TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኢትዮጵያ #ወታደራዊ ሃይሏን ለማዘመን በምታደርገው ጥረት የሕዋ ሃይልን የመከላከያ ሃይሏ አንድ አካል ለማድረግ ማቀዷን ብሉምበርግ በዘገባው አስነብቧል፡፡ “ዘመናዊ ጦርነት የየብስ፣ አየር፣ ባሕር፣ ሳይበር እና ጠፈር (ሕዋን) ያካተተ በመሆኑ ይህንኑ ከግምት ያስገባ መከላከያ ሃይል #እየገነባች ነው፡፡ በቅርቡ የተከለሰው የሀገሪቱ መከላከያ ፖለሲ ባሕር ሃይልን እና ወደፊት ደሞ የሳይበር ደኅንነትን እና ጠፈር ሃይልን የሚያካትት ይሆናል” የሚል ምላሽ ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጽህፈት ቤት ማግኘቱንም አክሎ ዘግቧል፡፡

ምንጭ፦ ብሉምበርግ(wazemaradio)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከ200 በላይ #የጥፋት_ሀይሎች በቁጥጥር ስር ዋሉ‼️

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ወረዳ ገንገን ቀበሌ ህገ ወጥ #ወታደራዊ_ስልጠና ሲከታተሉ የነበሩ ከ200 በላይ ወጣቶች በዛሬው እለት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የክልሉ ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል፡፡

የክልሉ የሰላም ግንባታ እና የፀጥታ ቢሮ ም/ሀላፊ ኮማንደር አብዱላዚም መሀመድ ለኢቢሲ እንደተናገሩት ወጣቶቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት የብሄራዊ መረጃና ደህንነት፣ የመከላከያ ሰራዊት፣ የፌደራል ፖሊስ እና የክልሉ የፀጥታ ሀይል በጋራ ባካሄዱት ኦፕሬሽን ነው።

የጥፋት ሀይሎቹ ከጥር 25/2011 ጀምሮ ከገንገን በመነሳት በሆሞሻ፣ ሸርቆሌ እና መንጌ ወረዳዎች አቋርጠው ወደ ኦዳ ቢልዲጊሉ ወረዳ በማቅናት የጥፋት እቅዳቸውን ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ ነው በቁጥጥር የዋሉት ብለዋል ኮማንደር አብዱላዚም።

#የጥፋት_ሀይሎቹ ሲጠቀሙበት የነበረ4 ክላሽንኮቭ፣ 1 ጅምስሪ፣ 1 ብሬን እና 4 ኋላ ቀር መሳሪያ በቁጥጥር መዋሉን ኮማንደር አብዱላዚም ተናግረዋል።

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቤንሻንጉል ጉምዝ‼️

በአሶሳ ወረዳ ከ190 በላይ የሚሆኑ የሚሊሺያ አባላት ከክልሉ መንግስት እውቅና ውጭ #ወታደራዊ ስልጠና መውሰዳቸው ተገለፀ። ይህን ባደረጉ አመራሮች ላይም ህጋዊ #እርምጃ ተወስዶባቸዋል።

በክልሉ የሰላም ግንባታና የፀጥታ ቢሮ የሚሊሺያ ዘርፍ ሃላፊ አቶ #ደርጉ_ዚያድ ለኢቢሲ እንደተናገሩት በክልሉ ደረጃ የሚሊሺያ ሰራዊትን በአዲስ መልክ ለማደራጀት እየተሰራ ነው ብለዋል።

ከሰሞኑ የሚሊሺያ ሰራዊት አባላት ግምገማ የተካሄደ ሲሆን ለውጡን ማስቀጠል የሚችል የሚሊሺያ ሰራዊት መዋቅር ለመዘርጋት በሚያስችል መልኩ ግምገማ ተካሂዷል። በዚህም ከአሶሳ ወረዳ ብቻ 140 የሚሊሺያ አባላት በክብር ተሰናብተዋል። እንዲሁም ሰኔ 17 በአሶሳ ከተማ ተከስቶ በነበረው ግጭት የተጠረጠሩ 9 የሚሊሺያ አባላት በህግ #ቁጥጥር ስር ውለዋል።

በአሶሳ ወረዳ 190 የሚሆኑ የሚሊሺያ ሰራዊት ከክልሉ መንግስት እውቅና ውጭ ወታደራዊ ስልጠና ወስደዋል ያሉት አቶ ደርጉ ይህን ባደረጉ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸው ብለዋል። የክልሉን የሚሊሺያ ሰራዊት በአዲስ መልክ ለማደራጀት እየተሰራ መሆኑን አቶ ደርጉ ለኢቢሲ ተናግረዋል።

Via ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወታደራዊ ልምምዳቸው ጀመሩ...

ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የሚያደርጉትን አመታዊ #ወታደራዊ ልምምድ ጀመሩ። ልምምዱ አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር ወታደራዊ ልምምድ ለማድረግ የደረሰችው ስምምነት ሲሆን፥ በዛሬው እለትም የአሜሪካ መከላከያ አባላት ከኢትዮጵያ መከላከያ ሃይል ጋር በጥምረት ልምምድ ማድረግ ጀምረዋል።

ወታደራዊ ልምምዱ በሶማሊያ በተሰማራው የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ሃይል (አሚሶም) አባላትን አቅም ማሳደግ ላይ ያተኮረ ሲሆን፥ ወደ 1 ሺህ 100 የሚጠጉ ወታደራዊና የመንግስት ሃላፊዎች ይሳተፉበታል።

ልምምዱ የመከላከያ አባላትን ዝግጁነትና አቅም በማሳደግ ሰላምን ለማስከበር የሚደረገውን ጥረት እንዲደግፉና በቀጠናው ሰላምን ለማስፈን እንደሚያግዝም ታምኖበታል። ከዚህ ባለፈም ሽብርተኝነትና የእርስ በርስ ግጭቶችን ቀድሞ ለመከላከል እንደሚያስችልም ተገልጿል።

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
📸ኤርትራ የግዳጅ ብሄራዊ #ወታደራዊ_አግልግሎት የጀመረችበትን 25ኛ ዐመት የብር እዮቤልዩ በዓል ትላንት አክብራለች፡፡ በዓሉ #በሳዋ_ወታደራዊ ማሰልጠኛ ነው በወታደራዊ ስነ ሥርዓት የተከበረው፡፡ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በክብረ በዓሉ ተገኝተው ነበር።

Via #wazema
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Turkey #Ethiopia የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ አካሂዶት በነበረው 5ኛ መደበኛ ስብሰባ ከቱርክ ሪፐብሊክ ጋር የተደረጉ ወታደራዊ የትብብር ስምምነቶችን ላይ ውይይት አድርጓል። ምክር ቤቱ ፤ ቱርክና ኢትዮጵያ ዘመናትን የተሻገረ ጥብቅ ወዳጅነት ያላቸው መሆኑን በማስታወስ ቱርክ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን አጋር መሆኗን በተደጋጋሚ ያረጋገጠች አገር ናት ብሏል። በዚህ መነሻነት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ…
#Ethiopia #Turkey

የኢትዮጵያ ፓርላማ በ #ኢትዮጵያ እና #ቱርክ መካከል የተደረጉ ወታደራዊ ስምምነቶችን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

ፓርላማው ስምምነቱን ያፀደቀው ባካሄደው ሰባተኛ መደበኛ ስብሰባው ነው።

ኢትዮጵያ እና ቱርክ ወታደራዊ ትብብሮችን ለማድረግ የሚያስችላቸውን የወታደራዊ ማዕቀፍ ስምምነት ነሃሴ 12 ቀን 2013 ዓ.ም በቱርክ አንካራ መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡

ከስምምነቱ መካከል በጥቂቱ ፦

(የወታደራዊ ማዕቀፍ ስምምነት)

➡️ ዓላማ፦ በ2ቱ አገሮች መካከል በመከላከያ ዘርፍ የሚደረገው ግንኙነት የሚመራበትን ግልጽ ማዕቀፍ ለመፍጠር ነው።

➡️ የስምምነቱ ይዘት ፦ በሁለቱ ሀገራት በትምህርት እና ስልጠና በተናጠልና በጋራ በሚዘጋጁ ወታደራዊ ልምምዶች ስለመካፈል፣ በመከላከያ ኢንዱስትሪ፣ የመረጃ ልውውጥ፣ የሎጅስቲክ፣ የጤና አገልግሎት፣ የመረጃ ስርአት እና የሳይበር ጥቃትን መከላከልና በሌሎች ተያያዥ መስኮች ፣ ከመደበኛ ጦርነት ውጭ ባሉ የሰላም ማስከበር ፣ የሰብዓዊ ድጋፍ ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ድንጋጌዎችን ያካተተ ነው።

➡️ በኢትዮጵያ ላይ የሚጥለው ግዴታ ፦ ሚስጥራዊ መረጃዎች፣ ሰነዶች እና ማቴሪያሎች ፣ አእምሮአዊ ንብረቶችን አስፈላጊውን ጥበቃ የማድረግ ኢትዮጵያ ለትምህርት እና ስልጠና ወደ ቱርክ ለምትልካቸው የመከላከያ አባላት እና ተማሪዎች በተቀባይ ሀገር የማይሸፈኑትን የህክምና ወጪዎችን ፣ ሌሎችንም የትምህርት እና ስልጠና ወጪዎችን የመሸፈን ግዴታ ይጥላል።

➡️ ከዚህ ስምምነት ኢትዮጵያ የምታገኘው ጥቅም ፦ የመከላከያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶችን ፣ የሎጅስቲክ አቅርቦቶችን እና ድጋፎችን ለማግኘት የሰራዊት ትጥቆችን እንዲሁም በሰው ኃይል እና አስተዳደር ዙሪያ የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ፣ የትምህርትና ስልጠና እድሎችን ለማግኘት ያስችላል።

(የወታደራዊ ፋይናንስ ትብብር ስምምነት)

➡️ ዓላማው ፦ በሁለቱ ሀገራት መካከል በመከላከያ ዘርፍ የሚደረገው ግንኙነት የሚመራበት ግልፅ የህግ ማዕቀፍ በመፍጠር የቱርክ መንግስት 100 ሚሊዮን የቱርክ ሊሬ ተመጣጣኝ የሆነ የአሜሪካ ዶላር ለኢትዮጵያ መንግስት ፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ ለመከላከያ ዓላማ የሚውል 100% በቱርክ ሀገር የተመረቱ የመከላከያ ቁሳቁሶችን እና አገልግሎቶችን መግዛት የሚችልበትን መርዕ ለመወሰን ነው።

➡️ የስምምነቱ ይዘት ፦ የቱርክ መንግስት 100 ሊሬ ተመጣጣኝ የአሜሪካ ዶላር ለኢትዮጵያ መንግስት ስለሚሰጥበት ሁኔታ የኢትዮጵያ መንግስት በዋናነት በቱርክ ከሚገኙ ኩባንያዎች 100% በቱርክ የተመረቱ የመከላከያ ቁሳቁሶችንና አገልግሎቶችን መግዛት የሚችልበትን መርህ ይደነግጋል።

➡️ በኢትዮጵያ ላይ የሚጥለው ግዴታ ፦ በሁለቱ ሀገራት የመረጃ ልውውጥ የተገኙ እና ሚስጥራዊ ተብለው የተለዩ መረጃዎችን ከሌላኛው ወገን የፅሁፍ ፍቃድ ሳይገኝ ለሌላ ሶስተኛ ወገን ያለ መግለፅ እና ሚስጥራዊ መረጃዎችን መጠበቅ እንዲሁም ከቱርክ መንግስት ለኢትዮጵያ መንግስት የተላለፈ ሀብት ፣ እቃ ወይም አገልግሎት ያለ ቱርክ መንግስት የፅሁፍ ፍቃድ ለሌላ ሀገር ወይም ሶስተኛ ወገን እንዳይተላለፍ ወይም ጥቅም ላይ እንዳይውል የማድረግ ግዴታን ይጥላል።

➡️ ከስምምነቱ ኢትዮጵያ የምታገኘው ጥቅም ፦ ኢትዮጵያ ከቱርክ መንግስት የምታገኘው 100 ሚሊዮን የቱርክ ሊሬ ተመጣጣኝ የአሜሪካ ዶላር ወታደራዊ ቁሳቁስ እና አገልግሎት ከቱርክ ድርጅቶች በመግዛት ለአስፈላጊ አገልግሎት ማዋል እንድትችል ያደርጋታል።

#Ethiopia_Turkey
#ኢትዮጵያ_ቱርክ #ወታደራዊ_ስምምነቶች

@tikvahethiopia
#Egypt #Somalia : የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ' ለሁለት ቀን የስራ ጉብኝት ' ብለው ግብፅ ይገኛሉ።

የፕሬዜዳንቱ ቢሮ እንዳለው በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸው በማጠናከር ላይ ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ጋር መክረዋል።

ስምምነታቸው ይዘቱ ምን እንደሆነ በዝርዝር ባይታወቅም ሀገራቱ #ወታደራዊ ትብብር ፕሮቶኮል ስምምነትም ተፈራርመዋል።

ግብፅ በሞቃዲሾ ኤምባሲ መክፈቷም ተነግሯል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ወደ ፕሬዜዳንትነት ስልጣን ከመጡ በኃላ ከግብፅ ጋር የተለየ ወዳጅነት ለመመስረት ሲሰሩ ታይቷል።

በተለይም ደግሞ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች በኋላና ሀገሪቱ ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነቷ ከሻከረ በኃላ ወደ ግብፅ ብዙ ጊዜ እየተመላሳለሱ ይገኛሉ።

Photo Credit - Villa Somalia

Via @thiqahEth