TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ደቡብ ክልል ? በደቡብ ክልል ስር ያሉ 10 የዞን እና 6 ልዩ ወረዳ ምክር ቤቶች ክልሉን በሁለት ክላስተር ለማደራጀት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ አፅድቀዋል። እስካሁን በአዲስ ክልል ለመደራጀት ስምምነት ላይ ደርሰዋል በም/ቤቶቻቸውም አፅድቀዋል የተባሉት ፦ - የወላይታ ዞን፣ - የጋሞ ዞን፣ - የጎፋ ዞን፣ - የደቡብ ኦሞ ዞን፣ - የኮንሶ ዞን - የጌዲኦ ዞን - የአማሮ ልዩ ወረዳ፣ - የቡርጂ…
#Update

" 10 ዞኖች እና 6 ልዩ ወረዳዎች ጥያቄያቸውን አቅርበዋል "

የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት በደቡብ ክልል ያሉ 10 ዞኖችና 6 ልዩ ወረዳዎች በሁለት ክልል የመደራጀት ጥያቄአቸውን እንዳቀረቡለት ገለፀ።

ዞኖቹ እና ልዩ ወረዳዎቹ በክልል የመደራጀት ጥያቄአቸውን ለፌደሬሽን ምክር ቤት ያቀረቡት ዛሬ መሆኑ ተገልጿል።

የፌደሬሽን ም/ ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር ጥያቄውን መቀበላቸውም ተነግሯል።

ም/ቤቱ ውሳኔውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ያሳውቃል ብለዋል።

በአንድ ላይ በክልልነት እንደራጅ ብለው ጥያቄያቸውን ያቀረቡት 10 ዞኖች እና 6ቱ ልዩ ወረዳዎች እነማን ናቸው ?

- ወላይታ፣
- ጋሞ፣
- ጎፋ፣
- ኮንሶ፣
- ደቡብ ኦሞ፣
- ጌዴኦ ዞኖች
- ደራሼ፣
- ባስኬቶ፣
- ኧሌ፣
- አማሮ እና ቡርጂ ልዩ ወረዳዎች በአንድ ላይ በክልል እንደራጃለን በማለት በየምክር ቤቶቻቸው በማጽደቅ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጥያቄያቸውን አቅርበዋል።

በሌላ በኩል ፦

- ስልጤ ፣
- ከምባታ ጠምባሮ፣
- ሀዲያ ፣
- ሀላባ ዞኖች
- የም ልዩ ወረዳ በአንድ ላይ በመሆን አንድ ክልል ለመመስረት በምክር ቤቶቻቸው አፅድቀው ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጥያቄያቸውን አቅርበዋል።

@tikvahethiopia
#ተመዝገቡ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የሃይማኖት የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን በመመዝገብ ላይ ይገኛል።

የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ፤ የሃይማኖት ድርጅቶች አስተምህሮታቸውን በመገናኛ ብዙኃን እንዲያደርሱ የብሮድካስት አገልግሎት ፈቃድ ማግኘት እንዳለባቸው ይደነግጋል፡፡

በዚህም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ከሰኔ 27/ 2014 ዓ.ም ጀምሮ የሃይማኖት የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን በመመዝገብ ላይ እንደሚገኝ አሳውቋል።

ማንኛውም የሃይማኖት የቴሌቪዥን ጣቢያ እስከ #ነሐሴ_13_ቀን_2014 ዓ.ም ድረስ https://www.eservices.gov.et/ በሚለው ፖርታል ውስጥ በመግባት ወይም #በአካል_በመቅረብ ማመልከትና ፈቃድ መውስድ እንዳለበት ባለሥልጣኑ አሳስቧል።

Via @EthMediaAuth
#አሜሪካ #ቪዛ

" አንዳንድ ተጓዦች የቪዛ ቃለመጠይቅ ቀጠሮ ለማግኘት ከ6 ወር እስከ አንድ ዓመት ድረስ ይፈጅባቸዋል "

ለጉብኝት ፣ ለሥራ ወይም ለመኖር ወደ አሜሪካ ለመጓዝ ቪዛ የሚጠይቁ አመልካቾች ከ1994ቱ የሽብር ጥቃት ወዲህ " እጅግ የተራዘመ " ቀጠሮ እንደሚሰጣቸው ተሰምቷል።

ይህ የተሰማው ሰሞኑን ከወጡ የሃገሪቱ የውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤት መረጃዎች እንደሆነ የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ዘግቧል።

አንዳንድ ዓለምአቀፍ ተጓዦች የቪዛ ቃለ መጠይቅ ቀጠሮ ለማግኘት ከስድስት ወር እስከ አንድ ዓመት እንደሚፈጅባቸው ተናግረዋል።

በካቶ ኢንስቲትዩት የስደተኞች ፖሊሲ ኃላፊ ዴቪድ ቤየር ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል፤ " በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የአሜሪካ ኤምባሲዎች ለ2 ዓመታት መዘጋታቸውና ቪዛ ‘መስጠት ማቆማቸው የፈጠረው ችግር ነው’ " ብለዋል።

“ በወረርሽኙ ምክንያት የተከማቸ ሥራ አለ፤ ከአንድ ዓመት በላይ ቀጠሮ ያስፈለገውም ለዚሁ ነው ” ሲሉ አክለዋል።

የቀጠሮ ርዝመት ከኤምባሲ ኤምባሲ ቢለያይም ‘አሁን ያለው ሁኔታ ግን ከ1994ቱ የሽብር ጥቃት ወዲህ የከፋ ነው’ ሲሉ ቤየር ገልፀዋል።

ከጥቃቱ ሁለት ዓመታት በኋላ ጉዳይ ለማስፈፀም የሚወስደው ጊዜ ሦስት ሳምንት ያህል እንደነበር አንድ የውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ኃላፊ በወቅቱ ለአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ተናግረው ነበር።

የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ሠንጠረዥ እንደሚያሳየው ለአንዳንድ ቪዛ አመልካቾች ቃለ መጠይቅ ለማደረግ ከ1 ዓመት በላይ ሲወስድ የንግድና የጉብኝት ቪዛ አመልካቾች ደግሞ ከ6 ወራት በላይ እንደሚጠብቁ ተገልጿል።

አሜሪካ ለ40 ሃገሮች ተጓዦች ያለ ቪዛ ገብተው ለዘጠና ቀናት እንዲቆዩ እንደምትፈቅድ የአሜሪካ ሬድዮ ጣቢያ መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሽልማት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሽልማት (በካቢኔ ውሳኔ) ፦ 🇪🇹 ለመላው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን 10 ሚሊዮን ብር 🇪🇹 የወርቅ ቅብ ሰሃን " እናመሰግናለን " የሚል ለኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ 🇪🇹 አትሌት ዳዊት ስዩም 250 ካሬሜትር መሬት 🇪🇹 አትሌት መቅደስ አበበ 250 ካሬሜትር መሬት 🇪🇹 አትሌት ወርቅውሃ ጌታቸው 350 ካሬሜትር መሬት 🇪🇹 አትሌት ለሜቻ ግርማ 350…
#ሽልማት

በ18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበው የአትሌቲክስ ቡድን አባላት የማበረታቻ ሽልማት ተበረከተ።

የዛሬው የማበረታቻ ሽልማት የተበረከተው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ባዘጋጀው የምስጋናና የማበረታቻ ሽልማት መርሀግብር ላይ ነው።

በዚህም መሰረት ፦

🥇 የወርቅ ሜዳሊያ ላስገኙ አራቱ አትሌቶች (ለተሰንበት ግደይ፣ ታምራት ቶላ፣ ጎተይቶም ገብረስላሴ፣ ጉዳፍ ፀጋይ) ለእያንዳንዳቸው የ60 ሺህ ብር የገንዘብ ስጦታ ፤

🥈 የብር ሜዳሊያ ላስገኙት አራት አትሌቶች (የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘችውን ጉዳፍ ፀጋይን ጨምሮ) ለእያንዳንዳቸው የ40 ሺህ ብር ስጦታ ፤

🥉የነሀስ ሜዳሊያ ላስገኙት ኹለት አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ30 ሺህ ብር ስጦታ ፤

➡️ ዲፕሎማ ላገኙ 10 አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ10 ሺህ ብር ስጦታና ለተሳተፉ 16 አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ7 ሺህ ብር የገንዘብ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ የፌደሬሽኑ አመራሮች፣ አሠልጣኞች እና የአትሌቲክስ ልዑካን ቡድኑ መሪዎች በየደረጃቸው የተለያዩ የገንዘብ ስጦታዎች ተበርክቶላቸዋል።

Credit : Addis Maleda Newspaper

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አኔት ዌበር ፣ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር ፣ የተመድ ተወካዮች ፣ የሀገራት አምባሳደሮች ከትግራይ ክልል ለፌዴራል መንግስት ደብዳቤ ይዘው ተመልሰዋል። ከዚህ ቀደም መልዕክተኞቹ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ባደረጉት ውይይት በትግራይ የመብራት፣ የቴሌኮም፣ የባንክ እና ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን #በፍጥነት ወደነበረበት…
#GoE

የጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ መልዕክተኞች እና አምባሳደሮች የመቐለ ቆይታን በተመለከተ ጉዳዩን የያዙበት መንገድ በመንግስት ላይ ቅሬታ እንደፈጠረበት ገልፀዋል።

አምባሳደሩ፤ ልዩ መልዕክተኞቹ እና አምባሳደሮቹ ለሰላም ንግግር ጥረት ማድረግ ሲገባቸው በሌላ ወገን የተቀመጠ ቅድመ ሁኔታ ማሟላት ላይ ተጠምደዋል ብለዋል።

" ተቋርጠው የሚገኙ መሠረታዊ አገልግሎቶች በተመለከተ የመንግሥት አቋም ግልጽ ነው ፤ አገልግሎት ማስጀመር የሚቻልባቸው ሁኔታ መፍጠር እና የሰላም ንግግር መጀመር ቀዳሚ መሆን አለበት " ሲሉ ገልፀዋል።

" ልዩ መልዕክተኞቹ እና አምባሳደሮቹ ከመቐለ ጉዟቸው በኋላ ባወጡት መግለጫ አሁንም ' ያልተገደብ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ' የሚል ትርክት እንደቀጠለ ነው " ያሉት አምባሳደሩ " አሁን ላይ ወደ ክልሉ ያልተገደብ በረራ እና የጭነት መኪኖች ጉዞ እየተደረገ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

የነዳጅ ጉዳይም መፍትሄ እንደተሰጠውና በሁሉም አድናቆት የተቸረው ጉዳይ ነው ብለዋል።

የሰላም ንግግሩን በተመለከተም ፤ " የሚመራው የአፍሪካ ኅብረት ብቻ ነው " ሲሉ አስረግጠው ፅፈዋል።

ከዚህ ቀደም የፌደራል መንግሥት ከህወሓት ጋር የሚደረገውን ንግግር መምራት ያለበት የአፍሪካ ኅብረት እንዲሆን ፍላጎት እንዳለው ገልጾ ነበር።

ትግራይ ክልልን እያስተዳደረ ያለው " ህወሓት " ደግሞ ድርድሩ በበላይነት የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እንዲመሩ ጠይቆ ነበር።

ማክሰኞ ትግራይ ክልል መቐለ የተጓዙት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ መልዕክተኞች ደግሞ በአፍሪካ ህብረት መሪነት የሚካሄደውን ንግግር ለመደገፍ ዝግጁ ነን ማለታቸውን ቢቢሲ ፅፏል።

ማስታወሻ t.me/tikvahethiopia/72609?single

@tikvahethiopia
ይህ ተጠቀሙ !

@officialtikvahethiopiaBot

ውድ ቤተሰቦቻችን ይህ ከማንኛውም የጥላቻ አመለካከት ፣ ከአድሏዊነት ፣ ከአግላይነት ፣ ከወገንተኝነት የራቀው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ቦታ ነው።

እንደሚታወቀው በዚህ ቤተሰብ ከተሰባሰብን አመታት ተቆጥረዋል።

ትልቁ የመሰባሰባችን ምክንያት እርስ በእርስ የምናውቀውን ፣ የሰማነውን ፣ ያየነውን ፣ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ያገኘነውን መረጃ፣ ጥቆማ እንድንለዋወጥ፣ ለሀገር ይሆናል ብለን የምናስበውን እንድናጋራ፣ እርስ በእርስ እንድንተጋገዝ ፣ ለሀገር በጎ አስተዋጽዖ ለማበርከት ብቻ ነው።

እርስ በእስር መረጃ ተለዋውጠን ለብዙሃኑ አባላት በይፋ የምናደርስበት መንገድ ደግሞ በውስጥ መስመር በምንላላካቸው መልዕክቶች መሆኑ ይታወቃል እስከዛሬ ስራ ላይ የነበረው @tikvahethiopiaBot ካለፉት ጥቂት ወራት አንስቶ የቴክኒክ መደነቃቀፍ ገጥሞታል በዚህም በትክክል መልዕክቶችን ለመቀበል አልተቻለም።

@tikvahethiopiaBot ተስተካክሎ ሁሉንም መልዕክቶችን መቀበል እስኪቻል ድረስ @officialTikvahethiopiaBot እንድትጠቀሙ ይሁን።

ከካለፉት ሳምንታት ወዲህ መልዕክቶችን ልካችሁ ፣ አስፈላጊውን ጥቆማ እንዲደርስ ብላችሁ በ @tikvahethiopia / @tikvahethmagazine ያልቀረበለችሁ ቤተሰቦቻችን መልዕክታችሁን በ @officialtikvahethiopiaBot በድጋሚ ላኩልን።

NB : መልዕክቶች በውስጥ እንዲያልፉ የተደረገው የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትን ስብሰብ ዓላማ ያልተረዱና ሆን ብለው ሰዎችን ለመዝለፍ፣ ጥላቻ እንዲያድርባቸው ለማድረግ፣ የራሳቸውን መጥፎ አመለካከት ለማስረፅ የሚመጡትን ለይቶ ለማውጣትና ለመቀነስ ነው።

@tikvahethiopia
#ጾመ_ፍልሰታ

የ2014 ዓ.ም ጾመ ፍልሰታን በተመለከተ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖትከዋሽንግተን ዲሲ፤ ሰሜን አሜሪካ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦

" ሁላችንም እንደምንገነዘበው በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት ፍጹም ሰላም ያላት ሀገር እንድትኖረው ነው፤ ይህ ትክክለኛ ፍላጎት ነው፡፡ ይሁንና ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ ሁሉም ነገር ስለማይሆን ፍጹም ሰላም በሀገር ሰፍኖ ሕዝባችን እግዚአብሔር በሰጠው ምድር በፍቅር፣ በአንድነት በነጻነትና በእኩልነት እንዲኖር ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ሁሉ በዚህ ወቅት የቅድስት ድንግል ማርያምን ጸሎትና ስእለት ተማኅፅኖና አስተበቊዖት አጋዥ አድርገን በልዩ ሱባዔ ወደ እግዚአብሔር በመቅረብ በንሥሐ፣ በጾም፣ በጸሎት፣ ነዳያንን በመርዳትና ቅዱስ ቊርባንን በመቀበል እሱን መማፀን ይኖርብናል፡፡

... በሀገራችን የተከሠቱት ያላስፈላጊ ግጭቶችን በድርድር ለመፍታት እየተሞከሩ ያሉ አንዳንድ የሰላምና የውይይት ድምፆች ተስፋ ሰጪ ስለሆኑ ሥር ሰደው፣ በተግባር ተተርጉመው፣ ለተጐዳው ሕዝባችን መጠገኛ ይሆኑ ዘንድ፣ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ሁሉ በዚህ ዙርያ በሱባዔው ወቅት ወደ እግዚአብሔር አቤት በማለትና ሂደቱን በመደገፍ የበኩላቸውን ጥረት እንዲያደርጉ፣ መንግሥትም ሆነ የዓለም አቀፉ ማኅበረ ሰብ በዚህ በጎ ሐሳብ እንዲገፉበትና ሕዝባችንንና ሀገራችንን ከጥፋት እንዲታደጉ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ጾሙን የሰላም፣ የሥርየት፣የፍቅር፣ የአንድነት ጾም ያድርግልን።

ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን "

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ጾመ_ፍልሰታ

ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነየሱስ ሊቀጳጳሳት ዘካቶለካውያን የ2014 ዓ.ም የፍልሰታ ፆም መግቢያን አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦

" ይህንን የፍልሠታ ጾም ስንጾም እና ሱባኤ ስንገባ ምንም እንኳን ዛሬም ቢሆን በብዙ ጨለማ ተከብበን የዲያብሎስን ውጊያ እየተጋፈጥንም ቢሆን እንደ ክርስቲያንነታችን በጽኑ እምነት እና ተስፋ ተሞልተን ነው። ምክንያቱም ምንም ያኽል ቢጨላልም ንጋት አይቀርምና። ሞት የመጨረሻ ቃል የለውምና። ትንሣኤ መሆኑ አይቀርምና።

ስለሆነም እያንዳንዳችን በልባችን በዚህ በጾም ወቅት ከእኔ በላይ የተቸገረ የሚሰቃይ፣ የተፈናቀለ፣ የተሰደድ፣ በጦርነት አውድ ዘወትር በስጋት እና ጭንቀት የሚኖር አለ በማለት የወንድማዊ የርህራሄ ፣ የአለኝታነት እና የቅርበት መንፈስ እየተሰማን ሊሆን ይገባል።

እነዚህንም የጾምና የሱባኤ ቀናት በተጋድሎም በማሳለፍ ለበዓለ ፍልሰታዋ በሰላም ለመድረስ ያብቃን። አምላክ የተቀደሰ የተባረከ ጾመ ፍልሰታ ለመላው ካቶሊካውያን እና በጎ ፈቃድ ላላቸው ሁሉ ያድርግልን እያልኩ የደስታ ምንጭ የሆነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለእኛ ለልጆቿ እና ለሀገራችን ለኢትዮጵያ ትለምንልን፡፡ አሜን!

ቸሩ አምላካችን በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ኢትዮጵያን ይባርካት፡፡ "

ካርዲናል ብርሃነየሱስ ሊቀ ጳጳሳት ዘካቶሊካዊያን የኢትዮጵያ ካቶሊካውያን ጳጳሳት ጉባኤ ፕረዝደንት

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ICRC

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፤ ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሰዎች አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ማግኘት ህይወታቸውን እንደሚታደግ ገልጾ ፦ በሐይቅ፣ ደሴ፣ ወልድያ፣ መርሳ፣ ኮምቦልቻ፣ አይደር፣ ማይጨው፣ ዓዲግራት፣ መሆኒ፣ ሽሬ፣ ኣክሱም፣ ላሊበላ፣ ሰቆጣ፣ ዋድላ፣ ባህር ዳር፣ ደባርቅ፣ ጎንደር፣ ነቀምት፣ ጊምቢ እና ደምቢዶሎ ሆስፒታሎች ያሉትን የአንድ መስኮት የአገልግሎት ማዕከላትን በመደገፍ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።

በሌላ በኩል ኮሚቴው በጤና ድንገተኛ አደጋዎች ፈጣን እና ውጤታማ የሆነ ምላሽ ለመስጠት ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ጋር በቅርበት በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጾ ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ለሚገኙ 14 የክልል እና ዞን የኢቀመማ ቅርንጫፎች የመጀመሪያ እርዳታ መስጫ መሳሪያዎችን እና የአምቡላንስ አቅርቦቶችን ድጋፍ ማድረጉ አሳውቋል።

ከዚህም በተጨማሪ ፤ ጦርነት በተካሄደባቸው አካባቢዎች #ተቀብረው_ሳይፈነዱ_የሚቀሩ ፈንጂዎች በሰዎች አካል ላይ የሚያደርሱት ጉዳት ከፍተኛ እንደሆነ የሚገልፀው የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ተጎጂዎችን ለመርዳት በኢትዮጵያ ውስጥ በባህር ዳር፣ ደሴ፣ አሶሳ፣ አሰላ፣ ነቀምት፣ አርባምንጭ፣ መናገሻ፣ ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ፣ መቐለ እና ኪዩር ሆስፒታል የአካል ማገገሚያ ማዕከላትን በማጠናከር ላይ እንደሆነ ገልጿል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia