TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Situation_Report_Northern_Ethiopia_Humanitarian_Update_19_Feb_2022.png
406.8 KB
#UNOCHA

PDF የሰሜን ኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰብዓዊ ድጋፍ ሁኔታ ሪፖርት።

@tikvahethiopia
Situation_Report_Northern_Ethiopia_Humanitarian_Update_3_Mar_2022.pdf
3.1 MB
#UNOCHA

PDF የሰሜን ኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰብዓዊ ድጋፍ ሁኔታ ሪፖርት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Situation_Report_Northern_Ethiopia_Humanitarian_Update_3_Mar_2022.pdf
#SituationReport

#Tigray #Amhara #Afar📍

የሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ የተመድ ሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ የዚህን ሳምንት ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።

ዋና ዋና ነጥቦች ፦

#Afar📍

- በአፋር ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች ያለው ሁኔታ ተባብሶ ቀጥሏል። በተለይም በራህሌ፣ ኢሬብቲ፣ ኬልቤቲ ዞን (ዞን 2) ውስጥ የትጥቅ ግጭቶች መኖራቸው ሪፖርት ተደርጓል።

- በአፋር እየተካሄደ ያለው ግጭት የሰብአዊ ድጋፍ መርሃ ግብሮችን እያደናቀፈ ፤ የሲቪሎችን ህይወት፣ ደህንነታቸውን አደጋ ላይ እየጣለ እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የሚሄደው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥርም የሰብአዊ ፍላጎቶችን እየጨመረው ይገኛል።

- በአፋር ክልል ዞን 4 መረጋጋት በመፈጠሩ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የውስጥ ተፈናቃዮች ወደ ቀደመው ቀያቸው ተመልሰዋል።

- በዞን 2 በቀጠለው ግጭት ምክንያት ተጨማሪ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው መፈናቀላቸውን የክልሉ ባለስልጣናት አሳውቀዋል። ተፈናቃዮቹ በተለይም ከአባላ፣ ኢረብቲ፣ በረሃሌ፣ መጋሌ እና ዳሎል ወረዳዎች መሆናቸው ተገልጿል። አብዛኞቹ ተፈናቃዮች በአሁኑ ወቅት በዳሎል፣ አፍዴራ፣ ሲልሳ/ጉያህ እና ሰመራ እየተጠለሉ ሲሆን አንዳንድ ተፈናቃዮች ደግሞ ራቅ ባሉ እና ለመድረስ አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ነው ያሉት።

- የተመድ አጋሮች በተደራሽነት ውስንነት ምክንያት በዞን 2 የሚገኙትን የተፈናቃዮች ቁጥር ማረጋገጥ አልቻሉም።

- ቁጥራቸው ያልተረጋገጠ ከአፋር የተፈናቀሉ ተፈናቃዮች በትግራይ ክልል በሚገኙ ጥቂት ትምህርት ቤቶች ይገኛሉ።

#Tigray 📍

- አሁን ላይ የ ሰመራ - አብአላ - መቐለ መስመር መዘጋት ወደ ትግራይ የሚደርሰውን የሰብአዊ አቅርቦት የበለጠ አባብሶታል። ሰብዓዊ አቅርቦቱ ከታህሳስ አጋማሽ በፊት ከተፈቀደው ውስን አቅርቦት ጋር ተዳምሮ በዋነኛነት ቀደም ባሉት አስተዳደራዊ ርምጃዎች ምክንያት ሰብዓዊ አቅርቦቱ ከሚያስፈልገው በታች ነበር።

- እኤአ ከሃምሌ 12 ጀምሮ አስፈላጊውን የሰብአዊ አቅርቦት ከያዙ 16,500 የጭነት መኪናዎች ውስጥ 8 በመቶው ብቻ ትግራይ ገብተዋል። በዚህም የተመድ ሰብአዊ አጋሮች ተግባራቸውን መቀነሳቸውን ቀጥለዋል።

- ይህ ሪፖርት በተዘጋጀበት በዚህ ሳምንት የሰብአዊ ድጋፍ አድራጊ ድርጅቶች 47 ሜትሪክ ቶን የህክምናና የስነ ምግብ አቅርቦቶችን ወደ ትግራይ ክልል መዲና መቐለ በበረራ አድርሰዋል። ይህ እኤአ ከጥር 24 አንስቶ በበረራ ወደ ትግራይ የገባውን አጠቃላይ አቅርቦት 144 ሜትሪክ ቶን አድርሶታል።

- በዚህ ሳምንት ወደ ትግራይ ከቀረበው አቅርቦት መካከል 10 ሜትሪክ ቶን የተመጣጠነ ምግብ (Ready to Use Therapeutic Food - RUTF) ይገኝበታል። ይህም ከታህሳስ አጋማሽ ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የገባ ሲሆን በመቐለ፣ በምስራቅ እና ደቡብ-ምስራቃዊ ዞን ይከፋፈላል። ከፍተኛ የሆነ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ያለባቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናትን ለመንከባከብ ይውላል።

- ባለፉት ሳምንታት ወደ መቐለ የደረሱ የህክምና ቁሳቁሶች ይህ ሪፖርት በተዘጋጀበት ሳምንት ወደ ምስራቅ ዞን ውቅሮ እና ዓዲግራት አጠቃላይ ሆስፒታሎች፣ ወደ ማዕከላይ ዞን ዓድዋ፣ አክሱም፣ አቢአዲ ጠቅላላ ሆስፒታሎች እና አክሱም ሪፈራል ሆስፒታል፣ በሰሜን ምዕራብ ዞን ወደ ስሁል ሽሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ተከፋፍለዋል።

- አሁንም የነዳጅ እጥረት ቀሪዎቹን ቁሳቁሶች ለማከፋፈል እንቅፋት እንደሆነ ነው።

- በትግራይ አሁንም የህክምና ቁሳቁሶች ችግርና የተወሰኑ አይነት መድሃኒት እጥረቶች ያሉ ሲሆን ከነዚህም መካከል HIV ላለባቸው ሰዎች ሚሰጥ መድሃኒት ይጠቀሳል፣ የHIV መመርመሪያ ኪት፣ የፀረ ራቢስ መድሃኒት፣ የኮሌራ ክትባት እጥረትም አለ።

#Amhara 📍

- በአማራ ክልል አንዳንድ ' ከትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች ' አሁንም ተደራሽ አይደሉም። በተለይም በሰሜን ጎንደር ፣ ዋግ ኽምራ እና ሰሜን ወሎ ዞኖች ያሉ አካባቢዎች እጅግ አሳሳቢ ሲሆኑ አልፎ አልፎ በሚከሰቱት ግጭቶች ምክንያት ሰዎች ወደ ዝቋላ ፣ ሰቆጣ ፣ ቆቦ እና ዛሪማ መፈናቀላቸውን የሚገልፁ ሪፖርቶች አሉ።

- በሰቆጣ እና ዝቋላ ከ40 ሺ በላይ ተፈናቃዮች እንደሚኖሩ ይገመታል።

- በአማራ ክልል በዘጠኝ ዞኖች እኤአ ከታህሳስ እስከ ጥር ባለው ጊዜ ውስጥ በ " Find -and - Treat " ዘመቻ ከ1 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ህጻናትን የመለየት ዘመቻ የተካሄደ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 21,804 ህጻናት ወይም 1.1 በመቶው ህጻናት በከፋ የምግብ እጥረት (SAM) ተጠቅተዋል።

- በምስራቅ አማራ እ.ኤ.አ. ከየካቲት 14 ጀምሮ በመካሄድ ላይ ባለው 'find and treat' ዘመቻ እስካሁን ምርመራ ከተደረገላቸው 293,208 ከ5 አመት በታች ህጻናት 8,160 SAM ኬዝ ወይም 2.7 በመቶና 48,118 GAM ኬዞች ወይም 16.4 በመቶ ተገኝቷል። ምርመራ ከተደረገላቸው 52,828 ነፍሰጡር እና የሚያጠቡ እናቶች ውስጥ 21,687 ሴቶች ወይም 41 በመቶው የተመጣጠነ ምግብ እጥረት አለባቸው ተብሏል።

#UNOCHA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ስጋት ፈጥሮብናል " - ኤምባሲዎቹ ሰሞነኛውን የሰሜን ኢትዮጵያን ጉዳይ አስመልክቶ በአዲስ አበባ የሚገኙት ፦ - የካናዳ፣ - የፈረንሳይ፣ - የጀርመን፣ - የጣሊያን፣ - የጃፓን፣ - የእንግሊዝ እና የአሜሪካ ኤምባሲዎች የጋራ አጭር መግለጫ አውጥተዋል። በዚህም ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ " #አወዛጋቢ " በሆኑት አካባቢዎች ከሰሞኑን የተፈጠረው ግጭት " ስጋት ፈጥሮብናል " ብለዋል። ሁሉም ወገኖች የታጣቂ…
#Raya #UNOCHA

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ዛሬ ባወጣው ሪፖርት 29,000 ሰዎች ከአላማጣ ገጠራማ አካባቢዎች ከቤታቸው ተፈናቅለው ፦
° በቆቦ / በሰሜን ወሎ
° ሰቆጣ / በዋግኽምራ በሚገኙ መጠለያዎች መጠለላቸውን ገልጿል።

23,000 ሰዎች ወደ ቆቦ ሰሜን ወሎ እንዲሁም 5,980 ሰዎች ወደ ሰቆጣ ዋግኽምራ ዞን ነው የተፈናቀሉት።

በአካባቢው ያለው ሁኔታ ሲታይ የተፈናቃዮች ቁጥር ከዚህ ሊጨምር እንደሚችል አመልክቷል።

ከተፈናቀሉት ዜጎች በዋነኝነት 70 በመቶዎቹ ህጻናትና ሴቶች ሲሆኑ ቀሩት ደግሞ አዛውንቶችና ታዳጊዎች ናቸው።

እንደ UN OCHA ሪፖርት ፦

🔘 ተፈናቃዮች ባሉበት ከበድ ያለ #የምግብ እና የውሃ እጥረት በመኖሩ አስቸኳይ የሆነ የህይወት አድን እርዳታ ያስፈልጋል።

🔘 ክፍት በሆኑ ቦታዎች ላይ የተጠለሉ ቤተሰቦች አስቸኳይ መጠለያ ያስፈልጋቸዋል።

ኦቻ ድጋፍ በሚያደርጉ #አጋር_አካላት የግብዓት እጥረት ምክንያት በጣም ተጋላጭ ለሆኑት የምግብ እና ውሃ ድጋፍ እየተደረገ ያለው መደበኛ ባልሆነ መንገድ በህብረተሰቡ ነው ብሏል።

ተጨማሪ ፦

🛑 እስከ ትላንት ድረስ በራያ አላማጣ ገጠራማ አካባቢዎች ላይ አንዳንድ መጠነኛ #ግጭቶች መከሰታቸውን ቢቀጥልም በአላማጣ ፣ ቆቦ ፣ ወልዲያ ከተሞች የጸጥታ ሁኔታው ​የተረጋጋ ነው።

⭕️ በአላማጣ እና በቆቦ መካከል ያለው መንገድ ተከፍቶ የንግድ ትራንስፖርት የቀጠለ ሲሆን እንደ ባንኮች ያሉ የህዝብ አገልግሎቶች ቀስ በቀስ ቀጥለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Raya #UNOCHA የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ዛሬ ባወጣው ሪፖርት 29,000 ሰዎች ከአላማጣ ገጠራማ አካባቢዎች ከቤታቸው ተፈናቅለው ፦ ° በቆቦ / በሰሜን ወሎ ° ሰቆጣ / በዋግኽምራ በሚገኙ መጠለያዎች መጠለላቸውን ገልጿል። 23,000 ሰዎች ወደ ቆቦ ሰሜን ወሎ እንዲሁም 5,980 ሰዎች ወደ ሰቆጣ ዋግኽምራ ዞን ነው የተፈናቀሉት። በአካባቢው ያለው ሁኔታ…
#Raya

እንደ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ሪፖርት መሰረት ከራያ አላማጣ ገጠራማ አካባቢዎች የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከ50 ሺህ በልጧል።

42 ሺህ ዜጎች ቆቦ ፤ 8,300 ሰዎች ሰቆጣ ይገኛሉ።

የተፈናቀሉት ከራያ አላማጣ፣ ዛታ፣ ኦፍላ ነው።

አብዛኞቹ ህጻናት ፣ ሴቶች ፣ ወጣቶች እና በእድሜ የገፉ አዛውንቶች ናቸው።

#UNOCHA

@tikvahethiopia