TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከ200 በላይ #የጥፋት_ሀይሎች በቁጥጥር ስር ዋሉ‼️

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ወረዳ ገንገን ቀበሌ ህገ ወጥ #ወታደራዊ_ስልጠና ሲከታተሉ የነበሩ ከ200 በላይ ወጣቶች በዛሬው እለት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የክልሉ ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል፡፡

የክልሉ የሰላም ግንባታ እና የፀጥታ ቢሮ ም/ሀላፊ ኮማንደር አብዱላዚም መሀመድ ለኢቢሲ እንደተናገሩት ወጣቶቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት የብሄራዊ መረጃና ደህንነት፣ የመከላከያ ሰራዊት፣ የፌደራል ፖሊስ እና የክልሉ የፀጥታ ሀይል በጋራ ባካሄዱት ኦፕሬሽን ነው።

የጥፋት ሀይሎቹ ከጥር 25/2011 ጀምሮ ከገንገን በመነሳት በሆሞሻ፣ ሸርቆሌ እና መንጌ ወረዳዎች አቋርጠው ወደ ኦዳ ቢልዲጊሉ ወረዳ በማቅናት የጥፋት እቅዳቸውን ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ ነው በቁጥጥር የዋሉት ብለዋል ኮማንደር አብዱላዚም።

#የጥፋት_ሀይሎቹ ሲጠቀሙበት የነበረ4 ክላሽንኮቭ፣ 1 ጅምስሪ፣ 1 ብሬን እና 4 ኋላ ቀር መሳሪያ በቁጥጥር መዋሉን ኮማንደር አብዱላዚም ተናግረዋል።

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia