#AddisAbaba ነገ የሚዘጉ መንገዶች !

( ከንጋቱ 11:30 ጀምሮ እስከ ቀኑ 6:00 ድረስ)

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በ #መሰቀል_አደባባይ ባዘጋጀው ስፖርታዊ ዝግጅት እና መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ በሚያደርገው የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ምክንያት ነገ እሁድ ሰኔ 12 ቀን 2014 ዓ.ም ከንጋቱ 11 ከ30 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 6:00 ሰዓት ድረስ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወሰዱ መንገዶች ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

የሚዘጉት መንገዶች ፦

🛣 ከወሎ ሰፈር መገንጠያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አካባቢ

🛣 ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያን በሰዓት 50 እና 80 ኪ.ሜ በተፈቀደባቸው በሁለቱም አቅጣጫ

🛣 ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያአትር የሚወስደው የቀድሞ ደሳለኝ ሆቴል

🛣 ከንግድ ማተሚያ ቤት በኦርማ ጋራዥ በፍል ውሃ ወደ መስቀል አደባባይ ኦርማ ጋራዥ መስቀለኛው ላይ
ከ4 ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ ኮንሰን ወይም ወደ ሸራተን ሆቴል የሚወስደው መንገድ ላይ፡፡

🛣 ከሳር ቤት አካባቢ ለሚመጡ አሸከርካሪዎች አፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት

🛣 ከፒያሳ አካባቢ በቸርቸር ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ፖስታ ቤት ትራፊክ መብራት ላይ

🛣 ከካዛንቺስ በፍል ውሃ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ እና በተመሳሳይ ካዛንቺስ የትራፊክ መብራት በባምቢስ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ የትራፊክ መብራት ላይ

🛣 ከጎፋ በቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ወደ ለገሐር አዲሱ መንገድ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛው ላይ

🛣 ከቄራ ወደ ሜክሲኮ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ጠማማ ፎቅ አካባቢ

🛣 ከጦር ኃይሎች ፣ በልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወሰደው መንገድ ባልቻ ሆስፒታል መስቀለኛ

🛣 ከመርካቶ በበርበሬ በረንዳ ወደ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው አረቄ ፋብሪካ አካባቢ

🛣 ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ አሸከርካሪዎች አጎና ሲኒማ አካባቢ

🛣 ከጎተራ በመሿለኪያ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ መንገዱ ይዘጋል።

ህብረተሰቡ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

ውድ ቤተሰቦቻችን ነገ እሁድ የሚያንቀሳቅሳችሁ ጉዳይ ካለ ከላይ በተገለፀው መረጃ መሰረት እንዳትጉላሉ አማራጭ መንገዶችን ተጠቀሙ።

@tikvahethiopia