍ ስርዓት አለመኖር ዋንኞቹ ናቸው።

- አሁን በተዘጋጀ መመሪያ መሰረት ቢሮው በለያቸው የስምሪት መስመሮች አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል።

- 138 ጊዜአዊ ታፔላዎችን ከዋናው መስመር ውጪ ተዘጋጅተዋል።

- የትራፊክ ምልክቶች ተከላ ማከናወን እና ማህበራትን ማደራጀት ዋንኛ ስራ ነበር። በ8 ክ/ከተሞች 123 ማህበራትን የማደራጀት ስራ የተሰራ ሲሆን አገልግሎቱም በኮድ 1 ታርጋ ብቻ ይሰጣል።

- የተሳፋሪ መጠን አሽከርካሪውን ጨምሮ 4 ሰው ብቻ ሴሆን የስራ ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰአት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ብቻ ነው። ህጉን ተላልፈው የተገኙ አሽከርካሪዎች በየደረጃው ቅጣት ይጣልባቸዋል።

- በከተማው መደበኛ ትራንስፖርት በማይገኝበት ከ0 ነጥብ 9 እስከ 2 ነጥብ 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ብቻ በ5 ብር ታሪፍ አገልግሎት እንዲሰጡ ተወስኗል።

- የባጃጅ ተሽከርካሪዎች በየትኛውም ርቀት ከ5 ብር በላይ ማስከፈል አይችሉም።

Credit : ADDIS MEDIA NETWORK / FBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ካህኑን ማን ገደላቸው ? " ኃይሌ ጋርመንት " የሁርሲሳ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ቀዳሽ ካህን ቀሲስ ዐባይ መለስ " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ አካላት በተፈፀመባቸው ጥቃት ተገድለዋል። ካህኑን የሚያውቋቸው አገልጋዮች /ምዕመናን  ስለነበረው ሁኔታ / ስለጥቃቱ ምን አሉ ? (ለማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ከተናገሩት የተወሰደ) ቃላቸውን የሰጡ ምዕመን አንድ ፦ " ትላንት/መጋቢት…
#ተጨማሪ

የቀሲስ ዐባይ መለሰ ግድያ በስፋት ተሰማ እንጂ የሁርሲሳ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ባለችበት አካባቢ ብዙ ፈተና ይገጥማት እንደነበር አገልጋዮችና ምዕመናን ለ " ማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን " ተናግረዋል።

እዛው ቤተክርስቲያን አካባቢ ስልክ የተቀሙ ፣ ጩቤ በያዙ ሰዎች ማስፈራሪያ የደረሰባቸው ፣ ሻሽ ጠምጥመው ሲሄዱ #የተመቱ መኖራቸውን ጠቁመዋል።

ያለውን ችግር የሚመለከታቸው አካላት እንዲያዩ ጠይቀዋል።

አንድ ምዕመን ፤ " ቤተክርስቲያን አምልኮተ እግዚአብሔር የሚፈፀምባት መሆኗን ገልፀው ተልዕኮዋን ለማስፈፀም ሰላም ያስፈልጋታል " ብለዋል።

" የቤተክርስቲያን ኃላፊዎች ሆኑ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ይህች ቤተክርስቲያን ከሚገባው በላይ እየተጎዳች ስለሆነ ጉዳቷን ለሚመለከተው አካል ማቅረብ የግድ ነው ፤ መስዋዕትነት መክፈልም ያስፈልጋል ምክንያቱም ቅዱስ ስጋ ክቡር ደሙን ካልተመገብን እኛ ሀገረ እግዚአብሔርን አናገኝም " ሲሉ ገልጸዋል።

መንግስት የመጀመሪያ ስራው ህግ ማስከበር መሆኑን የገለፁት እኚሁ ምእመን እንዲህ ያለ ጥቃት (በቀሲስ ዐባይ መለሰ ላይ የደረሰ) እንዳይደርስ ዜጎች ወጥተው እንዲገቡ ተገቢ የሆነ ጥበቃ ሊያደርግ ይገባዋል " ብለዋል።

" ትልቁ ችግር መንግስት ስራውን ባለመስራቱ ምክንያት ነው ይሄ ሁሉ ችግር እየተፈጠረ ያለው " የሚሉት ምዕመኑ " መንግሥት ከማንኛውም ነገር በፊት ቅድሚያ መስጠት ያለበት ሰላም ለማስከበር ነው ፤ ዜጎች የፈለጉበት ቦታ ሰርተው ፤ ጥረው ግረው እንዲኖሩ ዕልውናቸውንና ደህንነታቸው / ዕልውናችንን መጠበቅ ነው " ሲሉ  አስገንዝበዋል።

" ይህ ባለመሆኑ ነው ሰው በወጣበት የሚቀረው እዚሁ ሰፈሩ ውስጥ ጥቃት የሚደርሰው ፤ መንግሥት እንዲያህ አይነት ድርጊት እንዳይፈፀም ስራው ባለመስራቱ ነው ችግር እየተፈጠረ ያለው ፤ መንግስት ስራውን ሊሰራ ይገባል " ብለዋል።

@tikvahethiopia
#NedajApp

በነዳጅ የሞባይል መተግበርያ ሲመዘገቡ ምንም አይነት #ተጨማሪ_ክፍያ እንደሌለው ያውቃሉ ?

1⃣🅾🅾🅾 ሺህ በላይ በተመዘገቡ የነዳጅ ማደያዎች የነዳጅ አፕሊኬሽንን ተጠቅመው ይቅዱ !!

- ቀላል፣ፍጣን እና ምቹ

- በሲቢኢ ሞባይል ባንኪንግ (Utilities)ገብተው አካውንቶን Link ያርጉ

- አሁኑኑ ከPLAY STORE እና APP STORE ያውርዱ፣ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሂሳብ አካውንትዎ ጋር ያስተሳስሩ!

For Android: https://play.google.com/store/apps/details?id=com.eaglelionsystems.nedaj

For iOS:
https://apps.apple.com/us/app/nedaj/id1639807926

#Nedaj #nedajapp
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ተጨማሪ

የባህር ዳር ፣ ጎንደርና ሸዋሮቢት ነዋሪዎች ምን አሉ ?

የባህር ዳር ፣ ጎንደር ፣ ሸዋሮቢት ከተማ ነዋሪዎች ከተማቸው በመከላከያ ሰራዊት ስር እንደሚገኝና ዛሬ ተኩስ እንዳልነበር ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።

#ባህርዳር

ነዋሪ 1

" ከትለንት ከግማሽ ለሊት በኃላ መከላከያው ተቆጣጥሮታል።

ተኩስም የለም፤ መከላከያው ተቆጣጥሮታል። አንፃራዊ ሰላም አለ።

መከላከያው ነው እየተንቀሳቀሰ ያለው። ሰውም እንደ ሰሞኑን ሳይሆን መንቀሳቀስ ጀምሯል። ግን አገልግሎት መስጫ ተቋማት ዝግ ናቸው በተረፈ ቁስለኛ እየተነሳ ሃኪም ቤት እየሄደ ነው ፣ የሞተውም እየተቀበረ ነው።

ዘንዘልማ አካባቢ ብዙ ሰው ስለሞት እነሱ እየተነሱ እየተቀበሩ ነው። ከሟቾች ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ የተወሰኑ ናቸው እንጂ በቤተሰብ አማካኝነት እዛው እየተቀበረ ነው። ብዛት ያለው ሰው ደግሞ ከመኮድ ይወረወር የነበረ ከባድ ተወዋሪ መሳሪያ እሱ ነው ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰው። መኖሪያ ቤት ላይ እየወደቀ፤ ህፃናቶችም ሞተዋል።

ቁጥሩን ባልገልፅም ብዙ ሰላማዊ ሰው ሞቷል፣ በተለይ ቀበሌ 14 ላይ ከፍተኛ ውጊያ ነበር፤ በጣም ብዙ ሰው ሞቷል። ዛሬ ብዛት ያለው ሰው ቀብር ነው የዋለው። ህዝቡ እየወጣ መቅበር ጀምሯል። "

ነዋሪ 2

" እኛ ኤርፖርት አካባቢ ነን። ዛሬ ሰላም ነው። ተኩስም የለም። የተረጋጋ ነው። ግን ብዙ ሰው ፍራቻ ስላለው ወደ ከተማ አይሄድም። በጣም ብዙ የሞተ ሰው ስላለ ፍራቻ አለ። ነገር ግን ከንጋት ጀምሮ ምንም ድምፅ የለም።

በአብዛኛው ሲቪልያን ነው የሚሞቱት ካለመሳሪያ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ፣ የሚታኮሱት አይደለም የሚሞቱት በብዛት። ጀሌው አለ አይደል በአጋጣሚ መንገድ ለመዝጋት የሚሄደው ነው። "

#ጎንደር

ነዋሪ 1

" ጎነደር ከትላንት ማታ ጀምሮ ማለት ይቻላል ተኩሱ ቆሟል። መከላከያው ከተማው ውስጥ ያሉትን መንገዶች የማፅዳት ስራ እየሰራ ነው ያለው። መንገዶች በድንጋይም፣ በእንጨትም ተዘጋግተው ስለነበር።

ሌሎች እንቅስቃሴዎች ገና ናቸው። የሰው እንቅስቃሴም የለም። ቤት ውሥጥ ቁጭ ብለን ነው የሰነበትን ዛሬ ሳምንታችን ነው። የሚቀጥለው ምን እንደሚሆን እየጠበቅን ነው።

በትክክል ስለደረሰው ጉዳት ይህ ነው ማለት ባልችልም፤ ሰው ግን ለሳምንት ከገበያ ከሌሎችም አገልግሎቶች ተገልሎ መቆየቱ ብዙ ሰው አላሰበውም እሮብ ማታ ድረስ ጤናማ ስራውን እየሰራ ከዚያ ምሽት በኃላ ግን መውጣት መግባት  የማይቻልበት፣ የጥይት ድምፅ የከባድ መሳሪያ ሲስተናገድ ነበር ወደ ህክምና ለመሄድም ትራንስፖርት የለም ጉዳቱ ቀላል አይሆንም። "

ነዋሪ 2

" ዛሬ ተኩስ የለም። ከተማ ውስጥ ምንም እንቅስቃሴ የለም። ከመከላከያ ውጭ የሚንቀሳቀስ የለም። ሰው ከቤት አልወጣም።

ሰላማዊ ሰዎች ብዙ ተጎድተዋል።

ህክምና ለማግኘትም አልተቻለም። ጉዳቱ ከመብዛቱ አንፃር እንዲሁም አንስቶ የሚወስድም አልተገኘም።

የሞቱ ሰዎች ትላንት አልፎ አልፎ ተቀብረዋል። ከሟች ብዛት አንፃር ያልተቀበሩ አሉ። "

በተመሳሳይ በሸዋሮቢት ከተማ ሀገር መከላከያ የገባ ሲሆን ዛሬ የተረጋጋ ሁኔታ መኖሩን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

በግጭቱ ሳቢያ ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውና መቁሰላቸውን የገለፁት ነዋሪዎቹ የሞቱ ሰዎች እየተለቀሙ ተቀብረዋል።

አንድ ነዋሪ እሳቸው ብቻ ባረጋገጡት 13 ንፁሃን እንደሞቱ ገልፀው ሚካኤል ቤተክርስቲያን 10 ሰው፣ ማርያም 2 ሰው፣ ሙስሊም መቃብር 1 ሰው መቀበሩን መረጃ እንዳላቸው ተናግረዋል። በየገጠሩ ያለው ገና አልታወቀም ሲሉ አክለዋል።

ትራንስፖርት አለመኖሩ፣ መንቀሳቀስም አስፈሪ ስለነበር ተጎጂዎችን ወደሆስፒታል ለመውሰድ አስቸጋሪ እንደነበር ነዋሪዎች ለሬድዮ ጣቢያው ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ቻይና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወደ ቻይና አቅንተው በቻይና ይፋዊ ጉብኝት እያደረጉ ናቸው። ከጠ/ሚ ፅ/ቤት በወጣ መረጃ የቻይናው ጠ/ሚኒስትር ሊ ኪያንግ ለዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ይፋዊ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በኃላም የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል። በዚህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የምጣኔ ኃብት ትብብር ግንኙነት ማጠናከሪያ መንገዶች ላይ መክረዋል ተብሏል። ከሁለትዮሽ…
#UPDATE

ቻይና የሚገኙት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከልዑካቸው ጋር በመሆን ከቻይናው ፕሬዝደንት ሺ ጂንፒንግ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል።

ፕሬዝዳንት ሺ ፤ በኢትዮጵያ #ብሪክስን መቀላቀል ሁነት ለጠቅላይ ሚኒስትሩን " እንኳን ደስ ያለዎ " ብለዋቸዋል።

የኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነትም ከሁሉን አቀፍ ፅኑ ግንኙነት ወደ ሁኔታ የማይፈታው ስልታዊ ትብብር እና ወዳጅነት (All Weather Strategic Cooperation Partnership) ደረጃ ከፍ ማለቱን በይፋ አብስረዋል።

ፕሬዝዳንቱ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አድንቀው ከቻይናው አረንጓዴ ልማት ፖሊሲ ጋር ተናባቢ በመሆኑ የግሪን ቤልት እና ሮድ አካል ሆኖ ሊደገፍ እንደሚችል አረጋግጠዋል ተብሏል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ፤ የቻይና ኢንቬስትመንት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እመርታ የሚኖረውን አስተዋፅዖ ያነሱ ሲሆን በተለይም በ5ቱ ቁልፍ ምሰሶዎች፦
- በግብርና
- ማኑፋክቸሪንግ
- አይሲቲ
- ማእድን ልማት እና ቱሪዝም #ተጨማሪ ኢንቬስትመንት እንዲኖር የማበረታቻ ጥሪ ማቅረባቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
" የሃይማኖት ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል ?

በኢትዮጵያ አዲስ የተዘጋጀ " #የሃይማኖት_ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ አለ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በርካታ ጉዳዮችን ይዟል።

አንዱ የአምልኮና የመቃብር ቦታን የተመለከተ ሲሆን ፥ ረቂቅ አዋጁ ለሃይማኖት ተቋማት የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት ይወሰናል ይላል።

ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ ዓላማ የተሰጠ ቦታ አለመኖሩ ወይም ደግሞ #ተጨማሪ_ቦታ መስጠት አስፈላጊ መሆኑ መረጋገጥ እንዳለበትም ይገልጻል።

በተለያዩ ቤተ እምነቶች መካከል ላይ የሚኖረው ርቀት ቢያንስ 500 ሜትር መሆን አለበትም ይደነግጋል።

ትምህርትና የሃይማኖት ተግባራትን በተመለከተ ረቂቁ ፥ መደበኛ ትምህርት በሚሰጡ የመንግሥት / የግል ተቋማት የሚሰጠው ትምህርት ሃይማኖታዊ ይዘት የሌለው መሆን አለበት ይላል።

በትምህርት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውስጥ ሃይማኖታዊ ትምህርትን ማስተማር ወይም በቡድን ማምለክ ፈጽሞ የተከለከለ ስለመሆኑ ይገልጻል።

ሌላውረቂቁ ማንነትን ለመለየት ሚያስችሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን ጥቅም ላይ ሊውሉ እንደማይገባ ይደነግጋል።

ከአለባበስን ጋር በተያያዘ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት " ሃይማኖታዊ ምልክቶችን እንደ ቤተ እምነቱ አስገዳጅ ሕግጋቶች #ልዩ_ሁኔታዎች እንደሚኖሩ መደንገግ ሲገባው፣ ሙሉ ለሙሉ ከትምህርትና ሥራ ገበታ የሚያስገድዱ ድንጋጌዎችን መያዙ አግባብ አይደለም " በማለት ለሰላም ሚኒስቴር አስተያየት ፣ ቅሬታ እና የመፍትሔ ሐሳብ ልኳል።

የመንግስት ስራ ኃላፊዎችን በተመለከተ መንግሥትን ወክለው በሃይማኖት በዓላት አከባበር ላይ መገኘት እንደማይችሉ ተቀምጧል።

በየት/ቤት ፣ በመኖሪያ ቤት እና በሕክምና ማዕከላት አካባቢ የሚደረግ አምልኮ በተመለከተም ፤ በአካባቢ ጥበቃ ሕግ የተቀመጠውን የድምፅ መጠን ያከበረ መሆን አለበት ይላል።

ካልተፈቀደ በስተቀር ማስተማርን ጨምሮ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎች መፈጸም እንደማይቻልም ተቀምጧል።

የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል  ይህ በልዩ ሁኔታ በወንጌል አማኞች ላይ ጫና የሚፈጥርና ሕገ መንግሥታዊ የሆነ መሠረት የሌለው በመሆኑን መስተካከል ይኖርበታል በማለት ለሰላም ሚኒስቴር ደብዳቤ ልኳል።

#ሪፖርተርጋዜጣ

@tikvahethiopia