TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Amnesty International & HRW .pdf
#GoE

የኢትዮጵያ መንግስት አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና ሂዩማን ራይትስ ዎች በጣምራ ባወጡት ሪፖርት ዙሪያ ምላሽ ሰጥቷል።

መንግስት በወልቃይት ላይ ትኩረቱን ያደረገውን ሪፖርት ይዘት በጥንቃቄ እየመረመረ እንደሚገኝ ገልጿል።

ሪፖርቱ በሰብአዊ መብት ላይ የሚነሱ ከባድ ጥሰቶች ከሚባሉት በተጨማሪ በሀገሪቱ ውስጥ የተከሰቱትንና በጥንቃቄ መታየት የሚገባቸውን የፖለቲካ ለውጦች፣ ሰላምና ደህንነት፣ የውስጥ ወሰን ጉዳዮችን ያካተተ መሆኑንም መገንዘብ ያስፈልጋል ብሏል።

የዘር ማጽዳት፣ የጦር ወንጀል እና በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ክስንም ያቀረበ ሪፖርት መሆኑን ገልጿል።

የሰብአዊ መብት ጥሰት የፈፀሙትን ሁሉ ተጠያቂ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን የገለፀው መንግስት ለዚህም ነው የኢሰመኮ እና የተመድ የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ፅ/ ቤት የጋራ ምርመራ ዉጤቶችን ተከትሎ መንግስት የሚኒስትሮች ግብረ ሃይል ማቋቋሙን አስታውሷል።

ግብረሃይሉ ዛሬ ሁለተኛ ስብሰባ አካሂዶ የምርመራ ሂደቱን ለማፋጠን የተለያዩ መመሪያዎችን አውጥቷል፤ ለአሁኑ ሪፖርትም ተገቢውን ትኩረት በመስጠት በቅርበት ይመረምራል ሲል አስረድቷል።

መንግስት ሁለቱ ተቋማት ጉዳዪን ለመመርመር የተጠቀሟቸውን በርካታ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ትክክለኛነት ላይ ጥያቄ ማቅረቡን ገልጿል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/GoE-04-06

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አኔት ዌበር ፣ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር ፣ የተመድ ተወካዮች ፣ የሀገራት አምባሳደሮች ከትግራይ ክልል ለፌዴራል መንግስት ደብዳቤ ይዘው ተመልሰዋል። ከዚህ ቀደም መልዕክተኞቹ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ባደረጉት ውይይት በትግራይ የመብራት፣ የቴሌኮም፣ የባንክ እና ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን #በፍጥነት ወደነበረበት…
#GoE

የጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ መልዕክተኞች እና አምባሳደሮች የመቐለ ቆይታን በተመለከተ ጉዳዩን የያዙበት መንገድ በመንግስት ላይ ቅሬታ እንደፈጠረበት ገልፀዋል።

አምባሳደሩ፤ ልዩ መልዕክተኞቹ እና አምባሳደሮቹ ለሰላም ንግግር ጥረት ማድረግ ሲገባቸው በሌላ ወገን የተቀመጠ ቅድመ ሁኔታ ማሟላት ላይ ተጠምደዋል ብለዋል።

" ተቋርጠው የሚገኙ መሠረታዊ አገልግሎቶች በተመለከተ የመንግሥት አቋም ግልጽ ነው ፤ አገልግሎት ማስጀመር የሚቻልባቸው ሁኔታ መፍጠር እና የሰላም ንግግር መጀመር ቀዳሚ መሆን አለበት " ሲሉ ገልፀዋል።

" ልዩ መልዕክተኞቹ እና አምባሳደሮቹ ከመቐለ ጉዟቸው በኋላ ባወጡት መግለጫ አሁንም ' ያልተገደብ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ' የሚል ትርክት እንደቀጠለ ነው " ያሉት አምባሳደሩ " አሁን ላይ ወደ ክልሉ ያልተገደብ በረራ እና የጭነት መኪኖች ጉዞ እየተደረገ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

የነዳጅ ጉዳይም መፍትሄ እንደተሰጠውና በሁሉም አድናቆት የተቸረው ጉዳይ ነው ብለዋል።

የሰላም ንግግሩን በተመለከተም ፤ " የሚመራው የአፍሪካ ኅብረት ብቻ ነው " ሲሉ አስረግጠው ፅፈዋል።

ከዚህ ቀደም የፌደራል መንግሥት ከህወሓት ጋር የሚደረገውን ንግግር መምራት ያለበት የአፍሪካ ኅብረት እንዲሆን ፍላጎት እንዳለው ገልጾ ነበር።

ትግራይ ክልልን እያስተዳደረ ያለው " ህወሓት " ደግሞ ድርድሩ በበላይነት የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እንዲመሩ ጠይቆ ነበር።

ማክሰኞ ትግራይ ክልል መቐለ የተጓዙት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ መልዕክተኞች ደግሞ በአፍሪካ ህብረት መሪነት የሚካሄደውን ንግግር ለመደገፍ ዝግጁ ነን ማለታቸውን ቢቢሲ ፅፏል።

ማስታወሻ t.me/tikvahethiopia/72609?single

@tikvahethiopia
#GoE

የፌዴራል መንግስት በቅርቡ ወደ ትግራይ ፣ መቐለ ተጉዞ የነበረው የዲፕሎማቶች የልዑካን ቡድን " የህወሃትን የውሽት ትርክት አስተጋብቷል፤ ይህም ስህተት ነው " ብሏል።

ዛሬ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በመግለጫቸው ላይ መንግሰት በራሱ ተነሳሽነት የተኩስ አቁም ስምምንት ለማድርግ ወሰኖ እንደነበር እና አሁንም #ለሰላም ውይይት ፍላጎት እንዳለው ገልፀዋል።

በአሁን ሰዓት ለትግራይ ክልል ሰብዓዊ እርዳታ የሚውል የምግብ ድጋፍ በአየር እና በየብስ ትራንስፖርት ተደራሽ እየተደረገ ነው ያሉት ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ ፤ " መንግስት ወደ ትግራይ የሚገቡ የሰብዓዊ ድጋፍ ባላቋረጠበት እና ክልከላዎች ባላደረገበት ወደ መቐለ ተጉዞ የነበረው የአሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት ልዩ መልዕክተኞችን የያዘው የዲፕልማቶች ቡድን የህወሓት የውሽት ትርክት ማስተጋባቱ ስህተት ነው " ብለዋል።

መንግስት በ #አፍሪካ_ህብረት በኩል የሚካሄደው የሰላም ውይይት ሁሌም በማንኛውም ቦታ እና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲካሄድ መንግስት ዝግጁ መሆኑን በተደጋጋሚ አረጋግጧል ያሉት ወ/ሮ ሰላማዊት በህወሃት በኩል ከሰላም ድርድር ፍላጎት ይልቅ አሁንም የጦርነት ጉሰማዎችና ለሰላም ውይይት እንቅፋት የሚሆኑ ንግግሮች እየተሰሙ ነው ማለታቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA ለሰሜን ኢትዮጵያ ችግር ሰላማዊ የሆነ መፍትሄ ለመፈለግ እና ችግሩን በሰላማዊ ድርድር ለመቋጨት በፌዴራሉ መንግስት የተቋቋመው " የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴ " ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር። በመግለጫው ላይ ከተጠቀሱ #ወሳኝ ነጥቦች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል ፦ • ኮሚቴው ባደረገው ውይይት የትግራይ፣ የአፋር፣ የአማራ ክልል አካባቢዎች ነዋሪ የሆኑ ዜጎች በእለት ተእለት ኑሮዋችው ላይ…
#GoE

የጠቅላይ ሚኒስትር ፕሬስ ሴክሬተሪያት ቢልለኔ ስዩም ዛሬ በሰጡት መግለጫ የተለያዩ ጉዳዮችን አስንተዋል።

ከካነሷቸው ጉዳዮች አንዱ በሰላም አመራጭ ኮሚቴ በኩል ስለ ተዘጋጀው የሰላም ረቂቅ ሰነድ ነው።

በዚህም የሰላም ረቂቅ ሰነዱ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ለተከሰተው ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ ለመስጠት፤ በመጪዎቹ ሳምንታት የተኩስ አቁም እንዲደረስ፣ የሰላም ውይይት እንዲሁም ሌሎች በእንጥልጥል የቀሩ ጉዳዮች ደግሞ በብሄራዊ ምክክሩ እንዲዳሰሱ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።

ሰነዱ መንግስት ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ በሚፈታበት ሁኔታ ላይ እያደረገ ያለውን ከፍተኛ ጥረት አመላካች ነው ሲሉ ገልፀዋል።

በሌላ በኩል በትግራይ ክልል መላሶ ግንባታ እና መሰረታዊ ድጋፎች ላይ መንግስት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

መንግስት ባለሙያ በመላክም ሆነ እዛው ያለውን የሰው ኃይል በመጠቀም በክልሉ መሰረታዊ የህዝብ አገልግሎት ለመመለስ ፍላጎት እንዳለውና ለዚህም ደግሞ አንዳንድ በመሬት ላይ ያሉ ሁኔታዎች እንዲሻሻሉ እንደሚፈልግ ገልፀዋል፡፡

መንግስት በአፍሪካ ህብረት መሪነት በማንኛውም ጊዜና ቦታ የሰላም ድርድር ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።

ቢልለኔ በዛሬው መግለጫቸው ከአማራ ክልል ወደ አ/አ በሚደረገው ጉዞ ተጓዦች ላይ ስለሚደርስ እንግልት ተጠይቀው መልሰዋል።

በዚህም፤ "ህወሃት በአንዳንድ የአማራ ክልል አካባቢዎች ወረራ በፈፀመበት ወቅት የዘረፋቸውን የመንግስት ማህተሞች በመጠቀም ሀሰተኛ መታወቂያ በማሳተም ለእኩይ ተግባሩ እያዋለ በመሆኑ ይህንን ድርጊቱን ለመግታትና ተከታትሎ ለመያዝ በተወሰደ እርምጃ የተፈጠረ ነው" ብለዋል።

አሁን ላይ ግን የትራንስፖርት አገልግሎቱ ወደ ቀድሞ ሁኔታው መመለሱን ለጋዜጠኞች መናገራቸውን ከኤፍ ቢ ሲ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#GoE

የኢትዮጵያ መንግስት፤ የኢትዮጵያ ወዳጆች ወይም " የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ፣ የግዛት አንድነት እና ህገመንግስት እናከብራለን " የሚሉ ወገኖች ከሰላም ንግግሩ ጋር በተያያዘ የቃላት አጠቃቀም ላይ ጥንቃቄ እንዲደረጉ አሳሰበ።

ፌዴራል መንግስት ማሳሰቢያውን ያወጣው በስሩ ባለው የ " ወቅታዊ ሁኔታዎች መረጃ ማጣሪያ " በኩል ነው።

የመረጃ ማጣሪያው እንደ " የትግራይ መንግስት (Government of / state of Tigray " ወይም ፣ " የትግራይ የውጭ አገልግሎት / Tigray External Service " የመሳሰሉ አገላለጾች ተራ ስህተቶች ሳይሆኑ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ የሚጥሉ በመሆናቸው ሊፈተሹ ይገባል ብሏል።

የኢትዮጵያ ወዳጆች ወይም " የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት፣ የግዛት አንድነትና ሕገ መንግሥት  እናከብራለን " የሚሉ ወገኖች ሁሉ በኢትዮጵያ ሰሜናዊ ክፍል የተፈጠረውን ግጭት ለመፍታት በቅርቡ በሚደረገው የሰላም ንግግር ሕገ-ወጥ ቃላትን / አገላለፅን ከመጠቀም ይቆጠቡ ሲል አስገንዝቧል።

" ከዚህ የሰላም ንግግር አንፃር ወዳጆቻችን እና አጋሮቻችን ማስታወስ ያለባቸው ሁለቱ ወገኖች በመሰረታዊነት ልዩነት ያላቸው መሆኑን ነው " ያለው ይኸው የመረጃ ማጣሪያ ፤ " አንዱ በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ፣ ህጋዊ መንግስት እና ሌላኛው ' ህወሓት ' የታጠቀ ቡድን ነው " ብሏል።

እንደዚሁም እንደ " የትግራይ አስተዳደር / Tigray Administration " ወይም " የትግራይ ክልል መንግስት / Regional Government of Tigray " የመሳሰሉ አገላለፆችም ተቀባይነት የላቸውም ሲል አሳውቋል።

ምክንያት ያለውም ፤ " በትግራይ ክልል ውስጥ በኢትዮጵያ ህገ መንግስት መሰረት የተመረጠ አካል ስለሌለ ነው " ሲል አስረድቷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Peace #GoE #OLA

በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (OLA መካከል ከዚህ ቀደም ታንዛኒያ ላይ ሁለት ጊዜ የሰላም ድርድር ተደርጎ ያለ ስምምነት / ወጤት መበተኑ ይታወሳል።

አሁንም ሌላ #ሶስተኛ_ዙር የሰላም ውይይት/ድርድር ሊኖር የሚችልበት ዕድል መኖሩን የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናግረዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ምን አሉ ?

- የመጀመሪያው ንግግር በጣም ጥሩ ርቀት ሄዶ ነበር ፤ በዚህም ብዙ መካሰስ ቀርቶ ለሚቀጥለው ዙር ለመነጋገር እናመቻች በሚል ነው የተጠናቀቀው።

- ሁለተኛው የሰላም ድርድር መጀመሪያ ላይ ከሁለቱም ወገን አግባቢዎች ሄደው ከሳምንት በላይ ፈጅተዋል። አዝማሚያው ጥሩ ነበር።  መጨረሻ የማያግባቡ ነጥቦች መጡ። በዚህም ትንሽ የተሻለ ኃይል ያለው ሰው ይምጣ ተብሎ ከመንግሥትም ከነሱም ሄዷል። በዚህም ጊዜ ጥሩ ሂደት ነበር።

- በህገ-መንግስት ጥላ ስር "የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ፣ አንድነት መቀበል ላይ ፤ የኢትዮጵያን ሀገረ መንግስት በምርጫ የመጣ Legitimacy ያለው መሆኑ ላይ መግባባት ተደርሶ ነበር። ወደ ዝርዝር ሲመጣ ግን እነዚህን መግባባቶች የሚሸረሽር ነገር ነው የመጣው።

- ስምምነቱ በመጨረሻ ለህዝብ ይፋ የሚሆን ደረጃ / ወደ ሰነድ ደረጃ ሲደርስ ያልተጠበቁ ጥያቄዎች ተነስትዋል።

ምንድናቸው ?

* አንደኛው --- ' #ስልጣን_አካፍሉኝ ' ነው እያንዳንዱን ጠብመንጃ የያዘ፣ ጫካ የገባ ሁሉ ስልጣን ለማግኘት ከሆነ የሚደራደረው ይሄ ለሀገር ሰላም አይሰጥም።

ጫካ እየገቡ ፣ ግጭት የፈጠሩ ፣ ህዝቡን እያበሳሰቡ ከዛ እንነጋገር እያሉ " እሺ " ሲባል ስልጣን አካፍሉኝ የሚባል ነገር ካለ መቼም ስርዓት አይመጣም። ሀገር ሰላም አይሆንም።

ምሳሌ ብንወድስ ፦ ከአማራ፣  ከቤንሻንጉል ጉምዝም ከሌላውም የታጣቁ ኃይሎች ስልጣን አካፍሉኝ ካሉ ስንት የታጠቀ ኃይል ስልጣን ሲካፈል ይኖራል ? ይሄ ኢትዮጵያን ይጎዳል።

እንዲህ አይነት ጥያቄ ነው ይዘው የቀረቡት (OLAን ማለታቸው ነው)።

መንግሥት ስልጣን ላካልፍ ቢልም ፍፁም አይችልም ፤ መብትም የለውም። #ማሳተፍ ግን ይችላል። ሸኔን ጭምር ማሳተፍ ይችላል።

ዋናው መሰረታዊ ልዩነት ይሄ ነው። ስልጣን አካፍሉኝ ስሉም እራሳቸው ፕሮፖዛል አስቀምጠው ፤ እዚህ ላይ ስልጣን ስጡኝ የሚል ነበር።

* ሁለተኛው --- ወደ ' DDR ' አልገባም ነው።

በሰላም ለመታገል ፣ ፓርቲ አቋቁሞ ለመታገል ፣ ወደ ህዝብ ምርጫ ለመቅረብ የገጠር ትጥቅ ትግል ትቶ በሰላም ወደ ህዝብ መመለስ ነው። ለዚህ ደግሞ ትጥቅ መፍታት አለባቸው።

DDR / Disarm, Demobilized , Reintegrate መሆን አለባቸው። ይሄ ዓለም የሚሰራበት ነው። ማንኛውም ግጭት የተፈታውም በዚህ ነው። ይሄን ለመቀበል የመቸገር ነገር ተከስቷል።

ትጥቅ ሳይፈታ ፦
° እንዴት እንደራደራለን?
° እንዴት Demobilize ይሆናሉ?
° እንዴት ወደ ህብረተሰቡ ይቀላቀላሉ ?

መንግስት በግልፅ DDR ፕሮግራም ውስጥ መግባት አለብን ብሏል። በአንድ ሀገር በፍፁም ሁለት የታጠቀ ኃይል ሊኖር አይችልም። ትጥቅ የመያዝ መብት ያለው መንግስት ብቻ ነው።

ይሄንን #መቀበል_ነበረባቸው። በዓለም ላይ ይሄን ሳይቀበሉ ስምምነት የለም። ድርድር ብሎ ነገር የለም።

ንግግሩ ጥሩ ሄዱ ከላይ ባሉት ሁለት ምክንያት ነው መጨረሻ ላይ የቆመው።

- ሶስተኛ ዕድል ይኖራል ? እኔ የሚኖር ይመስለኛል።

- ሁለቱን #ያልተስማማንባቸው_ነጥቦችን በተሳሳተ መንገድ እንዲወስዱ በማድረግ ሌሎች ኃይሎች እጅ አላቸው። OLA ላይ ታዝሎ የሚሄዱ ኃይሎች አሉ። ከሀገር ውስጥም ከሀገ ውጭም አሉ። ባዕዳንም ዜጎችም እነዚህ ኃይሎች OLA በሰከነ መንገድ አይቶ ስምምነቱን እንዳይቀበል አድርገውታል። OLA ሌላ መስማት አልነበረባቸውም፤ ችግር ውስጥ ያሉት እራሳቸው ስለሆኑ እራሳቸው መወሰን ነበረባቸው።

(ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ እነዚ ኃይሎች እነማን እንደሆኑ በግልፅ አልተናገሩም)

- ሌላው ኃይል ጣልቃ ስለገባ በዓለም experience ታይቶ የማይታወቅ ቅድመ ሁኔታ በማቅረብ መንግሥትን አስቸግረዋል (OLA ማለታቸው ነው)።

- ሶስተኛ ዕድል ሊኖር ይችላል። ሰከን ብለው አስበው አደራዳሪዎች ጭምር የሚያምኑበት የመጨረሻው ወረቀት / ዶክመንት / የቀበል ደረጃ ከደረሱ ሶስተኛ ውይይት ሊኖር ይችላል።

- ምናልባት ሶስተኛ ውይይት እንደሁለተኛው ውይይት ሰፊ ላይሆን ይችላል እስካሁን የተደከመበት ሰነድን መቀበል ላይ ከተደረሰ ሶስተኛው ውይይት ሊኖር ይችላል፤ ሶስተኛው ውይይት የመጨረሻም ይሆናልም ብዬ ገምታለሁ ወደሰላም ለመምጣት ወይም እስከመጨረሻው ሁለተኛ ላለመነጋገር የመጨረሻ ሊሆን ይችላል።

🕊 የኢጋድ ዋና ፀሀፊ የሆኑት ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ከሳምንታት በፊት ያለ ስምምነት የተጠናቀቀውን 2ኛው ዙር የኢትዮጵያ መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሰላም ድርድርን በተመለከተ ሰጥተው በነበረው መግለጫ ሌላ አዲስ ዙር ውይይት ይጀመራል ብለው #ተስፋ እንደሚያደርጉ መግለፃቸው አይዘነጋም።

@tikvahethiopia