TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#FakeBot

"የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብር ልናንበሸብሽዎት በ ቴሌግራም መጥተናል። ይህ bot ቁጭ ብለው ገንዘብ የሚያፍሱበት ነው። በዚህ ቦት 1 ሰዉ ሲጋብዙ 1 ብር ያገኛሉ አሁኑኑ ይቀላቀሉን።"

#የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ ስምን እየተጠቀሙ የሚሰራጩ የተሳሳቱ መልዕክቶችን በርካታ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች ሲቀባበሉት ተመልክተናል ይህ ፍፁም #ሀሰት ነው። መልዕክቱም የሚሰራጨው በሀሰተኛ ገፅ ነው!!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeBot

"የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብር ልናንበሸብሽዎት በ ቴሌግራም መጥተናል። ይህ bot ቁጭ ብለው ገንዘብ የሚያፍሱበት ነው። በዚህ ቦት 1 ሰዉ ሲጋብዙ 1 ብር ያገኛሉ አሁኑኑ ይቀላቀሉን።"

#የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ ስምን እየተጠቀሙ የሚሰራጩ የተሳሳቱ መልዕክቶችን በርካታ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች ሲቀባበሉት ተመልክተናል ይህ ፍፁም #ሀሰት ነው። መልዕክቱም የሚሰራጨው በሀሰተኛ ገፅ ነው!!

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeBot በኢትዮ ቴሌኮም ስም!

ትላንት በንግድ ባንክ ስም ዛሬ ደግሞ በኢትዮ ቴሌኮም ስም #ሀሰተኛ መልዕክቶች ሲሰራጩ እየተመለከትን ነው

"Ethio Telecom ካርድ ልናንበሸብሽዎት በ ቴሌግራም መጥተናል። ይህ bot ቁጭ ብለው ገንዘብ የሚያፍሱበት ነው። በዚህ ቦት 1 ሰዉ ሲጋብዙ 1 ብር ያገኛሉ አሁኑኑ ይቀላቀሉን።"

#የኢትዮቴሌኮምን ስምን እየተጠቀሙ የሚሰራጩ የተሳሳቱ መልዕክቶችን በርካታ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች ሲቀባበሉት ተመልክተናል ይህ ፍፁም #ሀሰት ነው። መልዕክቱም የሚሰራጨው በሀሰተኛ ገፅ ነው!!

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የዶክተር ደብረፅዮን መገለጫ ፦ ዛሬ ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መግለጫ ሰጥተው ነበር። ዶ/ር ደብረፅዮን እየተደረገ ባለው ጦርነት ኤርትራ ወታደሮች ከፌዴራል የፀጥታ ኃይል ጋር ግንባር ፈጥረው እየወጉን ነው ብለዋል። ይህን በተጨባጭ ማሳየት እንችላለን ፣ የያዝናቸው የኢሳያስ (ኤርትራ) ወታደሮች አሉ ሲሉ ገልፀዋል። እስካሁን ከ10 ሺ በላይ ወታደሮች ማርከናል ከነዚህ ውስጥ ደግሞ የኢሳያስ ወታደሮች…
'የተከዜ ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ'

ትላንት ምሽት ዶክተር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል 'የተከዜ ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ' በአየር ተደብድቧል ፤ የትግራይ ክልል ከተሞች በጨለማ ውስጥ እንዲቆዩ ተደርጓል ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል።

በፌዴራል መንግስት ስር የሚተዳደረው "የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ" ተከዜ በቦንብ እንደተመታ የሚነገረው #ሀሰት ነው ብሏል።

ባለሁለት ክበብ ቅስት ያለው እና በውሀ የተሞላ ግድብ በቦንብ ቢመታ ሊያስከትል የሚችለው መጥለቅለቅ እና ጥፋት ማንም ሊገምተው የሚችለው ነው ሲልም ገልጿል።

* የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ በጉዳዩ ላይ ያወጣው መረጃ ከላይ ተያይዟል !

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
'የሽምግልና የውይይት ጉዳይ'

በፌዴራል መንግስት ስር የሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጣሪያ በዩጋንዳ የፌዴራሉ ባለስልጣናት "ከህወሓት" ጋር ለሽምግል እና ውይይት ሊቀመጡ እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ #ሀሰት ነው ብሏል።

ይህ መረጃ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር ሲሰራጭ ነበር።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጣሪያው ፥ "የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል የህግ የበላይነትን ለማስከበር በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል" ሲል ለህዝብ ባሰራጨው አጭር መግለጫ ገልጿል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#DireDawa : " ሙሉ እና ጎዶሎ በሚል የተጀመረ የትራንስፖርት አገልግሎት የለም " - የት/ባለስልጣን

በት/ባለስልጣን የድ/ዳ/ቅ/ጽ/ቤት ፥ በድሬደዋ የታክሲ አገልግሎት ሙሉ ጎዶሎ በሚል
መሰጠት ስለመጀመሩ እየተሰራጨ ያለው መረጃ
#ሀሰት ነው ሲል አሳውቋል።

ቅ/መስሪያ ቤቱ የታክሲ አሽከርካሪዎች ከመሰል የሀሰት ማደናገሪያዎችበመጠበቅ አገልግሎት መስጠታቸውን እንዲቀጥሉም አሳስቧል፡፡

የሚቀየሩ የአገልግሎት አሰጣጦች ሲኖሩ ከትራፊክ ፖሊስ ዳይሬክቶሬት ጋር በመቀናጀት እንደሚወጡና ይህንንም በተቋሙ ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅና በሌሎች ሚዲያዎች ይፋ እንደሚደረግ አሁን ላይ ግን ምንም አይነት የሙሉ ጎዶሎ አገልግሎት እንዳልተጀመረ እና እንደማይጀመር ገልጿል።

ከሰሞኑ በከተማው የታክሲ አገልግሎት ጎዶሎና ሙሉ በሚል እየተሰጠ አንደሚገኝ ተደርጎ ምንጩ ያልታወቀ መረጃ እየተሰራጨ ይገኛል፡፡

@tikvahethiopia
#ሀሰት_ነው !

" ከሱዳን ጋር #በቅርቡ በድንበር ጉዳይ የተደረሰ ስምምነት የለም " - በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ

ሰሞኑን አንዳንድ ሚዲያዎች በሱዳን የሚገኙትን የኢትዮጵያ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በመጥቀስ የኢትዮጵያንና የሱዳንን ድንበር በተመለከተ ስምምነት እንደተደረሰ ሲዘግቡ ተስተውሏል።

በተለይ Alsharq AL-awsat English ጋዜጣ በድህረ ገፁ “Addis Ababa, Khartoum Reach Deal on Border Dispute” በሚል ርዕስ እ.ኤ.አ ፌብርዋሪ 13 ቀን 2022 ያስነበበው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪ ጋዜጣው የመረጃውን ምንጭ ሳይጠቅስ ያቀረበው ሲሆን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ከዚህ ጋዜጣ ጋር ግንኙነት እንዳላደረጉ እና መረጃ እንዳልሰጡ ኤምባሲው ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ችሎት የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ እና አምባሳደር ድሪባ ኩማ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል መጥሪያ እንዲደርሳቸው ፍርድ ቤቱ አዘዘ። የመጥሪያ ትዛዙን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። በነ ሜ/ጀነራል ክንፈ ዳኘው የመርከብ ግዢ የሙስና ክስ ላይ በመከላከያ ምስክርነት ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲመሰክሩ ነው መጥሪያ እንዲደርሳቸው የታዘዘው።…
#ሀሰት_ነው !

የቀድሞ የሜቴክ ዋና ዳይሬክተር ሜ/ጀ ክንፈ ዳኘው ከእስር ተፈቱ እየተባለ በማህበራዊ ድረ ገጽ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው

ሜ/ጀ ክንፈ ዳኘው ከተከሰሱባቸው የሙስና ክሶች መካከል የመርከብ ግዢ እና የእርሻ መሳሪያ ግዥ ጋር ተያይዞ የቀድሞ ጠ/ሚ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ እና የኢጋድ ዋና ጸሀፊ ዶ/ ር ወርቅነህ ገበየሁን ጨምሮ ሌሎችም የመከላከያ ምስክሮች እንዲቀርቡ በታዘዘው ትዕዛዝ መሰረት የመከላከያ ማስረጃ ለመስማት ፍርድ ቤቱ በቀጠሮ ላይ መሆኑ ይታወቃል።

በሌላ በኩል ሜ/ጀ ክንፈ ዳኘው ከህዳሴው ግድብ ምንጣሮ ጋር ተያይዞ በቀረበባቸው ሌላኛው የሙስና ክስ ነጻ የተባሉ ቢሆንም በቀሪ ክሶች ግን በቀጠሮ ላይ ይገኛሉ።

ከእስር ተፈተዋል እየተባለ የሚናፈሰው መረጃ ሀሰት ነው

Credit : ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

@tikvahethiopia
#ሀሰት_ነው !

" ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ትደግማላቸሁ " በሚል የሚናፈሰው ወሬ ከእውነት የራቀ መሆኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

በ2014 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ማጠቃለያ ላይ ተማሪዎች ማጠቃለያ ፈተናዎችን ለመውስድ እየተዘጋጁ ይገኛሉ።

ነገር ግን ማህበራዊ ኃላፊነት በጎደላቸው አካላት ሆን ተብሎ ተማሪዎችን ለማዘናጋት በዘንድሮ ዓመት ከክፍል ወደ ክፍል መዘዋወር የለም ተብሎ በማህበራዊ የመገናኛ ዘዴዎች የሚናፈሰው ወሬ ፍፁም ከእውነት የራቀ መሆኑን ቢሮው ገልጿል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የወረደ አቅጣጫ የለም ያለው የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተማሪዎች " ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ትደግማላቸሁ" በሚል አሉባልታ ሳይምታቱ ለትምህርታቸው ትኩረት ስጥተዉ ለተሻለ ውጤት እንዲተጉ መልዕክት አስተላልፏል።

በተጨማሪ ⬇️

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚኒስቴሩን ስም እና አርማ በመጠቀም የተሳሳቱ እና የተዛቡ መረጃዎች እየተለቀቁ መሆኑን ገልጾ ተማሪዎች እና ወላጆች የሚሰረጩት መረጃዎች ከእውነት የራቁ መሆናቸውን በማወቅ በትኩረት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ አሳስቧል።

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia በአማራ ክልል በተለይ በሰሜን ሸዋ እና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ትላንት በተጠናቀቀው የካቲት ወር በተፈፀሙ ጥቃቶች በርካቶች ተገድለዋል። ጉዳትም ደርሷል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ በወሩ ስለነበሩት ሁኔታዎች ከሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ለማግኘት እጅግ በርካታ ቀናትን የወሰደ ሙከራ ቢያደርግም ምንም ምላሽ የሚሰጠ አካል አላገኘም። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ግን ስለነበሩት ሁኔታዎች…
#AmharaRegion

° " ህዝቡ በታጠቁ ቡድኖች ነው ለጥቃት የተዳረገው በገዛ ከተማው ነው መአት ያወረደበት ... ጥቃት ፈፃሚዎቹ ከአጎራባች ' ሸኔ ' ናቸው " - የአጣዬ ከተማ ከንቲባ

° " #ሀሰት_ነው የኦሮሞ አርሶ አደሮች እንጂ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት አይደሉም " " - አባገዳ አህመድ ማህመድ

በአማራ ክልል ፤ የሰሜን ሸዋን እና የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደርን በሚያጎራብቱ አካባቢዎች ላይ ግጭት ከጀመረ ከሳምንት በላይ ሆኖታል።

በተደጋጋሚ ፦
- የሰዎች ደም በሚፈስበት፣
- ንብረት በሚወድምበት ፣
- ሰዎች ቄያቸውን ለቀው በሚፈናቀሉበት በዚህ ቀጠና ባለፈው የካቲት ወር ውስጥም በርካቶች መገደላቸው ይታወሳል።

አሁን ደግሞ #ከ8_ቀናት በፊት የተቀሰቀሰው ግጭት እጅግ መባባሱን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በመነሻው ላይ በሁለቱም በኩል እርስ በእርስ መወነጃጀል ያለ ሲሆን በኤፍራታ ግድምና ቀወት ውስጥ ግጭቱ ከፍቶ መዋሉ ነው የተሰማው።

በሁለቱም በኩል ያሉት ነዋሪዎች ፣ የአጣዬ ከንቲባ ፣ የአካባቢው አባገዳ ምን አሉ ?

በኤፍራታ ግድም ወረዳ የአላላ ከተማ ነዋሪ ፤ ጦርነት ከተጀመረ 8 ቀን መያዙን ፣  ብዙ ቤቶች መቃጠላቸውን ገልጸዋል።

ነዋሪው " የአርሶ አደሮች ዱቄት ሳይቀር ፣ በግ ፣ ፍየል ፣ ግመል ፣ አህያ፣ ከብት በሙሉ ሙልጭ አድርገው ወስደውብናል። ኃላሸት የሚባል ሰውም ገድለውብናል እኛው ክልል ላይ ገብተው " ሲሉ ተናግረዋል።

ይህን ካደረጉ በኃላ ህዝቡ ተሬ እና ዘንቦ ወደሚባለው አካባቢ በለበሰው ልብስ ሸሽቶ ተጠልሎ እንደሚገኝ ገልጸዋል። " በተከታታይ 18 ሰዎችን ገድለውብናል "ም ብለዋል።

በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር የሰንበቴ ነዋሪ ፤ " እስከ ጅሌ ጥሙጋ ባርሲሳ ፣ ካራ ሌንጫ ፣ መከና ወይም አጣዬ ከተማ ዙሪያ ባሉ ቀበሌዎች ከትላንትና ጀምሮ ተኩስ ነበር። ትላንት አንዲት ሴት እንዲሁም ግመልና ከብቶችም ተመተው ነበር ግጭቱ የቀጠለው በዚህ ነው፤ አንድ ሰው ሲሞት ሁለት ሰው ቆስለዋል፤ አንዱ ወደ አዳማ ተልኳል። ዛሬ ደግሞ 4 ሰው ሲሞት 3 ሰው ቆስሏል " ብለዋል።

ዋነኛው እቅዳቸው የጅሌ ጥሙጋ ከተማ #ሰንበቴን " እንይዛለን ፣ እናጠፋለን " የሚል ነው ሲሉ ገልጸዋል።

አንድ የአጣዬ ነዋሪ ደግሞ ፤ ሰሞኑን ግጭት ተባብሶ ዛሬ አጣዬን በተኩስ ልውውጥ ሲያናውጥ መዋሉን ፣ 5 ሰው መገደሉም. ጥቃት ፈፃሚዎቹ የታጠቁ አካላት " ሸኔ " ናቸው ብለዋል።

ሌላው የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ፣ የሰንበቴ ነዋሪ " ግጭቱ የጀመረው #መጋቢት_አንድ ላይ ነው። ይህም በጅሌጥሙጋ ኮላሽ የሚባል ስፍራ 1 ሰው ገድለው 2 ሰው አቁስለው ከብቶችንም ነድተው ከሄዱ በኃላ ነው ግጭቱን የተስፋፋው " ሲሉ ተናግረዋል።

" ከባልች ቀበሌ እስከ ሰንበቴ እና መከና አጣዬ ድረስ ጦርነት ነው። የዛሬውን ለየት ያደረገው ታጣቂዎቹ #ከሰሜን_ሸዋ ተሰባስበው ፤ እራሳቸውን አደራጀትው ሌሊቱን በተሽከርካሪዎች ተጉዘው መጥተው ውጊያ መክፈታቸው ነው " ሲሉ አክለዋል።

ባለፉት 10 ቀናት 29 ሰዎች መገደላቸውን ተናግረው የተወሰዱት ከብቶችና የወደመው ንብረትም ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።

ይህ አስተያየት #አልቀበልም ያሉት የአላላ ነዋሪው ፤ " አማራው ሲያጠፋ በአማራው አጥፊውን መዞ ለህግ ማቅረብ፤ ከኦሮሞውም ሲያጠፋ አጥፊውን መዞ ለህግ ማቅረብ ሰላም የሚያሰፍነው ይሄ ብቻ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" በህግ እና በሽምግልና  ነገሩ መክሰም አለበት እነሱ የሚሉት ከጨፋ ጀምሮ እስከ ሸዋሮቢት ድረስ የኦሮሞ ቦታ ነው። አጣዬም #የኛ_ነች ፤ አላላም ፣ ሞላሌም ፣ ማጀቴም ... ሁሉም የኛ ነው የሚሉት። መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ችግሩን ሊፈታው ይገባል " ብለዋል።

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን #አባገዳ አህመድ ማህመድ " መንገድ የለም። ከጅሌ ጥሙጋ እና አርጡማ ፋርሲ ወረዳዎች እንዲሁም ከዞን መገናኘት አልቻልንም " ብለዋል።

" በዚህ ምክንያት የሃይማኖት አባቶች እና አባ ገዳዎች ተሰባስበው መፍትሄው ምንድነው ? ለማለት መንገዱ ተከፍቶ ለህዝቡ ምግብ ለማድረስ ፣ የቆሰሉትንም ወደ ህክምና ቦታ ለመውሰድ ጥረት ላይ ነን። መንገድ ከተዘጋ 1 ወር ሊሆነው ነው። እኛም ሆነ መንግሥታዊ አመራሩ ሄደን ማየት አልቻልንም። የአማራ ክልልም #ታጣቂዎቹን_ስለሚፈሯቸው ቀርበው ለማነጋገር አልተቻለም። እኛ ጋር ያሉትን #ወሰናችሁን አልፋችሁ አትሂዱ እያልን እየመከርናቸው ነው ። " ገልጸዋል።

ነዋሪዎችና የአካባቢው አስተዳደሮች ጥቃቱን የከፈቱት " ሸኔ (የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት) " ናቸው ቢሉም አባገዳ አህመድ " ሀሰት ነው " ብለዋል።

" ሀሰት ነው የኦሮሞ አርሶ አደሮች እንጂ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት አይደሉም። የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እዚህ አልገባም። እየተዋጋ ያለው እራሱ ነዋሪው ነው " ብለዋል።

የአጣዬ ከተማ ከንቲባው ተመስገን ተስፋ ፤ ከተማዋና ህዝቡ በታጠቁ ቡድኖች ነው ለጥቃት የተዳረጉት ብለዋል።

አጣዬ ላይ ' #ወረራ ' መፈፀሙን ገልጸው " ሰውም አልቋል፤ ሚሊሻውም የሚችለውን ያህል ሞከረ አለቀ " ብለዋል።

ይህን የሚፈፅሙት ከአጎራባች  " #ሸኔ በሏቸው " ሲሉ የጠሯቸውን የታጠቁ ኃይሎች መሆናቸውን ገልጸዋል።

" ዋናው መፍትሄ መንግሥት ጠንከር ብሎ #እርምጃ መውሰድ ያለበት ላይ እርምጃ መውሰድ ፤ ይሄ ነበረ መፍትሄው  አሁን ባለው መንገድ ፣ #በእሹሩሩ ሰውም አለቀ " ብለዋል።

#የአጣዬ_ህዝብ የገዛ ከተማው ላይ እንዳለ መአት እንደወረደበት የገለጹት ከንቲባው " እጅግ በጣም አስቸጋሪ ነው፤ መንግስት ቢደርስልን ጥሩ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ከኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር በኩል ለጥፋቱ ለችገሩ " የፋኖ ታጣቂዎችን " ተጠያቂ ሲያደርጉ ከሰሜን ሸዋ ዞን በኩል ደግሞ " ሸኔን (የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት) " ተጠያቂ ያደርጋሉ።

NB. ባለፉት አምስት ዓመታት አጣዬ ከ10 ጊዜ በላይ የመቃጠል አደጋ አስተናግዳለች።

እስካሁን የአማራ ክልል መንግሥት ስለ ጉዳዩ ያለው ነገር የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ #ባለቤትነቱ የቪ.ኦ.ኤ. ራድዮ (ጋዜጠኛ መስፍን አራጌ) መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia