TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#DrTedrosAdhanom

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ቀጥ አድርጎ የሚያቆም ተዓምረኛ መፍትሄ ላይገኝ ይችላል ሲሉ አስጠንቀቅዋል።

ዶ/ር ቴድሮስ ፥ ወረርሽኙን ለመግታት የሚበጀው ሀገራትና ግለሰቦች በሙሉ ቫይረሱን ለመከላከል የሚጠቅሙ መንገዶችን ሁሉ ስራ ላይ ማዋል እንደሆነ አሳስበዋል።

የመጨረሻ ደረጃ ሙከራ ላይ ያሉ ክትባቶች አሉ ነገር ግን ምርመራ ፣ ንክኪ ያላቸው ሰዎች ፈልጎ መለየት ፣ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ ፣ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ መጠቀም እና መሰል መንገዶችን መጠቀሙ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom

ዓለም የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት ወደማግኘት እየተቃረበ ቢሆንም የኮቪድ-19 መከላከያዎችን ማላላት የለበትም ሲሉ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም አሳሰቡ።

ዶ/ር ቴድሮስ ፥ "የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) አሁንም የዛሬ 8 ወር እንደነበረው አስጊ ወረርሽኝ መሆኑን እንደቀጠለ ነው" ብለዋል።

በፓሪስ እየተካሄደ በሚገኝ የሰላም ጉባዔ ላይ "በኮቪድ-19 ታክቶን ይሆናል ነገር ግን እርሱ ገና አልሰለቸንም" ብለዋል ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም።

የአውሮፓ አገራት እየታገሉ ነው ነገር ግን ስርጭቱን ለማቆም የተወሰዱት እርምጃዎች እንዲሁም ቫይረሱ ምንም ለውጥ አላሳየም" ሲሉ ተናገረዋል።

ከሰሞኑን የተለያዩ ሀገራት ተመራማሪዎች "ውጤታማ" የሆነ ክትባት ማግኘታቸውን እየገለፁ ነው።

ዶ/ር ቴድሮስ ገና ደህንነቱ እና ውጤታማነቱ መፈተሽ ባለበት ክትባት ላይ መተማመን አደገኛ መሆኑን ገልፀዋል።

"ክትባት በፍጥነት ያስፈልጋል ፣ ነገር ግን እጃችንን አጣጥፈን ቁጭ አንልም" ብለዋል። (BBC)

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#FDREDefenseForce የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ብርሃኑ ጁላ የWHO ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም የ 'ህወሓትን ቡድን' በመደገፍ ከሰዋል። የኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገራትን ጭምር ጦርነቱን እንዲያወግዙ ሰርተዋል፤ የጦር መሳሪያዎችንም እንዲያገኙ ሰርተዋል ሲሉ ተናገረዋል። ዶ/ር ቴድሮስ እስካሁን ለቀረበባቸው ክስ ምላሽ አልሰጡም። @tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom

ዶ/ር ቴድሮስ ኣድሃኖም ዛሬ በሰጡት መግለጫ በኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ባለው ሁኔታ 'ለየትኛውም ወገን አልወገንኩም' ሲሉ አሳውቀዋል።

ከሰሞኑን እሳቸውን በሚመለከት እየወጡ ያሉ ዘገባዎችንም 'እውነት አይደሉም' ብለዋቸዋል።

እኔ የምወግነው ከአንድ ወገን ጋር ብቻ ነው እሱም ከ'ሰላም' ጋር ነው ብለዋል።

ዶክተር ቴድሮስ ኣድሃኖም በመግለጫቸው ፥ ሁሉም ወገኖች "ለሰላም እና ለሲቪሎች ደህንነት መጠበቅ" እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

* ዶ/ር ቴድሮስ የሰጡት መግለጫ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#WHO #DrTedrosAdhanom

የአስትራዜኔካ ክትባት የደም መርጋትን ስለማስከተሉ ምንም ዓይነት ማረጋገጫ ባለመኖሩ በዚህ ስጋት አገሮች ክትባቱን ከመስጠት መቆጠብ የለባቸውም ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።

በትንሹ 5 የአውሮፓ ሀገራት አይስላንድ፣ ቡልጋሪያ፣ ዴንማርክ እና ኖርዌይ ክትባቱን መስጠት አቁመዋል ፤ ይህ የሆነ አንዲት የዳኒሽ ሴት ከደም መርጋት ጋር በተገናኘ እንደሞተች ከተነገረ በኃላ ነው።

ይህንን በተመለከተ የዓለም ጤና ድርጅት በክትባቱ እና በደም መርጋት መካከል ምንም አይነት ግንኙነት የለም ብሏል።

እስካሁን ወደ 5 ሚሊዮን የሚጠጉ አውሮፓውያን የአስትራዜኔካ ክትባትን ወስደዋል።

የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ ኣድሃኖም በበኩላቸው ፥ እስካሁን በመላው ዓለም 335 ሚሊዮን በላይ የኮቪድ-19 ክትባት መሰራጨቱን የገለፁ ሲሆን እስካሁን ከክትባቱ ጋር በተገናኘ ምንም ሞት አለመመዝገቡን አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#DrTedrosAdhanom

የWHO ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የዓለምን የኮቪድ-19 ክትባት አቅርቦት ለራሳቸው ብቻ የሚሰበስቡ ሃገሮች አጥብቀው ነቅፈዋል።

ዶክተር ቴድሮስ ፥ በኒው ዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ላይ ባወጡት ጽሁፋቸው ክትባቱን ማግኘት ለሚቸግራቸው ሃገሮች ለማቅረብ በዓለም የጤና ድርጅት አሰባሳቢነት በተቋቋመው በኮቫክስ አማካይነት የሚደረገውን ጥረት “ክትባት ለራስ ሃገር ብቻ መሰብሰብ" ሲሉ በገለጹት አድራጎት ጥረቱ እየተዳከመ መሆኑን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ ጥቂት ከበርቴ ሃገሮች የሚመረቱ ክትባቶችን የበለጠ ዋጋ ለሚከፍላቸው ከሚሸጡ ኩባኒያዎች ላይ ተቀራምተው በመግዛት የሚያግበሰብሱበት ሌሎች ትርፍራፊው የሚቃርሙበት ሁኔታ እየታየ ነው ብለዋል።

አያያዘውም ወረርሽኙን ለመዋጋት መፍትሄው ቀላል ነው ፣ ያም ማካፈል ወይስ አለማካፈል ከሁለት አንዱን የመምረጥ ጉዳይ ነው ሲሉ አሳስበዋል። አስከትለውም በዚያ ደግሞ የሚፈተነው ሳይንስ ወይም የኢኮኖሚ እና የኢንዱስትሪ አቅም ሳይሆን የሚፈተነው ማንነታችን ነው" ማለታቸውን ቪኦኤ በድረገፁ አስነብቧል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom

በዓለም ዙሪያ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር በተከታታይ ለዘጠነኛ ሳምንት ፣ በበሽታው ሳቢያ ለህልፈት የተዳረጉት ሰዎች ቁጥር ደግሞ ለስድተኛ ሳምንት ማሻቀቡን መቀጠሉን የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል።

የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አደሃኖም ይህን ያሳወቁት ትናንት በአባል ሃገራቱ የመረጃ ልውውጥ ጉባኤ ላይ ነው።

ዶ/ር ቴድሮስ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ የተመዘገበው የኮሮና ቫይረስ ተያዦች ቁጥር በወረርሽኙ የመጀመሪያ 6 ወር ውስጥ ከተመዘገቡት ይበልጣል ብለዋል።

በመሆኑም ወቅቱ የቫይረሱ ስርጭት እየቀነሰላቸው ባሉትም ሃገሮች ጭምር ከመጠንቀቅ ወደኋላ የሚባልበት አይደለም ሲሉ ማሳሰባቸውን ቪኦኤ በድረ ገፁ አስነብቧል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom

በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ 'አስደንጋጭ ነው' ሲሉ የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ተናገሩ።

ዳይሬክተሩ ይህን ያሉት ትላንት ለጋዜጠኞች መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው።

ዶ/ር ቴድሮስ ትግራይ ውስጥ እያጋጠመ ያለው ሁኔታ እጅግ አስደንጋጭ ነው ፥ ሰዎች በረሃብ እየሞቱ ነው፥ የጤና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወድመዋል፤ የአስገድዶ መድፈር ተግባር ተስፋፍቷል ሲሉ ተደምጠዋል።

አክለው ፥ በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በአንድ ቃል ተጠቅሜ ልግለፀው ብል "በጣም አስደንጋጭ" ነው ብለዋል።

ዶ/ር ቴድሮስ በክልሉ ወደ 5 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች አሁን ላይ የሰብዓዊ እርዳታ በተለይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ጠቁመዋል።

በርካታ ሰዎች በረሃብ መሞት ጀምረዋል የሚሉት ዳይሬክተሩ ከባድ እንዲሁም አጣዳፊ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እየተስፋፋ ነውም ብለዋል።

በተጨማሪ በመቶ ሺህ ሰዎች ተፈናቅለዋል፤ ወደ ሱዳን ብቻ 60 ሺህ ሰዎች ከቤታቸው ተፈናቅለው ተሰደዋል ብለዋል።

የጤና ተቋማት መዘረፋቸውን እና መውደማቸውን በማንሳት አብዛኞቹ አገልግሎት የሚሰጡ አይደሉም ሲሉ አስረድተዋል።

ፆታዊ ጥቃትን በተመለከት ፥ “አስገድዶ መድፈር ተስፋፍቷል ፥ በእውነቱ በዛ ያለውን ደረጃ ያህል በየትኛውም የዓለም ዙሪያ ያለ አይመስለኝም" ሲሉም ተደምጠዋል።

በትግራይ ስላለው የCOVID-19 ሁኔታ የተጠየቁት ዶ/ር ቴድሮስ ፥ በሽታውን ለመቆጣጠር ምንም ዓይነት አገልግሎት አለመኖሩን ገልጸው ፤ ከሌሎቹ ቀውሶች አንፃር ግን ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ አይደለም ብለዋል።

@tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom #DrLiaTadesse

የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም የሀርቫርድ ቲ.ኤች.ቻን ህብረተሰብ ጤና ትምህርት ቤት የ2021 ጁሊየስ ቤንጃሚን ሪችመንድ ሽልማትን ተቀብለዋል።

ዶ/ር ቴድሮስ ፥ የዶክተር ሪችመንድን ምሳሌነት በመከተል የዓለምን ህዝብ ጤና በተለይም አቅመ ደካሞች ጤና ለማሻሻል በቻልኩት ሁሉ ለመስራት ቁርጠኛ ነኝ ብለዋል።

በሌላ በኩል ፥ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የሀርቫርድ ቲ.ኤች ቻን የህብረተሰብ ጤና ትምህርት ቤት የ2021 ኔክስት ጄኔሬሽን ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።

ዶ/ር ሊያ ለሽልማቱ የበቁት በተለይ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመቆጣጠር በወሰዷቸው ወሳኝ እርምጃዎች መሆኑ ተገልጿል።

ዶክተር ሊያ ታደሰ ፥ የሀርቫርድ ቲ.ኤች ቻን የኅብረተሰብ ጤና ትምህርት ቤት ለዚህ የከበረ ሽልማት የመረጣቸው በመሆኑ የተሰማቸውን ክብር ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የዓለም ጤና ድርጅትን እንዲመሩ በድጋሚ እጩ ሆነው ቀረቡ፡፡

ዶ/ር ቴድሮስ በራሱ በዓለም ጤና ድርጅት ቦርድ ነው በድጋሚ እጩ ሆነው የቀረቡት፡፡

ይህም በመጪው ወርሃ ግንቦት 2022 ለሚካሄደው የዋና ዳይሬከተርነት ምርጫ በብቸኛነት የቀረቡ እጩ ያደርጋቸዋል።

ዶ/ር ቴድሮስ ምርጫውን አሸንፈው ድርጅቱን በድጋሚ በዋና ዳይሬክተርነት የመምራታቸው እድል ሰፊ ስለመሆኑ ይነገራል፡፡

#AlAIN

@tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለኢትዮጵያ እጥብቅና በመቆም ሚንቀሳቀሰው የተቆርቋሪ ኢትዮጵያውያን ማህበር ፥ የዓለም ጤና ድርጅትን መርህ በመጣስ ይንቀሳቀሳሉ ባላቸው የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ላይ አቤቱታ ቀረበ።

ማህበሩ ለዓለም ጤና ድርጅት ስራ አስፈጻሚ ቦርድ የዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖምን ህገወጥ እንቅስቃሴ በተመለከተ ደብዳቤ ጽፏል።

በደብዳቤው ዳይሬክተሩ የድርጅቱን መርህ በመጣስ ከሙያ ስነ ምግባር እንዲሁም ከገለልተኝነት ውጪ እየፈጸሙት ስለሚገኘው ከስነምግባር ውጭ የሆኑ ተግባራት አስረድቷል።

ዶ/ር ቴድሮስ የሚያካሂዱትን ህገ ወጥ ተግባር የተ.መ.ድን ታማኝነት ጥያቄ ውስጥ የሚከት መሆኑን አመልክቶ በኢትዮጵያ መንግስት በአሸባሪነት የተፈረጀውን ድርጅት ሽፋን በመስጠት በሚያከናውኑት ተግባር ላይ ምርመራ እንዲደረግ አቤቱታ አቅርቧል።

#ENA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#DrTedrosAdhanom

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሓኖም የትግራይ ሰማእታት የሃዘንና የክብር ቀን ስነ-ሰርዓት በማስመልከት የማፅናኛ መልእክት አስተላለፉ።

ዶ/ር ቴድሮስ አድሓኖም በመፅናኛ መልእክታቸው " ትግራይ ፅናቱ ይስጥሽ። አይዞን " ብለዋል።
                     
@tikvahethiopia