TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ አማራ ባንክ በዛሬው ዕለት ተመርቆ ሥራውን በይፋ ጀምሯል። የባንኩ የምረቃ እና ስራ ማስጀመሪያ ሰነ ስርዓት ለገሃር በሚገኘው የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ነው የተካሄደው። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ፦ - የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶክተር ይናገር ደሴ ፣ - የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ፣ - የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የተለያዩ የመንግስት ባለስልጣናት…
#AmharaBank

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ ዛሬ በዛሬው የአማራ ባንክ ይፋዊ ምረቃና ስራ ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ የተናገሩት ፦

" አማራ ባንክ ወደ ገጠሩ ማህበረሰብ በመድረስና ከፍተኛ የአክስዮን ድርሻን በመሸጥ እንዲሁም ከፍተኛ የተከፈለ ካፒታል ይዞ የባንክ ኢንዱስትሪውን በመቀላቀል ቀዳሚው ነው።

በቴክኖሎጂ እና በአገልግሎት አሰጣጥም ተወዳዳሪ በመሆን ቀዳሚ መሆን እንዲችል ራሱን ሊያዘጋጅ ይገባል።

ይህ ከሃገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ከሚታሰቡ የውጭ ባንኮች ጋር ጭምር ለመወዳደር ያስችላል።

ወደ ሀገር እንደሚገቡ ከሚጠበቁት የውጭ ባንኮች ጋር ለመወዳደር ትልቅ ዝግጅት ይጠብቀናል። ለዚህም አማራ ባንክን ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ ባንኮች ራሳቸውን ሊያዘጋጁ ይገባል።

አማራ ባንክ ይህን የሚያደርግና የቁጠባ ገንዘብ አቅሙን ለማሳደግ የሚችል ከሆነ በአጭር አመታት ውስጥ ከፍተኛ ደረጃ ሊደርስ ይችላል።

... 60 ሚሊዮን ገደማ ኢትዮጵያውያን የተንቀሳቃሽ ስልክ (ሞባይል) ተጠቃሚ ናቸው ፤ አማራ ባንክ የተፋጠነ የሞባይል አገልግሎትን በየደረጃው ለመስጠት መስራት አለበት።

የሞባይል አገልግሎት የሚሰጡ የውጭ ተቋማት በቅርብ ጊዜ የአገልግሎት ፈቃድ ሊያገኙ ይችላሉ፤ በአሁኑ ወቅት ቴሌ ብር ብቻ ነው አገልግሎቱን እየሰጠ የሚገኘው በመሆኑም አማራ ባንክ ቅርንጫፎችን ከመክፈት በዘለለ በቴክኖሎጂ ላይ ኢንቨስት ማድረግ ወደ ከፍታ ሊወስደው እንደሚችል አስባለሁ "

#ALAIN

@tikvahethiopia