TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Assosa

ከሰሞኑን በአሶሳ ከተማ ውስጥ በግለሰቦች ቤት በተደረገ ፍተሻ የተከማቸ 50 በርሜል ነዳጅ ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውሏል።

የአሶሳ ከተማ ፖሊስ ለኢዜአ በሰጠው ቃል ፤ በህገ-ወጥ መንገድ የተከማቸው 50 በርሜል ነዳጅ (ቤንዚን እና ናፍጣ) ከ4 ተጠርጣሪዎች ጋር በህብረተሰብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስረድቷል።

በተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ እየተደረገ መሆኑንም ገልጿል።

በአሁኑ ወቅት በከተማው #ቤንዚን እና #ናፍጣ በጥቁር ገበያ በሊትር እስከ 200 ብር እየተሸጠ መሆኑን ፖሊስ የጠቆመ ሲሆን የዚህ ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት ምንጭ በህጋዊ መንገድ ከነዳጅ ማደያዎች ተቀድቶ በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ጥቂት ግለሰቦች እጅ መግባት መሆኑን አስረድቷል።

@tikvahethiopia
#Wecare

በህፃናት ላይ የሚታዩ አስጊ የጤና ምልክቶች ከምስሉ ላይ ይመልከቱ።

የ WeCare ET ሕክምና መተግበሪያ ሥመጥር ስፔሻሊስት ሐኪሞችን ባሉበት ቦታ ሆነው ለማማከር የሚያስችል መተግበሪያ ነው።

መተግበሪያውን ለመጫን ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ። https://play.google.com/store/apps/details?id=com.icare.patient

ለበለጠ መረጃ 9394 ላይ ይደውሉልን።
መረጃዎችን ለማግኘት wecare.et ን ይጎብኙ
Wecare Et social medias

📌 Telegram: https://publielectoral.lat/WeCareET
#selamdoctor #wecareet
#Update

#ፊንላንድ #ስውዲን #ሩስያ #NATO

➡️ የስዊድን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አን ሊንዴ ሀገራቸው የNATO አባል እንድትሆን ማመልከቻ መፈራረማቸው ተነግሯል። ሚኒስትሯ የፈረመት የአባልነት ጥያቄ ማማልከቻ ከፊንላንድ የNATO ማመልከቻ ጋር አብሮ ይቀርባል ሲሉ የሀገሪቱ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

➡️ ዛሬ የፊንላንድ ፓርላማ የNATO ወታደራዊ ጥምረት አባል ለመሆን የቀረበውን ሀሳብ በ188 ድምጽ በስምንት ተቃውሞ አፅድቋል።

➡️ ፊንላንድ ለNATO አባልነት ማማልከቻ ልታቀር መሆኑን ተከትሎ ሩሲያ የኒኩሊየር ጦር መሳሪያ አስወንጫፊ ሚሳየሎችን ወደ ፊንላንድ ድንበር ማስጠጋቷ ተነግሯል ፤ ወደ ፊንላንድ ድንበር ያስጠጋ የኢስካንደር ሚሳየሎች እንደሆነ ተሰምቷል።

➡️ ስዊድን ለNATO አባልነት ጥያቄ ለማቅረብ ከውሳኔ ላይ መድረሷን ተከትሎ ሩሲያ በብሔራዊ ደህንነቷ ላይ የሚደርሰውን ስጋት ለመቅረፍ ወታደራዊ-ቴክኒካል እና ሌሎች የምላሽ እርምጃዎችን እንደምትወስድ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ከሰዓት ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

➡️ የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በድጋሚ ሀገራቸው ፊንላንድ እና ስውዲን የNATO አባል ለመሆን የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንደማይደግፉ አረጋግጠዋል። ሀገራቱ ወደ አንካራ የአግባቢ ልዑክ ይልካሉ እየተባለ ሲሆን ኤርዶጋን ግን " አቋማችን ግልፅ ነው ወደ አንካራ ልኡክ በመላክ ባትለፉ እኛንም ባታስቸግሩን ይሻላችኃል " ብለዋቸዋል።

ቱርክ ፤ ፊንላንድ እና ስውዲን የNATO አባል ለመሆን የሚያደርፉትን እንቅስቃሴ ለምንድነው የማትደግፈው ? ይህን ያንብቡ ፦ https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/70164?single

መረጃዎቹ የተሰባሰቡት ፦ ከአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ፣ ሲጂቲኤን ፣ ቴሌግራፍ፣ ኤፒ ፣ ዬል ነው።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

በመጀመሪያ ዕጣ 7 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው የልዩ -2 ሎተሪ አጣ ዛሬ ወጥቷል።

የልዩ -2 ሎተሪ ዛሬ በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡

በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆኗል።

1ኛ. 7,000,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 0759162

2ኛ. 3,000,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 0134613

3ኛ.1,000,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 0299997

4ኛ. 400,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 1037132

5ኛ. 100,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 0530065

6ኛ. 50,000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 0516747

7ኛ. 30,000 ብር የሚያስገኘው የ7ኛ ዕጣ ቁጥር 1185534

8ኛ. 12 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 2,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 01329

9ኛ.12 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 31649

10ኛ. 12 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 400 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 02455

11ኛ. 120 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 120 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 4335

12ኛ. 120 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 0652

13ኛ. 1,200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 768

14ኛ. 12,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 60 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 50

15ኛ. 120,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 40 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ 6 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡

ምንጭ፦ የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ሀገር እንደ ልብስ አትበጣጠስም " - ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ

ዛሬ የ2014 ዓ/ም ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የመክፈቻ ጸሎት መርሐ ግብር በአዲስ አበባ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተካሂዷል።

በዚሁ መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ ስለ #ሰላም መልዕክት አስተላልፈዋል።

ብፁዕነታቸው ፥ " በአሁን ጊዜ በቤተክርስቲያናችን በኩል ያለው ከሚመጣው መከራ የተነሳ ምዕመናን ከመሞታቸው ፣ ካህናት ሰማዕት ከመሆናቸው የተነሳ ቤተክርስቲያኒቱ መከረኛ ሆናለች ፤ ድሮም መከረኛ ናት በእርግጥ የሰማዕታት ቤት ናት ፤ ስለዚህም ተግተን ልንፀልይ ሰላምንም ልናስገኝ ይገባል " ብለዋል።

" ሁሉ የተጣላበት ዘመን ነው " ያሉት ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ " በሰዎች ዘንድ ፣ በሁሉ ዘንድ ሰላም የለም " ሲሉ ገልፀዋል።

" አንድ አካል ፣ አንድ ህዝብ ፣ አንድ ህብረ አባል፣ አንድ ህብረ ሀገር የሆነች ኢትዮጵያ በአሁን ጊዜ እርስ በእርሱ መጣላት ፣ መጋጨት ፣ መጋደል እየታየ ነው " ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ " ይህችን ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያን ለመከፋፈል የሚሞክሩ የተወገዙ ይሁኑ ፤ ለምንድነው ይሄ የሚሆነው ? ሀገር አትከፈልም፣ ሀገር እንደ ልብስ አትበጣጠስም ፥ ይህኔ ሁሉ ያርቅልን ዘንድ እግዚአብሔር አምላካችን በጥበቡ በቅዱስ ፍቃዱ ያርቅልን " ሲሉ መልዕክታቸውን አስታላልፈዋልን።

ዛሬ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በነበረው የመክፈቻ ጸሎት መርሐ ግብር ላይ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፣ ብፁአን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ተገኝተው ነበር።

ፎቶ ፦ EOTC TV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Turkey #Ethiopia የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ አካሂዶት በነበረው 5ኛ መደበኛ ስብሰባ ከቱርክ ሪፐብሊክ ጋር የተደረጉ ወታደራዊ የትብብር ስምምነቶችን ላይ ውይይት አድርጓል። ምክር ቤቱ ፤ ቱርክና ኢትዮጵያ ዘመናትን የተሻገረ ጥብቅ ወዳጅነት ያላቸው መሆኑን በማስታወስ ቱርክ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን አጋር መሆኗን በተደጋጋሚ ያረጋገጠች አገር ናት ብሏል። በዚህ መነሻነት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ…
#Ethiopia #Turkey

የኢትዮጵያ ፓርላማ በ #ኢትዮጵያ እና #ቱርክ መካከል የተደረጉ ወታደራዊ ስምምነቶችን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

ፓርላማው ስምምነቱን ያፀደቀው ባካሄደው ሰባተኛ መደበኛ ስብሰባው ነው።

ኢትዮጵያ እና ቱርክ ወታደራዊ ትብብሮችን ለማድረግ የሚያስችላቸውን የወታደራዊ ማዕቀፍ ስምምነት ነሃሴ 12 ቀን 2013 ዓ.ም በቱርክ አንካራ መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡

ከስምምነቱ መካከል በጥቂቱ ፦

(የወታደራዊ ማዕቀፍ ስምምነት)

➡️ ዓላማ፦ በ2ቱ አገሮች መካከል በመከላከያ ዘርፍ የሚደረገው ግንኙነት የሚመራበትን ግልጽ ማዕቀፍ ለመፍጠር ነው።

➡️ የስምምነቱ ይዘት ፦ በሁለቱ ሀገራት በትምህርት እና ስልጠና በተናጠልና በጋራ በሚዘጋጁ ወታደራዊ ልምምዶች ስለመካፈል፣ በመከላከያ ኢንዱስትሪ፣ የመረጃ ልውውጥ፣ የሎጅስቲክ፣ የጤና አገልግሎት፣ የመረጃ ስርአት እና የሳይበር ጥቃትን መከላከልና በሌሎች ተያያዥ መስኮች ፣ ከመደበኛ ጦርነት ውጭ ባሉ የሰላም ማስከበር ፣ የሰብዓዊ ድጋፍ ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ድንጋጌዎችን ያካተተ ነው።

➡️ በኢትዮጵያ ላይ የሚጥለው ግዴታ ፦ ሚስጥራዊ መረጃዎች፣ ሰነዶች እና ማቴሪያሎች ፣ አእምሮአዊ ንብረቶችን አስፈላጊውን ጥበቃ የማድረግ ኢትዮጵያ ለትምህርት እና ስልጠና ወደ ቱርክ ለምትልካቸው የመከላከያ አባላት እና ተማሪዎች በተቀባይ ሀገር የማይሸፈኑትን የህክምና ወጪዎችን ፣ ሌሎችንም የትምህርት እና ስልጠና ወጪዎችን የመሸፈን ግዴታ ይጥላል።

➡️ ከዚህ ስምምነት ኢትዮጵያ የምታገኘው ጥቅም ፦ የመከላከያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶችን ፣ የሎጅስቲክ አቅርቦቶችን እና ድጋፎችን ለማግኘት የሰራዊት ትጥቆችን እንዲሁም በሰው ኃይል እና አስተዳደር ዙሪያ የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ፣ የትምህርትና ስልጠና እድሎችን ለማግኘት ያስችላል።

(የወታደራዊ ፋይናንስ ትብብር ስምምነት)

➡️ ዓላማው ፦ በሁለቱ ሀገራት መካከል በመከላከያ ዘርፍ የሚደረገው ግንኙነት የሚመራበት ግልፅ የህግ ማዕቀፍ በመፍጠር የቱርክ መንግስት 100 ሚሊዮን የቱርክ ሊሬ ተመጣጣኝ የሆነ የአሜሪካ ዶላር ለኢትዮጵያ መንግስት ፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ ለመከላከያ ዓላማ የሚውል 100% በቱርክ ሀገር የተመረቱ የመከላከያ ቁሳቁሶችን እና አገልግሎቶችን መግዛት የሚችልበትን መርዕ ለመወሰን ነው።

➡️ የስምምነቱ ይዘት ፦ የቱርክ መንግስት 100 ሊሬ ተመጣጣኝ የአሜሪካ ዶላር ለኢትዮጵያ መንግስት ስለሚሰጥበት ሁኔታ የኢትዮጵያ መንግስት በዋናነት በቱርክ ከሚገኙ ኩባንያዎች 100% በቱርክ የተመረቱ የመከላከያ ቁሳቁሶችንና አገልግሎቶችን መግዛት የሚችልበትን መርህ ይደነግጋል።

➡️ በኢትዮጵያ ላይ የሚጥለው ግዴታ ፦ በሁለቱ ሀገራት የመረጃ ልውውጥ የተገኙ እና ሚስጥራዊ ተብለው የተለዩ መረጃዎችን ከሌላኛው ወገን የፅሁፍ ፍቃድ ሳይገኝ ለሌላ ሶስተኛ ወገን ያለ መግለፅ እና ሚስጥራዊ መረጃዎችን መጠበቅ እንዲሁም ከቱርክ መንግስት ለኢትዮጵያ መንግስት የተላለፈ ሀብት ፣ እቃ ወይም አገልግሎት ያለ ቱርክ መንግስት የፅሁፍ ፍቃድ ለሌላ ሀገር ወይም ሶስተኛ ወገን እንዳይተላለፍ ወይም ጥቅም ላይ እንዳይውል የማድረግ ግዴታን ይጥላል።

➡️ ከስምምነቱ ኢትዮጵያ የምታገኘው ጥቅም ፦ ኢትዮጵያ ከቱርክ መንግስት የምታገኘው 100 ሚሊዮን የቱርክ ሊሬ ተመጣጣኝ የአሜሪካ ዶላር ወታደራዊ ቁሳቁስ እና አገልግሎት ከቱርክ ድርጅቶች በመግዛት ለአስፈላጊ አገልግሎት ማዋል እንድትችል ያደርጋታል።

#Ethiopia_Turkey
#ኢትዮጵያ_ቱርክ #ወታደራዊ_ስምምነቶች

@tikvahethiopia
Addis Ababa University- Cisco Network Academy, @CiscoExams www.netacad.com

Cisco CCNA and CCNP Professional Network Engineering Training & Certification Preparation.

Class start date: June 18, 2022.

CCNA trainees will receive 3 international certificate of training completion, digital badge & 58% discount voucher for the international exam.

Phone #: 0902-340070 OR 0935-602563 OR 0945-039478:

Follow our telegram channel: @CiscoExams
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #ፊንላንድ #ስውዲን #ሩስያ #NATO ➡️ የስዊድን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አን ሊንዴ ሀገራቸው የNATO አባል እንድትሆን ማመልከቻ መፈራረማቸው ተነግሯል። ሚኒስትሯ የፈረመት የአባልነት ጥያቄ ማማልከቻ ከፊንላንድ የNATO ማመልከቻ ጋር አብሮ ይቀርባል ሲሉ የሀገሪቱ ሚዲያዎች ዘግበዋል። ➡️ ዛሬ የፊንላንድ ፓርላማ የNATO ወታደራዊ ጥምረት አባል ለመሆን የቀረበውን ሀሳብ በ188 ድምጽ…
#Update

#ፊንላንድ #ስውዲን #ሩስያ #NATO

➡️ ፊንላንድ እና ስዊድን NATOን ለመቀላቀል በይፋ የማመልከቻ ደብዳቤያቸውን ለNATO አስገብተዋል።

➡️ የNATO ዋና ፀሃፊ ጄንስ ስቶልተንበርግ ፊንላንድ እና ስዊድን የዓለም ትልቁን ወታደራዊ ህብረት ለመቀላቀል በይፋ ጥያቄ ማቅረባቸውን አረጋግጠዋል። ዋና ፀሀፊው 2ቱ ሀገራት የNATO አባል ለመሆን ያቀረቡትን ጥያቄ በከፍተኛ ደስታ መቀበላቸውን ገልፀዋል።

➡️ ፊንላንድ እና ስዊድን የNATO ጥምረት አባል ለመሆን ያቀረቡት ማመልከቻ በ30ዎቹ አባል አገራት የሚታይ ሲሆን ሂደቱ ሁለት ሳምንታትን ሊፈጅ እንደሚችል ተነግሯል። ቱርክ ሀገራቱን የአሸባሪዎች ማረፊያ ናቸው በማለት NATOን ለመቀላቀል የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ደጋግማ መቃወሟ ይታወቃል።

➡️ ነገ ሀሙስ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን የስውዲን ጠቅላይ ሚኒስትር እና የፊንላንድ ፕሬዜዳንት በዋይትሀውስ ተቀብለው ያነጋግራሉ፤ የ2ቱ ሀገራት መሪዎች NATOን ለመቀለቀል እያደረጉት ስለለው ሂደት ከባይደን ጋር ይወያያሉ ተብሏል። አሜሪካ ሀገረቱ የNATO አባል እንዲሆኑ ከፍተኛ ድጋፍን እየሰጠች ከምትገኝ ሀገር አንዷ ናት።

➡️ NATOን መቀላቀል በማሰቧ ከዩክሬን ጋር ጦርነት ውስጥ የምትገኘው ሩስያ አሁንም ወታደራዊ ኦፕሬሽኖችን እያካሄደች ነው። ሩስያ
በዶኔትስክ እና ሉሃንስክ የምድር ላይ ወታደራዊ ኦፕሬሽኖች መቀጠሏ ተነግሯል።

➡️ ሩስያ፤ ፊንላንድና ስዊድን NATO የሚቀላቀሉ ከሆነ አፀፋዊ እርምጃ እንደምትወስድ እየዛተች ነው ይህን ተከትሎ ፊንላንዳውያን በገፍ ወታደራዊ ስልጠናዎችን እየወሰዱ ነው። እንደ ዩክሬን ልንወረር እንችላል በሚል የሃገሪቱን ጦር በመቀላቀል በፈቃደኝነት ወታደራዊ ስልጠናዎች እየወሰዱ ይገኛሉ።

#አልጀዚራ #አፒ #አልአይን #ቲአርቲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሀገር እንደ ልብስ አትበጣጠስም " - ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ ዛሬ የ2014 ዓ/ም ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የመክፈቻ ጸሎት መርሐ ግብር በአዲስ አበባ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተካሂዷል። በዚሁ መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ ስለ #ሰላም መልዕክት አስተላልፈዋል። ብፁዕነታቸው ፥ " በአሁን ጊዜ በቤተክርስቲያናችን በኩል ያለው ከሚመጣው መከራ የተነሳ…
#UPDATE

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓመት ሁለት ጊዜያት ከሚካሄዱት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤያት አንዱ የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ (የ2014 ዓ/ም) መካሄድ ጀምሯል።

ጉባኤውን አስመልክቶ ፥ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸው ፤ ጉባኤው ራሱን ከማናቸውም አደረጃጀት ነጻ አድርጎ የሰላም ጥሪን በማሰማት ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ሰላም መረጋገጥ ለሰላም በሰላም መሥራት መጣርና ውጤት ማምጣት እንደሚጠበቅበት ገልፀው በዚህ ዙርያ ይህ ዓቢይ ጉባኤው በስፋት ተወያይቶ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥ ይጠበቀል ብለዋል።

አክለውም ፤ " ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን እና ወገኖቻቻችን የምናስተላልፈው መልእክት ሰላምንና አንድነትን ለማረጋገጥ ጕልበትን እንደ አማራጭ መውሰድ አቁመን የተከሠቱብንን ችግሮች በውይይትና በድርድር ለመፍታት ለሚደረገው ጥረት የላቀ ድጋፍ በመስጠት በጦርነትና በረኃብ፣ በድርቅና በበሽታ እያለቁ ያሉ ልጆቻችንንና ወገኖቻችንን እንድንታደግ በእግዚአብሔር ስም በመማፀን መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን " ብለዋል።

(የአባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia