TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#AmharaBank የአማራ ባንክ ነገ ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ.ም ሥራውን በይፋ ይጀምራል። ባንኩ ነገ በይፋ ስራ የሚጀምርበትን የምረቃት ስነስርአት ከጥዋት 3:00 ጀምሮ ለገሃር በሚገኘው ዋናው መስሪያ ቤት ያካሂዳል። ነገ ቅዳሜ ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ.ም የሚያካሂደውን የምርቃ ስነስርዓት በማስመልከት በልዩ ሁኔታ ለአዲስ አበባ እና ዙሪያው #አንበሳ አውቶቡስ ተጠቃሚዎች በሙሉ የሙሉ ቀን (ከጠዋቱ…
ፎቶ ፦ አማራ ባንክ በዛሬው ዕለት ተመርቆ ሥራውን በይፋ ጀምሯል።

የባንኩ የምረቃ እና ስራ ማስጀመሪያ ሰነ ስርዓት ለገሃር በሚገኘው የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ነው የተካሄደው።

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ፦
- የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶክተር ይናገር ደሴ ፣
- የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ፣
- የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የተለያዩ የመንግስት ባለስልጣናት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ባንኩ ከ70 በላይ የሚሆኑ ቅርንጫፎቹ በይፋ ስራ መጀመራቸው ተነግሯል።

አማራ ባንክ ዘመኑ የደረሰበትን የኮር ባንኪንግ ሲስተም በመጠቀም ከ165,000 በላይ ባለአክሲዮኖችን በመያዝ የተመሰረተ ባንክ ነው።

አማራ ባንክ ከቀደሙት ባንኮች ብዙ በመማር በተለይም ዝቅተኛውን የህብረተሰብ ክፍል ለማቀፍ ተደራጅቶ " ከባንክ ባሻገር " በሚል መሪ ቃል የተመሰረተ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የቀጠለው ግድያ በአሜሪካ ! ትላንት አንድ የ23 ዓመት ወጣት በምዕራብ ሜሪላንድ ስሚዝበርግ ገጠራማ አካባቢ በሚገኝ የማምረቻ ድርጅት (Columbia Machine) ተኩስ ከፍቶ 3 ሰራተኞችን ገድሏል። ግለሰቡ በድርጅቱ ውስጥ ሰራተኛ ሲሆን ተኩስ ከፍቶ 3 ሰራተኞችን ለመግደል ያነሳሳው ጉዳይ ምን እንደሆነ አልታወቀም። ተኩስ ከፍቶ ከገደላቸው 3 ሰዎች በተጨማሪ ከአንድ ሜሪላንድ ግዛት ፖሊስ ጋር ተኩስ…
በአሜሪካ የቀጠለው ግድያ !

ደቡባዊ አሜሪካ በምትገኘው በአላባማ ክፍለ ሀገር ጥቂት ሰዎች በተሰባሰቡበት ቤተ ክርስቲያን ታጣቂ ተኩስ ከፍቶ 3 ሰዎች ገድሏል።

ባለሥልጣናት በርሚንግሃም ከተማ አቅራቢያ በሚገኝ ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ጥቃቱን በማድረስ የተጠረጠረው ማንነቱ ያልታወቀ ሰው ተይዟል ብለዋል።

አሜሪካ ውስጥ ሰሞኑን የመሳሪያ ጥቃት በተከታታይ መድረሱ የመሳሪያ ቁጥጥር ለውጥ እርምጃን አስፈላጊነት የሚመለከተውን ክርክር መቀስቀሱን ቪኦኤ ዘግቧል።

ባለፈው ወር ኒው ዮርክ ባፈሎ ከተማ ውስጥ በሚገኝ የምግብ እና ሸቀጣ ሸቀጥ መደብር በዘረኛ ጥቃት አስር ጥቁር አሜሪካውያን ተገድለዋል።

ከዚያም ወዲህ ቴክሳስ ዩቫልዴ ከተማ ትምህርት ቤት ውስጥ ተኩስ የከፈተ አጥቂ አስራ ዘጠኝ ተማሪዎች ጨመሮ ሃያ አንድ ሰዎች ገድሏል።

በተጨማሪ ከሳምንታት በፊት በተለያዩ ከተሞች በተከፈቱ ተኩሶች እና ጥቃቶች 9 ሰዎች ሲገደሉ በርካቶች መቁሰላቸው እንዲሁም በምዕራብ ሜሪላንድ ገጠራማ አካባቢ በሚገኝ የማምረቻ ድርጅት ተኩስ ተከፍቶ 3 ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#ማሳሰቢያ📣

" ከሚመለከታቸው የጸጥታ አካላት ውጭ የጦር መሣሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው " - የደብረ ማርቆስ ፖሊስ መምሪያ

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ማንኛውም ግለሠብ ከፀጥታ ሀይሎች ውጭ ያሉ ግለሠቦች ያለበቂ ምክንያት በከተማ ውስጥ መሣሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ መሆኑን የከተማው ፖሊስ አሳስቧል።

መሣሪያን በመዝናኛ ቦታዎች ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች ያለበቂ ምክንያት ይዞ መንቀሳቀስ የፀጥታ ሀይሉን የሚያዘናጋ እና እኩይ ተግባር ያላቸውን ግለሰቦች ለይቶ ለመቆጣጠር የማያስችል ነው ተብሏል።

ከዚህ ባለፈ የጸጥታ ሀይሉ የህግ ማስከበር ስራውን ለመስራት እንቅፋት እንደሆነበትና የተዝረከረከ የጦር መሣሪያ አያያዝ ለከተማው ህዝብ ደህንነት ስጋት እየሆነ በመምጣቱ በህግ ማስከበር ስራ ላይ ከተሠማራ የጸጥታ ሀይል ውጪ ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ሳያገኝ በየትኛውም በከተማው ክልል ውስጥ በማንኛውም ሰአት መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ እና ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል።

በተለይ ፦
- በአልጋ ድርጅቶች እና ሆቴሎች ፣
- በወለል ቤቶች ፣
- በዶርም ፣
- በመኖሪያ ቤት በእንግድነት የሚመጡ ግለሠቦች መሣሪያ ይዘው የመጡበትን ጉዳይ ቅድሚያ ለፖሊስ እውቅና ሳይፈጥሩ እና ፈቃድ ሳያገኙ አገልግሎት ማግኘት የለባቸውም ተብሏል።

የአልጋ ድርጅቶች ፣ ወለል አከራዮች እና የዶርም አከራዮች የተከራዮችን ማንነት እስከ ታጠቁት መሣሪያ ሙሉ አድራሻውን በመመዝገብ በየጊዜው ለፖሊስ ማሳወቅ ይገባቸዋል ተብሏል።

ማህበረሰቡ ከፀጥታ ኃይል ውጭ የጦር መሣሪያ ይዞ የሚንቀሳቀስ አካላትን በሚመለከትበት ግዜ ፦
0587711232 (3ኛ ፖሊስ ጣቢያ)
0587711669 (1ኛ ፖሊስ ጣቢያ)
0581785658 (2ኛ ፖሊስ ጣቢያ) በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba ነገ የሚዘጉ መንገዶች !

( ከንጋቱ 11:30 ጀምሮ እስከ ቀኑ 6:00 ድረስ)

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በ #መሰቀል_አደባባይ ባዘጋጀው ስፖርታዊ ዝግጅት እና መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ በሚያደርገው የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ምክንያት ነገ እሁድ ሰኔ 12 ቀን 2014 ዓ.ም ከንጋቱ 11 ከ30 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 6:00 ሰዓት ድረስ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወሰዱ መንገዶች ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

የሚዘጉት መንገዶች ፦

🛣 ከወሎ ሰፈር መገንጠያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አካባቢ

🛣 ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያን በሰዓት 50 እና 80 ኪ.ሜ በተፈቀደባቸው በሁለቱም አቅጣጫ

🛣 ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያአትር የሚወስደው የቀድሞ ደሳለኝ ሆቴል

🛣 ከንግድ ማተሚያ ቤት በኦርማ ጋራዥ በፍል ውሃ ወደ መስቀል አደባባይ ኦርማ ጋራዥ መስቀለኛው ላይ
ከ4 ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ ኮንሰን ወይም ወደ ሸራተን ሆቴል የሚወስደው መንገድ ላይ፡፡

🛣 ከሳር ቤት አካባቢ ለሚመጡ አሸከርካሪዎች አፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት

🛣 ከፒያሳ አካባቢ በቸርቸር ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ፖስታ ቤት ትራፊክ መብራት ላይ

🛣 ከካዛንቺስ በፍል ውሃ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ እና በተመሳሳይ ካዛንቺስ የትራፊክ መብራት በባምቢስ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ የትራፊክ መብራት ላይ

🛣 ከጎፋ በቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ወደ ለገሐር አዲሱ መንገድ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛው ላይ

🛣 ከቄራ ወደ ሜክሲኮ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ጠማማ ፎቅ አካባቢ

🛣 ከጦር ኃይሎች ፣ በልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወሰደው መንገድ ባልቻ ሆስፒታል መስቀለኛ

🛣 ከመርካቶ በበርበሬ በረንዳ ወደ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው አረቄ ፋብሪካ አካባቢ

🛣 ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ አሸከርካሪዎች አጎና ሲኒማ አካባቢ

🛣 ከጎተራ በመሿለኪያ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ መንገዱ ይዘጋል።

ህብረተሰቡ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

ውድ ቤተሰቦቻችን ነገ እሁድ የሚያንቀሳቅሳችሁ ጉዳይ ካለ ከላይ በተገለፀው መረጃ መሰረት እንዳትጉላሉ አማራጭ መንገዶችን ተጠቀሙ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ አማራ ባንክ በዛሬው ዕለት ተመርቆ ሥራውን በይፋ ጀምሯል። የባንኩ የምረቃ እና ስራ ማስጀመሪያ ሰነ ስርዓት ለገሃር በሚገኘው የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ነው የተካሄደው። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ፦ - የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶክተር ይናገር ደሴ ፣ - የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ፣ - የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የተለያዩ የመንግስት ባለስልጣናት…
#AmharaBank

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ ዛሬ በዛሬው የአማራ ባንክ ይፋዊ ምረቃና ስራ ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ የተናገሩት ፦

" አማራ ባንክ ወደ ገጠሩ ማህበረሰብ በመድረስና ከፍተኛ የአክስዮን ድርሻን በመሸጥ እንዲሁም ከፍተኛ የተከፈለ ካፒታል ይዞ የባንክ ኢንዱስትሪውን በመቀላቀል ቀዳሚው ነው።

በቴክኖሎጂ እና በአገልግሎት አሰጣጥም ተወዳዳሪ በመሆን ቀዳሚ መሆን እንዲችል ራሱን ሊያዘጋጅ ይገባል።

ይህ ከሃገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ከሚታሰቡ የውጭ ባንኮች ጋር ጭምር ለመወዳደር ያስችላል።

ወደ ሀገር እንደሚገቡ ከሚጠበቁት የውጭ ባንኮች ጋር ለመወዳደር ትልቅ ዝግጅት ይጠብቀናል። ለዚህም አማራ ባንክን ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ ባንኮች ራሳቸውን ሊያዘጋጁ ይገባል።

አማራ ባንክ ይህን የሚያደርግና የቁጠባ ገንዘብ አቅሙን ለማሳደግ የሚችል ከሆነ በአጭር አመታት ውስጥ ከፍተኛ ደረጃ ሊደርስ ይችላል።

... 60 ሚሊዮን ገደማ ኢትዮጵያውያን የተንቀሳቃሽ ስልክ (ሞባይል) ተጠቃሚ ናቸው ፤ አማራ ባንክ የተፋጠነ የሞባይል አገልግሎትን በየደረጃው ለመስጠት መስራት አለበት።

የሞባይል አገልግሎት የሚሰጡ የውጭ ተቋማት በቅርብ ጊዜ የአገልግሎት ፈቃድ ሊያገኙ ይችላሉ፤ በአሁኑ ወቅት ቴሌ ብር ብቻ ነው አገልግሎቱን እየሰጠ የሚገኘው በመሆኑም አማራ ባንክ ቅርንጫፎችን ከመክፈት በዘለለ በቴክኖሎጂ ላይ ኢንቨስት ማድረግ ወደ ከፍታ ሊወስደው እንደሚችል አስባለሁ "

#ALAIN

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአፋር ባህላዊ እርቅ (1).pdf
ሙከጀላ በኤደን ገስላሴ.pdf
665.6 KB
#3

#እኔም_የዕርቅ_ሀሳብ_አለኝ

ሙከጀላ ባሕላዊ የዕርቅ ስርዓት በድሬዳዋ ማህበረሠብ

አዘጋጅ፦ ኤደን ገ/ስላሴ

በድሬዳዋ ሙከጀላ የሚባል የቀደመ ባሕል አለ፡፡ ሙከጀላ በማህበረሰቡ መካከል ለሚፈጠረ ማንኛውም ግጭትም ሆነ አለመግባባት በዛፍ ጥላ ሆኖ የሚመከርበት ቀደምት ባህል ነው፡፡

የዕርቁ ሂደት የሚካሔድበትን ቀንና ቦታ የሚመርጡት ማኅበረሰቡ የመረጣቸው፤ ትልቅ ቦታ በሚሰጣቸውና በሚከበሩ ትልልቅ አባቶች
ነው፡፡ የዕርቅ ሥርዓቱም የሚካሄደው በአካባቢው በሚገኘው ሙከጀላ በተባለ የዛፍ ጥላ ስር ነው፡፡

በባህሉ መሠረት ሽማግሌዎች ቀን እና ቦታ በቆረጡበት በሠአቱ ይገኛሉ፡፡ ይህም ሠዓትን የማክበር ልምድ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ የማህበረሰቡ ልምድ እና ባህል ነው፡፡

የተፈፀመው ጥፋት ተመጣጣኝ ነው ተብሎ ከታመነ ይቅር ለፈጣሪ ተባብለው እንዲያልፉት ቢደረግም በዚህ ሂደት ውስጥ ግን ጥፋቱ ከባድ ሆኖ ከተገኘ በመጀመሪያ በዳይ እግር ስር ወድቆ ይቅርታ ይጠይቃል፡፡

ከዚህ በኋላ አላጠፋም ፣ እታረማለው፣ ካሣዬንም እከፍላለው በማለት በአባቶች ፊት መሃላ ይፈፅማል፡፡ ተከሳሽም የሚከፍለው ካሣ መጠን በታዛቢዎች ፊት ለተበዳይ በግዜውና በሠዓቱ አንዲሰጥ ይወሰናል።

ባህላዊ የዕርቅ ሥርዓት ፍትህ እንዲገኝ ትልቅ አስተዋፅኦ የሚያደርገው እውነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ነው፡፡ ዘርን፣ ሀይማኖትን፣ ፆታን፣ ሀብትን እና ሌሎች ልዩነቶችን ሳያደርግ ሚዛናዊ የሆነ ዳኝነት ስለሚሰጥ የባህላዊ ዕርቅ ሥርዓት ፍትህን ያስገኛል፡፡

ሙከጀላ በፊት ላይ ከፍተኛ ተቀባይነት የነበረው ቢሆንም አሁን ላይ ግን ይህ ስርዓት ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ወደ መረሳት ላይ ደርሷል፡፡ ይህ ባህል አለ እንኳን ቢባል በጣም በተወሰኑ ቦታዎች ላይ ነው፡፡

📁 ሙሉ ጹሑፉን ከላይ ተያይዟል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ያላየነው ብዙ ጭካኔ ይኖር ይሁን ? በርካቶች በጋምቤላ ተቀርፆ በተሰራጨው ጨካኔ የተሞላበት አረመኔያዊ ቪድዮ የተሰማቸውን ሀዘን በአግባቡ ሳይወጡ ዛሬ ደግሞ አንድ ቀኑ ሆነ አድራሻው የት እንደሆነ የማይታወቅ የጅምላ ርሸና ቪድዮ ተሰራጭቷል። ለጊዜው ድርጊቱ መቼ .. ? የት ? እንዴት ? ተፈፀመ ስለሚለው ማወቅ ቢያዳግትም ከዚህ ቀደም እንዳየናቸው እጅግ በጣም ዘግናኝ እና ህጋዊ ያልሆነ የጭካኔ ተግባር…
#UPDATE #EHRC

በማህበራዊ ሚዲያ የተለቀቀው ቪድዮ

" ... በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ የሚታየው ከሕግ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት (Extra-judicial killings) ኢሰመኮ መጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ሪፖርት ላይ የተካተተ ነው።

የኢሰመኮ የምርመራ ሪፖርት ከምስክሮች እና በስፍራው በመገኘት በመስክ ምልከታ ያሰባሰበውን መረጃ መሰረት በማድረግ፣ ድርጊቱ በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ ልዩ ቦታው እንቶሊ አካባቢ በታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. የመጀመሪያ ሳምንት (ቀኑ በትክክል ያልታወቀ) መፈጸሙን፤ እንዲሁም በወቅቱ በነበረው መረጃ መሰረት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በሁለት የጭነት መኪኖች ጭነው ያመጡዋቸውን እና ወደ 30 የሚጠጉ የኦነግ ሸኔ አባሎች ናቸው ያሏቸውን ሰዎች በጅምላ በጥይት ደብድበው መግደላቸውን ይገልጻል። 

ኢሰመኮ ተንቀሳቃሽ ምስሉን ከተመለከተ በኋላ ባደረገው ተጨማሪ ማጣራትና የቴክኒክ ምርመራ፣ በመስክ ምርመራ በለየው ስፍራና በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ ያለውን ስፍራ በቴክኒክ ምርመራ በማነጻጸር፣ እንዲሁም ምስሉ የተቀረጸበትን ቦታ ለማነጻጸርና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የቴክኒክ ምርመራዎችን በማድረግ፤ ከዚህ በላይ የተገለጸው በኢሰመኮ ምርመራ የተዘገበው ከፍርድ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት የሚያመለክት ተጨማሪ ማስረጃ ስለመሆኑ በምክንያታዊ አሳማኝነት አረጋግጧል "

#ኢሰመኮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ያላየነው ብዙ ጭካኔ ይኖር ይሁን ? በርካቶች በጋምቤላ ተቀርፆ በተሰራጨው ጨካኔ የተሞላበት አረመኔያዊ ቪድዮ የተሰማቸውን ሀዘን በአግባቡ ሳይወጡ ዛሬ ደግሞ አንድ ቀኑ ሆነ አድራሻው የት እንደሆነ የማይታወቅ የጅምላ ርሸና ቪድዮ ተሰራጭቷል። ለጊዜው ድርጊቱ መቼ .. ? የት ? እንዴት ? ተፈፀመ ስለሚለው ማወቅ ቢያዳግትም ከዚህ ቀደም እንዳየናቸው እጅግ በጣም ዘግናኝ እና ህጋዊ ያልሆነ የጭካኔ ተግባር…
#EHRC

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን በመዘዋወር ላይ የሚገኘውን እና በርካታ ሰዎች ከመኪና እንዲወርዱ በማድረግ በጅምላ ሲገደሉ የሚያሳየውን ተንቀሳቃሽ ምስል ሁኔታ መርምሯል።

በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ የሚታየው ከሕግ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት (Extra-judicial killings) ኢሰመኮ መጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. “በኢትዮጵያ የአፋር እና የአማራ ክልሎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች እና የዓለም አቀፍ የሰብአዊነት ሕግ ጥሰቶች ላይ የተደረገ ምርመራ ሪፖርት” በሚል ርዕስ ባወጣው ሪፖርት ውስጥ ከተዘረዘሩት ክስተቶች ውስጥ አንዱ መሆኑን ተረድቷል። 

በዚሁ የኢሰመኮ የምርመራ ሪፖርት ከምስክሮች እና በስፍራው በመገኘት በመስክ ምልከታ ያሰባሰበውን መረጃ መሰረት በማድረግ፣ ድርጊቱ በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ ልዩ ቦታው እንቶሊ አካባቢ በታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. የመጀመሪያ ሳምንት (ቀኑ በትክክል ያልታወቀ) መፈጸሙን፤ እንዲሁም በወቅቱ በነበረው መረጃ መሰረት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በሁለት የጭነት መኪኖች ጭነው ያመጡዋቸውን እና ወደ 30 የሚጠጉ የኦነግ ሸኔ አባሎች ናቸው ያሏቸውን ሰዎች በጅምላ በጥይት ደብድበው መግደላቸውን ይገልጻል። 

ኢሰመኮ ተንቀሳቃሽ ምስሉን ከተመለከተ በኋላ ባደረገው ተጨማሪ ማጣራትና የቴክኒክ ምርመራ፣ በመስክ ምርመራ በለየው ስፍራና በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ ያለውን ስፍራ በቴክኒክ ምርመራ በማነጻጸር፣ እንዲሁም ምስሉ የተቀረጸበትን ቦታ ለማነጻጸርና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የቴክኒክ ምርመራዎችን በማድረግ፤ ከዚህ በላይ የተገለጸው በኢሰመኮ ምርመራ የተዘገበው ከፍርድ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት የሚያመለክት ተጨማሪ ማስረጃ ስለመሆኑ በምክንያታዊ አሳማኝነት አረጋግጧል፡፡

ስለሆነም ኢሰመኮ ከዚህ ቀደም ባቀረበው ምክረ ሃሳብ መሰረት የተሟላ የወንጀል ምርመራ ተደርጎ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ በድጋሚ ያሳስባል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን
ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ/ም

@tikvahethiopia
#OromiaRegion

ጊምቢ ወረዳ በርካታ ሰዎች ተገደሉ።

በዛሬው ዕለት #በምዕራብ_ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ውስጥ በርካታ ንፁሃን በታጣቂዎች መገደላቸው ተሰምቷል።

መልዕክታቸውን የላኩ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በአካባቢው ይንቀሳቀሳል ያሉት የታጠቀ ቡድን ጥቃት ከፍቶ #በርካታ ሰዎች መገደለቸውን (ትክክለኛ ቁጥሩን ለማወቅ አዳጋች ነው) ታግተው የተወሰዱ መኖራቸውን እንዲሁም ነፍሳቸውን ለማትረፍ ወደ ጫካ የሸሹ ስለመኖራቸውን ገልፀዋል።

ከሟቾች መካከል ህፃናት እና ሴቶች እንደሚበዙ ፤ ቤቶች መንደዳቸውንም ፤ ጥቃቱ ሲፈፀም የነበረው በከባድ መሳሪያ ጭምር እንደነበር አመልክተዋል።

ለሚመለከተው የወረዳው አካል በሰዓቱ ጥቃት መኖሩን ጥቆማ ቢያደርሱም በቶሎ የደረሰ አካል እንዳልነበረ አስረድተዋል።

የዛሬውን እጅግ አሳዛኝ ጥቃት ክልሉም አምኖ አረጋግጧል። ጥቃቱን ጭካኔ የተሞላበትም ነበር ብሏል።

ክልሉ ባወጣው መግለጫ " የሸኔ ቡድን በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ባደረሰው ጥቃት በንጹሃን እና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል " ብሏል።

" ቡድኑ መንግሥት እየወሰደበት ያለውን እርምጃ መቋቋም ሲያቅተው በንጹሃን ላይ ጭካኔ የተሞላበት ጥቃት አድርሷል " ሲል ገልጿል።

በቡድኑ ላይ የፌደራል እና የክልሉ የጸጥታ አካላት የሚወስዱትን እርምጃ አጠናክረው ይቀጥላሉም ብሏል።

ክልሉ ምን ያህል ንፁሃን እንደተገደሉ እንዲሁም ታፍነው ስለተወሰዱ ሰዎች ምንም ያለው ነገር የለም።

@tikvahethiopia