TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሀጫሉ_ሁንዴሳ ከፋና ጋዜጠኛ ጋር በነበረው ቆይታ በርካታ ጥያቄዎች ተነስተውለት መልሷል።

እኔም ዝግጅቱን ከሰማው በኋላ የአቅሜን ከዚህ በታች በፅሁፍ አስቀምጬዋለሁ።
.

ጥቂት ስለ ጂራ...?

ጂራ ማለት አለን ማለት ነው። የህዝቡን ስነ ልቦና ስታይው አለን የሚያስብል ነው።... ጂራ ኤርትራም ገብቷል። ህዝብ ተለያይቶ አይለያይም። ኤርትራዊያንም ጂራ ገብቷቸዋል ማለት ነው።
.
.
ስለ ስሙ...??

ሀጫሉ ማለት "ይብለጥ" ማለት ነው። አባቴ በልጅነቴ ፈጣን እና ንቁ ስለነበርኩ ያወጣልኝ ስም ነው። እኔ ከማንም እበልጣለሁ ብዬ አላስብም።"
.
.
ስለ ዶክተር አብይ...??

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ የሀገራችን ህዝቦች ዴሞክራሲ ምን እንደሚመስል ያዩ ይመስለኛል። ባልተለመደ መልኩ የሰው ልጅ የተሰማውን በአደባባይ እንደፈለገ እንዲናገር ...ከሀገራችን ህዝብ አምዕሮ በላይ የሆኑ ነገሮች ታይተዋል።

#ግን ህዝባችን ለመላመድ ጊዜ የሚያስፈልገው ይመስለኛል። ሲረገጥ፣ ሲጨቆን፣ ሲበደል የነበረ ህዝብ በአንድ ጊዜ እንደዚህ ፈሪሀ እግዚያቤር ያለው መሪ መጥቶ #እንደፈለክ ሁን ሲለው ያን እራሱ እንዴት አድርጎ መሆን እምደሚችል ላያቅበት ይችላል።

በአጠቃላይ ጥንቃቄ ያስፈልጋል ከመንግስትም ከህዝብም እንጂ በሂደት የሚስተካከል ይመስለኛል።
.
.
.
ስለ ሀምሌ 7 የሚሊኒየም አዳራሽ ዝግጅት...?

እኔ እንደዛን ዕለት ቦታና ወቅቱን መርጬ ያስተላለፍኩት መልዕክት ያለም አይመስለኝም። ጠቅላይ ሚንስቱር ግና እንደተመረጡ ...እያንዳንዱን በየፕሮፌሽኑ ልምድ ሲሰጡ ነበር አርቲስቱንም እንደዛው የህዝባችሁን ጩኸት አሰሙ ያመናችሁበትን ስሩ ብለው ነው የመከሩት። የሳቸው ምክር More ጉልበት ሆኖኛል። እኔ የዛን ቀን ምንም ሀጢያት አልሰራሁም። እኔ ኢትዮጵያ የማውቃት #አዲስ_አበባ ብቻ አይደለችም። ምናልባት ድግስ ሊኖር ይችላል አዲስ አበባ ላይ ...መተማ ላይ ኢትዮጵያዊ ከሞተ ኢትዮጵያዊ እየሞተ ነው ብሎ address ማድረግ ..ሀረር ላይ ኢትዮጵያዊ ከሞተ ኢትዮጵያዊ እየተገደለ ነው ስለዚህ መንግስት አንድ ነገር ማድረግ አለበህ ብሎ በጥበብ መልክ ለማስተላለፍ እኔ ቦታው ነው ቦታው አይደለም ብሎ ማሰብ ተገቢ ነው ብዬ አላምንም። እንግዳን መናቅ አይመስለኝም።
.
.
ሀጫሉ ዘረኛ ነው ይሉሀል??

#ዘረኛ ነህ ካልሽኝ ዘረኛ #አደለሁም። እኔ ያሳደገኝ እና የወጣሁት ከኦሮሞ ማህበረሰብ ነው። በኦሮሞ ማህበረሰብ #ዘረኝነት ይኮነናል። በገዳ ስርዓት ውስጥ ዘረኝነት ይኮነናል። ዘረኛ መሆንም #አልችልምዘረኛ ብሆን ኢንተቪው የምናደርገው በአስተርጓሚ ነው።

አፌን የፈታሁት በኦሮሚኛ ነው። ዘረኛ ስላልሆንኩ ነው በአማርኛ የማወራው። ለሌላውም ቋንቋ አድናቆት እና ክብር አለኝ።

በምን አይነት መልኩ ተረድተውኝ እንደዚህ እንዳዚህ እንዳሉኝ ሊገባኝ አይችልም። ምናልባት የሚመስለኝ እሱ የሚዘፍነው ኦሮሞ...ኦሮሞ...ኦሮሚያ እያለ ነው የሚል ከሆነ ኦሮሞና ኦሮሚያ ከኢትዮጵያ ውጭ አይደሉም። ኦሮሞ ሆኜ ስለ ሱዳን እና ስለ ኬንያ ብዘፍን ነው የሚያስወቅሰኝ። ለምሳሌ አንድ ዘፈን አለ የሻምበል በላይነህ ዘፈን...
ወልቃይት ጠገዴ፤ ሰሜን አርማጭሆ ዳንሻና ሁመራ
ሰውም ጎንደሬ ነው መሬቱም ያማራ ..ብሎ የሚዘፍነው ዘፈን አለ ይሄ ዘረኝነት ሊያስብለው አይችልም።
.
.
.
ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን እንዴት ታየዋለህ...??

ኢትዮጵያ painting ናት ለኔ። ኢትዮጵያን ስንስላት 80 ቀለሞችን ቀላቅለን ነው የምንስላት። እነዛ 80 ቀለሞች የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ናቸው። ለኔ ኢትዮጵያዊነት የ80 ብሄር ብሄረሰቦች ቅልቅል ውጤት ናት። በኢትዮጵያዊነቴ ማንም ሰው አንተ ኢትዮጵያን አትወድም አንተ ኢትዮጵያን ትወዳለህ ሊለኝ አይችልም። #ምክንያቱም ቅድመ አያቴ ቦንሲቱቃበታ ከዚህ #መቀሌን ነፃ ለማውጣት በእግሯ ስትጓዝ ኦሮሞ እዛ ስላለ አይደለም። እኔ የአያቴ አስክሬን ሲሸ ኝ አውቃለሁ ሲፎከርላት የነበረው በፈረስ .."ቦንሲቱ ጋፋ መቀሌ እየተባለ ቦንሲቱ ያኔ በመቀሌ ጊዜ..." እየተባለ ሲፎከርላት ነው አስክሬና ሲሸኝ የነበረው።

በህይወት የሌሉ ቅድመአያቶቼ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለማስከበር አጥንታቸውን ከስክሰዋል።

ማንም ሰው ሀጫሉ #በኢትዮጵያዊነቱ ላይ እንደዚህ ያለ አቋም አለው የለውም የሚል መብት የለውም ምክንያቱም እኔ ስለማውቀው። ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው። ምክንያቱም 80 ቀለም ስላለው።
.
.
ስጋት አለኝ ስጋቴ ምንድነው ...ድሮ መንግስት ሀላፊነቱን ይረሳና ጡንቻውን የሚያሳይበት ነበር። ያን ነገር ምስኪን ህዝብ ለመቀየር ይሄ ነው የማይባል መስዋትነት ከፍሏል። ከከፈለ በኋላ አሁን ይመስለ ኛል በተወሰነ መልኩ ባልተጠበቀ መንገድ ህዝባዊነት የሚታይበት ነገር አለ ስጋቴ ምንድ ነው ይሄን መንግስት መያዝ እንዳያቅተው ነው ስጋቴ። ጥንቃቄ እንደሚፈልግ እና በጥንቃቄ ማየት እንዳለበት።
.
.
በቀጣይ ስለ ሚሰራው ስራዎች...??

አሁን ከመንግስት ትወርጅና ደግሞ misunderstanding ተፈጥሮ ልዩነት ማስፋት ሳይሆን በማጥበብ ሀገርን ማኖር እንደሚቻል #በመከባበር አንዱ ያንዱን ሀሳብ ለማድመጥ በመዘጋጀት በመተማመን፣ በመነጋገር አብሮ ለመኖር እንደሚቻል የሚያሳዩ ስራዎችን ለመስራት ነው ወደፊት የማስበው።
.
.
ጎንደር ተውልከድ ወይም መቀሌ ተወልደክ ቢሆን ኖሮ የአሁኑን አይነት ሰው ትሆን ነበር??

#ጎንደሬነቴ ክብሬ ነው! ማለቴ አይቀርም..
.
.
.
ከሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን ምን ተማርክ?
(ሀጫሉ የኢትዮጵያ ባለውለታው ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን ዘመንድ እንደሆነ ይታወቃል)
.
.
ኢትዮጵያዊነታቸውን እና ኦሮሞነታቸውን እንዴት እንዳካሄዱት ነው የተማርኩት።
.
.
.
ለኢትዮጵያ ህዝብ ምን ሙዚቃ ትጋብዛቸዋለህ??

.ጂራ...ጂራ...ጂራ...(የራሱን ሙዚቃ)
.
.
.
የነዋይ ደበበ - የክብሬ መመኪያ (በራሱ ድምፅም ትንሽ አንጎራጉሯታል)

የክብሬ መመኪያ ደስታና ህይወቴ
ሌላ ምን ሀብት አለኝ ሀገሬ ናት ሀብቴ
እሰይ እሰይ ...ዛሬም እሰይ ነገም እሰይ
#ኢትዮጵያ እምዬ...

ሀጫሉ ሁንዴሳ ከፋና ብሮድክስቲንግ FM 98.1 ጋር በነበረው ቆይታ!

ማሳሰቢያ ከይቅርታ ጋር፦ ምናልባት የቃላት ስህተት አፃፃፍ ላይ ካለ እርማት ስጡበት።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በጋና የአክራ ዩኒቨርሲቲ በቅጥሩ ይገኝ የነበረውን የማህተመ ጋንዲን ሀውልት #አፈረሰ። ሃውልቱ የፈረሰው የዩኒቨርሲቲው አንድ ፕሮፌሰር ጋንዲ #ዘረኛ ነበሩ በማለት ሃውልቱ እንዲፈርስ ፊርማ ማሰባሰባቸውን ተከትሎ ነው። ምንም እንኳ ጋንዲ አገራቸው ህንድ ከእንግሊዝ አስተዳደር ነፃ እንድትወጣ ባደረጉት ትግል የነፃነት ተምሳሌት ቢሆኑም ስለ አፍሪካዊያን የተናገሯቸው ነገሮች ለብዙዎች አወዛጋቢ ናቸው።

©BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom #WHO #DonaldTrump

ትላንት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ለWHO የምትሰጠውን ከፍተኛ ገንዘብ እንደምታቅብ ተናገረዋል። የዓለም የጤና ድርጅት ኮቪድ-19 የዓለም አቀፍ ወረርሽኝ መሆኑን በጊዜ አልተናገረም ብለዋል ፕሬዘዳንቱ።

ድርጅቱ ይህን ያደርገው በሽታው ለተጀመረባት #ቻይና ሲል ሊሆን ይችላል ሲሉ ግምት አዘል አነጋገር ተናግረዋል። "በጣም ቻይና ተኮር ይመስላሉ ፣ ይህን ማጤን ይኖርብናል' ሲሉ ተደምጠዋል ዶናልድ ትራምፕ።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ወረርሽኝ ባለበት በዚህ አይነት ሁኔታ ለጤናው ድርጅት /WHO/ የሚዋጣ ገንዘብ መከልከ ተገቢ ነው ወይ? ተብለው ከጋዜጠኛ የተጠየቁት ትራምፕ 'እኔ አንሰጥም አላልኩም፣ እናጤነዋለን ነው ያለኩት' ሲሉ መልሰዋል።

ከፍተኛ ዘመቻ እየተካሄደባቸው የሚገኙት የዓለም የጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ዛሬ በሰጡት ዕለታዊ መግለጫቸው ላይ የግድያ ዛቻ እንደደረሰባቸው ፤ እሳቸው ግን ግድ እንዳልሰጣቸው ተናግረዋል። በማን ይህ ሊደረግ እንደቻለ ግን አልተናገሩም።

ከሁለት (2) እና ከሦስት (3) ወር በላይ #ዘረኛ ጥቃቶች ተሰንዝረውብኛል ያሉት የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴድሮስ 'ጥቁር ተብያለሁ። እውነቱን ለመናገር እኔ በጥቁርነቴ እኮራለሁ። የሚባለው ነገርም ግድ አይሰጠኝም' ሲሉም ተደምጠዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ፣ ቪኦኤ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#DonaldTrump

"የዓለም ጤና ድርጅት /WHO/ ቻይና በአፍሪካዊያን ላይ የፈጸመችውን ዘረኛ ድርጊት ችላ ብሏል" - ዶናልድ ትራምፕ

(በቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት)

የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በቻይናዋ ደቡባዊ ከተማ ጉዋንዡ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መቀስቀሱን ተከትሎ በአፍሪካዊያን ላይ ሲፈጸም ለነበረው ዘረኛ ድርጊትና መድልዎ የዓለም ጤና ድርጅት ጠንካራ ምላሽ አልሰጠም ሲሉ ትችት ሰንዝረዋል፡፡

ትራምፕ ለድርጅቱ ኃላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በጻፉት ደብዳቤ ላይ አፍሪካዊያን በግድ ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ ፣ ከመኖሪያቸው እንዲባረሩ ፣ እንዲሁም አገልግሎት እንዳያገኙ ማድረግን ጨምሮ ዘረኛ እና አድሎአዊ ድርጊት ደረሰብን ቢሉም፤ ድርጅቱ በቻይና #ዘረኛ ድርጊት ላይ አስተያየት አልሰጠም ሲሉ ከሰዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia