TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሀጫሉ_ሁንዴሳ ከፋና ጋዜጠኛ ጋር በነበረው ቆይታ በርካታ ጥያቄዎች ተነስተውለት መልሷል።

እኔም ዝግጅቱን ከሰማው በኋላ የአቅሜን ከዚህ በታች በፅሁፍ አስቀምጬዋለሁ።
.

ጥቂት ስለ ጂራ...?

ጂራ ማለት አለን ማለት ነው። የህዝቡን ስነ ልቦና ስታይው አለን የሚያስብል ነው።... ጂራ ኤርትራም ገብቷል። ህዝብ ተለያይቶ አይለያይም። ኤርትራዊያንም ጂራ ገብቷቸዋል ማለት ነው።
.
.
ስለ ስሙ...??

ሀጫሉ ማለት "ይብለጥ" ማለት ነው። አባቴ በልጅነቴ ፈጣን እና ንቁ ስለነበርኩ ያወጣልኝ ስም ነው። እኔ ከማንም እበልጣለሁ ብዬ አላስብም።"
.
.
ስለ ዶክተር አብይ...??

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ የሀገራችን ህዝቦች ዴሞክራሲ ምን እንደሚመስል ያዩ ይመስለኛል። ባልተለመደ መልኩ የሰው ልጅ የተሰማውን በአደባባይ እንደፈለገ እንዲናገር ...ከሀገራችን ህዝብ አምዕሮ በላይ የሆኑ ነገሮች ታይተዋል።

#ግን ህዝባችን ለመላመድ ጊዜ የሚያስፈልገው ይመስለኛል። ሲረገጥ፣ ሲጨቆን፣ ሲበደል የነበረ ህዝብ በአንድ ጊዜ እንደዚህ ፈሪሀ እግዚያቤር ያለው መሪ መጥቶ #እንደፈለክ ሁን ሲለው ያን እራሱ እንዴት አድርጎ መሆን እምደሚችል ላያቅበት ይችላል።

በአጠቃላይ ጥንቃቄ ያስፈልጋል ከመንግስትም ከህዝብም እንጂ በሂደት የሚስተካከል ይመስለኛል።
.
.
.
ስለ ሀምሌ 7 የሚሊኒየም አዳራሽ ዝግጅት...?

እኔ እንደዛን ዕለት ቦታና ወቅቱን መርጬ ያስተላለፍኩት መልዕክት ያለም አይመስለኝም። ጠቅላይ ሚንስቱር ግና እንደተመረጡ ...እያንዳንዱን በየፕሮፌሽኑ ልምድ ሲሰጡ ነበር አርቲስቱንም እንደዛው የህዝባችሁን ጩኸት አሰሙ ያመናችሁበትን ስሩ ብለው ነው የመከሩት። የሳቸው ምክር More ጉልበት ሆኖኛል። እኔ የዛን ቀን ምንም ሀጢያት አልሰራሁም። እኔ ኢትዮጵያ የማውቃት #አዲስ_አበባ ብቻ አይደለችም። ምናልባት ድግስ ሊኖር ይችላል አዲስ አበባ ላይ ...መተማ ላይ ኢትዮጵያዊ ከሞተ ኢትዮጵያዊ እየሞተ ነው ብሎ address ማድረግ ..ሀረር ላይ ኢትዮጵያዊ ከሞተ ኢትዮጵያዊ እየተገደለ ነው ስለዚህ መንግስት አንድ ነገር ማድረግ አለበህ ብሎ በጥበብ መልክ ለማስተላለፍ እኔ ቦታው ነው ቦታው አይደለም ብሎ ማሰብ ተገቢ ነው ብዬ አላምንም። እንግዳን መናቅ አይመስለኝም።
.
.
ሀጫሉ ዘረኛ ነው ይሉሀል??

#ዘረኛ ነህ ካልሽኝ ዘረኛ #አደለሁም። እኔ ያሳደገኝ እና የወጣሁት ከኦሮሞ ማህበረሰብ ነው። በኦሮሞ ማህበረሰብ #ዘረኝነት ይኮነናል። በገዳ ስርዓት ውስጥ ዘረኝነት ይኮነናል። ዘረኛ መሆንም #አልችልም። ዘረኛ ብሆን ኢንተቪው የምናደርገው በአስተርጓሚ ነው።

አፌን የፈታሁት በኦሮሚኛ ነው። ዘረኛ ስላልሆንኩ ነው በአማርኛ የማወራው። ለሌላውም ቋንቋ አድናቆት እና ክብር አለኝ።

በምን አይነት መልኩ ተረድተውኝ እንደዚህ እንዳዚህ እንዳሉኝ ሊገባኝ አይችልም። ምናልባት የሚመስለኝ እሱ የሚዘፍነው ኦሮሞ...ኦሮሞ...ኦሮሚያ እያለ ነው የሚል ከሆነ ኦሮሞና ኦሮሚያ ከኢትዮጵያ ውጭ አይደሉም። ኦሮሞ ሆኜ ስለ ሱዳን እና ስለ ኬንያ ብዘፍን ነው የሚያስወቅሰኝ። ለምሳሌ አንድ ዘፈን አለ የሻምበል በላይነህ ዘፈን...
ወልቃይት ጠገዴ፤ ሰሜን አርማጭሆ ዳንሻና ሁመራ
ሰውም ጎንደሬ ነው መሬቱም ያማራ ..ብሎ የሚዘፍነው ዘፈን አለ ይሄ ዘረኝነት ሊያስብለው አይችልም።
.
.
.
ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን እንዴት ታየዋለህ...??

ኢትዮጵያ painting ናት ለኔ። ኢትዮጵያን ስንስላት 80 ቀለሞችን ቀላቅለን ነው የምንስላት። እነዛ 80 ቀለሞች የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ናቸው። ለኔ ኢትዮጵያዊነት የ80 ብሄር ብሄረሰቦች ቅልቅል ውጤት ናት። በኢትዮጵያዊነቴ ማንም ሰው አንተ ኢትዮጵያን አትወድም አንተ ኢትዮጵያን ትወዳለህ ሊለኝ አይችልም። #ምክንያቱም ቅድመ አያቴ ቦንሲቱቃበታ ከዚህ #መቀሌን ነፃ ለማውጣት በእግሯ ስትጓዝ ኦሮሞ እዛ ስላለ አይደለም። እኔ የአያቴ አስክሬን ሲሸ ኝ አውቃለሁ ሲፎከርላት የነበረው በፈረስ .."ቦንሲቱ ጋፋ መቀሌ እየተባለ ቦንሲቱ ያኔ በመቀሌ ጊዜ..." እየተባለ ሲፎከርላት ነው አስክሬና ሲሸኝ የነበረው።

በህይወት የሌሉ ቅድመአያቶቼ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለማስከበር አጥንታቸውን ከስክሰዋል።

ማንም ሰው ሀጫሉ #በኢትዮጵያዊነቱ ላይ እንደዚህ ያለ አቋም አለው የለውም የሚል መብት የለውም ምክንያቱም እኔ ስለማውቀው። ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው። ምክንያቱም 80 ቀለም ስላለው።
.
.
ስጋት አለኝ ስጋቴ ምንድነው ...ድሮ መንግስት ሀላፊነቱን ይረሳና ጡንቻውን የሚያሳይበት ነበር። ያን ነገር ምስኪን ህዝብ ለመቀየር ይሄ ነው የማይባል መስዋትነት ከፍሏል። ከከፈለ በኋላ አሁን ይመስለ ኛል በተወሰነ መልኩ ባልተጠበቀ መንገድ ህዝባዊነት የሚታይበት ነገር አለ ስጋቴ ምንድ ነው ይሄን መንግስት መያዝ እንዳያቅተው ነው ስጋቴ። ጥንቃቄ እንደሚፈልግ እና በጥንቃቄ ማየት እንዳለበት።
.
.
በቀጣይ ስለ ሚሰራው ስራዎች...??

አሁን ከመንግስት ትወርጅና ደግሞ misunderstanding ተፈጥሮ ልዩነት ማስፋት ሳይሆን በማጥበብ ሀገርን ማኖር እንደሚቻል #በመከባበር አንዱ ያንዱን ሀሳብ ለማድመጥ በመዘጋጀት በመተማመን፣ በመነጋገር አብሮ ለመኖር እንደሚቻል የሚያሳዩ ስራዎችን ለመስራት ነው ወደፊት የማስበው።
.
.
ጎንደር ተውልከድ ወይም መቀሌ ተወልደክ ቢሆን ኖሮ የአሁኑን አይነት ሰው ትሆን ነበር??

#ጎንደሬነቴ ክብሬ ነው! ማለቴ አይቀርም..
.
.
.
ከሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን ምን ተማርክ?
(ሀጫሉ የኢትዮጵያ ባለውለታው ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን ዘመንድ እንደሆነ ይታወቃል)
.
.
ኢትዮጵያዊነታቸውን እና ኦሮሞነታቸውን እንዴት እንዳካሄዱት ነው የተማርኩት።
.
.
.
ለኢትዮጵያ ህዝብ ምን ሙዚቃ ትጋብዛቸዋለህ??

.ጂራ...ጂራ...ጂራ...(የራሱን ሙዚቃ)
.
.
.
የነዋይ ደበበ - የክብሬ መመኪያ (በራሱ ድምፅም ትንሽ አንጎራጉሯታል)

የክብሬ መመኪያ ደስታና ህይወቴ
ሌላ ምን ሀብት አለኝ ሀገሬ ናት ሀብቴ
እሰይ እሰይ ...ዛሬም እሰይ ነገም እሰይ
#ኢትዮጵያ እምዬ...

ሀጫሉ ሁንዴሳ ከፋና ብሮድክስቲንግ FM 98.1 ጋር በነበረው ቆይታ!

ማሳሰቢያ ከይቅርታ ጋር፦ ምናልባት የቃላት ስህተት አፃፃፍ ላይ ካለ እርማት ስጡበት።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጉዞ ሉሲ~ለሰላምና ለፍቅር!

‹‹ጉዞ ሉሲ ለሰላምና ለፍቅር መርሀ-ግብር›› ትላንት ምሽት በሚሊኒዬም ተጀምሯል፡፡ በዝግጅቱ መክፈቻ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢፌዴሪ ባሕልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር #ሂሩት_ካሰው ‹‹ዘረኝነት፣ መለያዬት፣ ማግለልና ንፉግነት የኛ የኢትዮጵያዊነት ባሕል አይደለም፡፡ ከዛሬ ጀምሮ የነበረንን መተዛዘን፣ #ፍቅርና #አንድነት ወደ ነበረበት እንዲመለስ ለውጥ የሚጀምረው ከራስ ነውና ለለውጥ እዘጋጃለሁ፤ ለለውጥ እንዘጋጅ›› በሚል #የአንድነት ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

በመርሀ-ግብሩ ከአፋር ክልል ጀምሮ በተለያዩ ክልሎች ሉሲ የአምስት ቀናት ቆይታ እያደረገች ሕዝቡ #በአንድነቱ ዙሪያ እንደሚወያይ የገለጹት ሚኒስትሯ ‹‹ሉሲንና ሌሎች አንድ የሚያደርጉን በዩኔስኮ የተመዘገቡ ቅርሶችን በታላቅ ክብር ከብሔራዊ ሙዚዬም ወደ ፓርላማ አጓጉዘን ወደ አፋር በመሸኘት ይጀመራል›› ነው ያሉት፡፡

ሉሲ የእገሌ የሚባል ሃይማኖት፣ ብሔር፣ አስተሳሰብ ወይም ሌላ #ወካይ_ያልሆነች የሁሉም የሰው ዘር ግንድ መሆኗን የጠቀሱት ሚንስትሯ ‹‹ደግነትና አብሮነት ስላልተለየን በጎ ትሩፋት ሳይሠራ የሚውል #ኢትዮጵያዊ የለም፡፡ የትኛውም ኢትዮጵያዊ የተራበ ሳያበላ፣ የተጠማ ሳያጠጣ፣ የወደቀ ሳያነሳ፣ የሞተ ሳይቀብር አይውልም፤ ኢትዮጵያዊነትም ይህ ነው›› ብለዋል፡፡ እንኳን እርስ በእርስ ከሌላውም ዓለም ጋርም ኢትዮጵያዊ በሉሲ የተዛመደ መሆኑንና #ዘረኝነት የኢትዮጵያዊነት ባሕል አለመሆኑን ነው ዶክተር ሂሩት ያስገነዘቡት፡፡

በመርሀ-ግብሩ መክፈቻ ዝግጅት በአዲስ አበባ ሚሊኒዬም አዳራሽ አንጋፋና ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ዝግጅቶቻቸውን አቅርበዋል።

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ👆

ዘረኝነትን #እጠየፋለሁ፤ ከተማዬን አፀዳለሁ! #ETHIOPIA #ኢትዮጵያ #ቡሌሆራ #ዘረኝነት ቆሻሻ ነው!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ኢትዮጵያ ከተለወጠች የምትለወጠው በትጉ አይነት ሰራተኛ ልጆቿ ነው ። የነገዋ ኢትዮጵያ ልታምር የምትችለው #ከጥላቻና #ዘረኝነት ይልቅ የስራ ባህልን ለልጆቻቸው ባወረሱ ቅን ወላጆች ነው።" Mesued M.

መልካም ቀን ይሁንልን!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EOTC ብፁዕ አቡነ አብርሃም ምን አሉ ? - በዓለ ጥምቀቱን ለማክብረ በመንግሥት ዘንድ ቤተክርስቲያን ይሄን ትበል ፣ አለበለዚያ እንዲህ አይደለም የሚሉ መልዕክቶች ደርሰውናል። - ቤተክርስቲያን ሰላሟን ታውጃለች። - አሉ አሉ እየተባሉ ስለተነገሩ ንግግሮች እና ግለሰቦች፣ ጳጳሳት እና ሊቃነጳጳሳት ከሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ታያለች፣ ትመክራለች ታስተምራለች። ህግ አላት በህጓ መሰረት ትገስፃላች። ከዚህ…
#EOTC

" ሀገራችን ሰላም ትሁን፤ የሃይማኖት ሰዎች እንደ ሃይማኖት እናስብ፣ እንደ ሃይማኖት እንናገር፣ አላስፈላጊ ጀግንነትን እንርሳው " - ብፁዕነታቸው

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ምን አሉ ?

- የማይደፈር ሲደፈር አይተናል፤ ቤተክርስቲያን ስትደፈር ዝም አንልም።

- " ፖለቲካው የፖለቲካው መስመር ሲደፈር ዝም እንደማይል ሁሉ እኔም ደግሞ የመጀመሪያዋም የመጨረሻዋም ህይወቴም ማንነቴም ክብሬም ቤተክርስቲያኔ ስለሆናች እሷ ስትደፈር ዝም አልልም። እናገራለሁ፤ የመጣውን በፀጋ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ "

- ከዚህ በፊት ለመንግሥት ችግር ካለ እዚህ ጠቅላይ ቤተክህነት ውስጥ ንገሩን ብለናቸዋል። እኛ እናርማለን፣ እኛው እናስተካክላለን፣ አላስፈላጊ እርምጃ አትውሰዱ ብለናቸዋል። ትላንት ግን ከቤተክህነት የሚወጣው በሙሉ ይፈተሻል ዛሬም፣ የሚወጣ መኪና በሙሉ ይፋተሻል፤ የሚገባው ግን አይፈተሽም። የሚገባውን የኛ ዘበኞች ይፈትሹ ይሆናል፤ የመንግሥት ወታደሮች ግን አይፈትሹም። አንዱ ሌላ ነገር ይዞ ገብቶ ሲወጣ ፈታሹ ሌላ ነገር ይዞ ተብሎ የቤተክርስቲያን ስም እና ክብር ቢዋረድ ማነው ኃላፊው?

- ምንድነው የተፈለገው? ከቤተክርስቲያን ምንድነው የሚወጣው? መድፍ ነው? መሳሪያ ነው? አከፋፋይ ናት ቤተክርስቲያኒቱ? አትታመንም? መንግሥትን ያስጮኸ ነገር አለ እኛም የጮህንበት ከመንግስት በፊት፤ ግለሰቦችን ስለተናገሩት ንግግር የማይባል ተብሏል እያልን እኛ ነን የጮህን ይሄ የቤተክርስቲያን ቋንቋ አይደለም ብለን ነበር፤ መግለጫ ለመስጠት ተዘጋጅተን ነበር መንገዱን ስናየው መጠላለፊያ እንጂ ከፅድቅ ስላልሆነ ነው ዝም ያለነው። የፅድቅ ሲሆን ገፍተን ነው የምንወጣው።

- ከቤተክህነት ምንድነው የሚወጣው ? ከተፈለገ መባል ያለበት ጥርጣሬ አለን ቤተክህነት ውስጥ ይባላል፤ እንዲህ አይነት ነገር ቢወጣ ኃላፊነቱ የናተ ነው ጠብቁ ነው ልንባል የሚገባው ወይም ሰው እንሥጣችሁ የሚያንሳችሁ ከሆነ ቤተክርስቲያኒቱን እንዳያስወቅስ ነው መባል ያለበት እንጂ ቤተክርስቲያን የማትታመን ሆነ ከትላንት ጀምሮ እስካሁን እኛ መሪዎቹ በማናውቀው ፈታሽ በር ላይ ቆሞ መፈተሽ ድፍረት ነው። ቤተክርስቲያኒቱን ህልውናዋን መፈታተን ነው። አቅሟንም መፈትን ነው ተገቢ አይደለም።

- መደፋፈሩ በዝቷል፤ መንግስትም ቤተክርስቲያኒቱን ይደፍራል አልፎ ይሄዳል።

- እንደ ግለሰብ በስሜት የሚናገሩ ሰዎች ይኖራሉ። ቤተክርስቲያኒቱን መድፈር አዳጋ ነው። ለሃይማኖቱ የማይሞት የለም፣ ከዚህ በፊት ብዙዎች ሞተዋል፤ ተከባብረን እንኑር ለሰላም እንኑር።

- ካህን ነው ሲሉት ሌላ ነጭ ለባሽ ይሆናል፣ ነጭ ለባሽ ነው ሲሉት ካህን ሆኖ ይገኛል፤ የቤተክርስቲያን መሪ ነው ሲሉት የፖለቲካ መሪ ሆኖ ይገኛል፤ የፖለቲካ መሪ ሲሉት ቀዳሽ ሆኖ ይገኛል ምን አመጣው ይሄን ቀጥ ብለን እንቁም። ደሃ ሲበደል ተበደለ እንበል ሲታሰር ፍቱ እንበል፤ እያልን ነው እኮ፤ መንግሥትን ፍቱ እያልን እንመካከራለን ይፈታል ለዚህ ደግሞ እናመሰግናለን።

- በሃይማኖት ጉዳይ አንደራደርም።

- ካህን ካህን ይሁን፣ ወታደርም ወታደር ይሁን ሌላውም እራሱን ይሁን በሚያስተሳስረን ነገር ተሳስረን ጥላቻና ሁከትን፣ ሽብርና አላስፈላጊ ነገርን እናርቅ።

- ካላስፈላጊ #ጎጠኝነት#ዘረኝነት እንራቅ።

- ሀገራችን ሰላም ትሁን የሃይማኖት ሰዎች እንደ ሃይማኖት እናስብ፣ እንደ ሃይማኖት እንናገር፣ አላስፈላጊ ጀግንነትን እንርሳው። አላስፈላጊ ሙገሳንም እንርሳው። ካላስፈላጊ ሙገሳ አስፈላጊ በሆነ ወቀሳና ለመጨረሻው መከራ እራሳችንን እናዘጋጅ።

ያንብቡ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-12-2

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia