TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#BahirDarUniversity

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በበይነ መረብ (Virtual) ትምህርታቸውን እንዲጨርሱ ያስቻላቸው የድህረ ምረቃ (ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ) ተማሪዎቹን ፣ እንዲሁም ከኮሮና ወረርሽኝ መከሰት በፊት ትምህርታቸውን አጠናቀው ምረቃቸው በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ከጸደቀ በኋላ በወረርሽኙ ምክንያት የምረቃ ስነ-ስርዓቱ ሳይካሄድ የቆዩትን በዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የሙያ መስኮች በመደበኛና መደበኛ ያልሆኑ መርሃ-ግብሮች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎችን ነገ ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም በበይነ መረብ (Virtual) ስነ-ስርዓት ያስመርቃል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የዩኒቨርሲቲዎች ዝግጅት ምን ይመስላል ?

#BahirDarUniversity

- የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ለመቀበል የዝግጅት ሥራዎችን እየሰራ ይገኛል።

- በተለይ የዶርምተሪ ጥገናዎች ተደርገዋል፤ ተማሪዎች በዶርም ውስጥ የሚኖራቸው ቁጥር በመመሪያው መሰረት ከዛም በተሻለ መልኩ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

- የተለያዩ የግብዓት አቅርቦቶችም እየተሟሉ ይገኛል።

- ዩኒቨርሲቲው ካሉት ካምፓሶች ሁለቱ (2) ብቻ በኳራንቲን ማዕከልነት አገልግለዋል ፤ በእነዚህ ዩኒቨርሲቲዎች የጽዳት ሥራም ይሰራል።

#DireDawaUniversity

- ዩኒቨርሲቲው አሁን ላይ በኳራንቲን ማዕከልነት እያገለገለ ሲሆን በቅርቡ ሙሉ ለሙሉ ወደ ቀድሞ ተግባሩ ለመመለስ እየተሰራ ነው።

- በዶርም ውስጥ የሚገኙ ፍራሾች በአዲስ የሚተኩ ሲሆን የእድሳት ሥራዎችንም በአጭር ግዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ታቅዷል፡፡

- ትምህርትን በሚመለከት ተመራቂ ተማሪዎች እና የአራተኛ አመት ኢንጂነሪንግ ተማሪዎች በተለይ (አፓረንት) የሚወጡ ተማሪዎች ቀድመው ይጠራሉ።

- ተማሪዎች የአንደኛ (1) ሴሚስተር ፋይናል ፈተና ሳይወስዱ ከግቢ በመውጣታቸው ምክንያት ሲመለሱ የማጠናቀቂያ ፈተናቸውን ይወስዳሉ።

- ሆለስቲክ ፈተናም ይሰጣል።

- በተጨማሪም የተግባር ልምምድ (አፓረንት) በተመለከተ ከፈተናው በኃላ የሚወጡ ይሆናል።

(ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ቅድመ ዝግጅት በየጊዜው እየጠየቀ እና እየተከታተለ ለተማሪዎች እንዲሁም ለተማሪ ወላጆች ያሳውቃል)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ ፦

#WolaitaSodoUniversity

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ እለተ ዛሬ 29 ቀን 2013 ዓ.ም በመደበኛ እና በተከታታይ የትምህርት መርሃ-ግብር በቅድመ ምረቃ እና በድህረ ምረቃ ያሰለጠናቸውን 5,310 ተማሪዎችን እያስመረቀ ይገኛል።

#WoldiaUniversity

የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ላለፋት ዓመታት በተለያዩ ትምህርት መስኮች ሲያሰለጥናቸው የቆዩ ተማሪዎቹን ዛሬ በሼህ ሙሃመድ ሁሴን አሊ ኣላሙዲን ስታዲየም እያስመረቀ ይገኛል።

በመደበኛው፣ በተከታታይ እና በክረምት መርሃግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 2785 የሚሆኑ እጩ ተመራቂ ተማሪዎችን ነው እያስመረቀ የሚገኘው።

ከጠቅላላ ተመራቂዎች ውስጥም 926 ሴቶች ናቸው።

#BahirdarUniversity

ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መድኮች ሲያስተምራቸው የቆያቸውን 5,117 ተማሪዎችን በፔዳ ካምፓስ በማስመረቅ ላይ ይገኛል።

4,203 የሚሆኑት የመጀመሪያ ዲግሪ (ቅድመ ምረቃ ፕሮግራም) የተማሩ ናችው። 759 በሁለተኛ ድግሪይ የተማሩ፣10 የፒኤችዲ ተመራቂዎች ይገኙበታል።

በሌላ በኩል በህክምና ስፔሻሊቲ የተመረቁ 40 የሚሆኑ ሰልጣኞች ዛሬ እየተመረቁ ነው።

ከአጠቃላይ ተመራቂዎቹ ውስጥ 1,623 የሚሆኑት ሴቶች ናቸው።

#DebarkUniversity

ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 773 ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በማስመረቅ ላይ ይገኛል፡፡

#MizanTepiUniversity

ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ከ2 ሺህ በላይ ተማሪዎችን እያስመረቀ ይገኛል።

በሌላ በኩል፦

ሂልኮ የኮምፒዩተር ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ኮሌጅ ነገ ጥር 29/2013 ዓ/ም ተማሪዎቹን ያስመርቃል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
* Congratulations !

በዛሬው ዕለት ብቻ ከተለያዩት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ከ30,192 በላይ ተማሪዎች ተመርቀዋል።

የትኞቹ ዩኒቨርሲቲዎች ምን ያህል ተማሪ ? በምን ደረጃ እና የትምህርት ዘረፍ አስመረቁ ? ለጥያቄዎቹ መልስ ይህን አጭር ቁጥራዊ መረጃ አስቀምጠናል።

#HawassaUniversity

- አጠቃላይ 6 ሺህ 793 ተማሪዎችን አስመርቋል።
- ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 2 ሺህ 158ቱ ወይም 32 በመቶ ሴቶች ናቸው።
- ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ፣ በ2ኛ እና በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛና ተከታታይ መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

#BahirdarUniversity

- አጠቃላይ 5 ሺህ 586 ተማሪዎች አስመርቋል።
- ከተመራቂዎቹ 1 ሺህ 714ቱ ሴቶች ናቸው።
- በመጀመሪያ፣ በ2ኛ እና በ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናሰቁ ናቸው።

#JimmaUniversity

- አጠቃላይ 696 ተማሪዎች አሰመርቋል።
- 450 ወንድ እና 246 ሴት ተማሪዎች ናቸው።
- በቅድመ ምረቃና በድህረ ምረቃ መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
- ከተመራቂዎቹ 252 ተማሪዎች በአጠቃላይ ሕክምናና በጥርስ ሕክምና የሰለጠኑ ናቸው።
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሶማሊላንድ ሀርጌሳ ካምፓሱ በ 'ኒውትሬሽን' የትምህርት ዘርፍ ያስተማራቸውን 19 የ2ኛ ዲግሪ ተማሪዎችንም አስመርቋል።

#AdamaScience_and_TechnologyUniversity (ASTU)

- አጠቃላይ 1 ሺህ 298 ተማሪዎች አስመርቋል።
- ሰባቱ በሦሥተኛ ዲግሪ (ፒኤችዲ) ተመራቂዎች ናቸው።
- 215ቱ በሁለተኛ ዲግሪ የተመረቁ ናቸው።
- 1 ሺህ 76 ተማሪዎች በመጀመረያ ዲግሪ የተመረቁ ናቸው።

#MettuUniversity

- አጠቃላይ 2 ሺህ 262 ተማሪዎች አስመርቋል።
- 116ቱ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
- ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብሮች በመቱ እና በበደሌ ካምፓሶች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።

#ArsiUniversity

- አጠቃላይ 831 ተማሪዎችን አስመርቋል።
- በበቆጂ ካምፓስ የሰለጠኑ ናቸው።
- ተመራቂዎቹ በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ በመደበኛና በተከታታይ መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
- በመጀመሪያ እና በ2ኛ ዲግሪ ከተመረቁት መካከል 392ቱ ሴቶች ናቸው።

#AmboUniversity

- አጠቃላይ 4 ሺህ 524 ተማሪዎች አስመርቋል።
- በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ የሰለጠኑ ናቸው።
- ከተመራቂዎቹ 1 ሺህ 980ዎቹ ሴት ተማሪዎች ናቸው።
- ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 450 የሚሆኑት የሁለተኛ ዲግሪ ተመራቂ ሲሆኑ 11 የደቡብ ሱዳን ስደተኛ ተማሪዎች ይገኙበታል።

#JigjigaUniversity

- አጠቃላይ 1 ሺህ 202 ተማሪዎችን አስመርቋል።
- ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 336ቱ ሴት ተማሪዎች ናቸው።
- 233ቱ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ሲሆን ቀሪዎቹ 969ኙ በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።

* ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል #AdmasUniversity

- አጠቃላይ ከ10 ሺህ በላይ ተማሪዎችን አስመርቋል።
- ከተመራቂዎቹ 67 በመቶ ሴቶች ናቸው።
- በቴክኒክና ሙያ፣ በመጀመሪያ ዲግሪ እና 2ኛ ድግሪ በቀንና በማታ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
- ከተመራቂዎቹ መካከል 1 ሺህ 532ቱ በ2ኛ ዲግሪ የተመረቁ ናቸው።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳዮችን በ @tikvahuniversity ተከታተሉ።

@tikvahethiopia
#BahirDarUniversity

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከመቐለ ፣ አክሱም ፣ ዓዲግራት እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲዎች በጊዚያዊነት ወደ ተቋሙ የተመደቡ የመደበኛ መጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ምዝገባ ከየካቲት 21 እስከ 24/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

በመሆኑም በተገለጹት ቀናት የትምህርት ማስረጃችሁን (የምዝገባ ስሊፕ ፣ ግሬድ ሪፖርት እና የተማሪነት መታወቂያ) በመያዝ በተቋሙ በመገኘት ሪፖርት አድርጉ ብሏል።

የመጀመሪያ ዓመት ትምህርት ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ደግሞ ለ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች (አዲስ ገቢዎች) ጥሪ እስከሚደረግ መጠበቅ ይኖርባቸዋል ተብሏል።

More : @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
" ስለ ትውልዱ ግድ ይለናል የምትሉ ኃላፊዎች መፍትሄ ስጡን " - ተማሪዎቹ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፤ " መፍትሄ የሚሰጠን አጥተን ያለ ትምህርት ቤታችን ቁጭ ብለናል ፤ ጊዜያችንም እየተቃጠለ ነው " ሲሉ አማረዋል። የባህር ዳር ዩንቨርሲቲ የ2016 ዓ/ም የ1ኛ ዓመት እና የሬሚድያል ተማሪዎች ወደ ግቢ እንዲገቡ ጥሪ ተደርጎላቸው በኃላም መራዘሙ ይታወሳል። ነገር ግን እስካሁን ምንም አይነት ጥሪ…
#BahirDarUniversity

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም አዲስ ለተመደቡ እና በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ለተከታተሉ ተማሪዎች ጥሪ አደረገ።

በዚህም በ2016 ዓ.ም አዲስ የተመደቡ Freshman ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስትከታትለው ቆይተው የማለፊያ ውጤት በማምጣት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደበ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ከመጋቢት 26 እስከ 28/2016 ዓ.ም መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።

የምዝገባ ቦታውም ፦
➤ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሰላም ግቢ
➤ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በግሽ አባይ ግቢ ነው ተብሏል።

በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን አቋርጠው ለአንደኛ ዓመት የመጀመሪያ ሴሚስተር ለመልሶ ቅበላ የሚያበቃ ውጤት ያላቸውና የመልሶ ቅበላ ፎርም የሞሉ ተማሪዎች ምዝገባ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዛሬ ያወጣው ጥሪ በማካካሻ መርሐ ግብር (Remedial Program) በ2016 ዓ/ም አዲስ የተመደቤ ተማሪዎችን #አይመለከትም ተብሏል።

Via @tikvahuniversity
#BahirDarUniversity

ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ለ2016 የሪሚዲያል ተማሪዎቹ ጥሪ ሊያደርግ ነው፡፡

ዩኒቨርሲቲው በፀጥታ እና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች በ2016 ዓ/ም አዲስ ለተመደቡለት የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች እስካሁን ድረስ ጥሪ ሳያደርግ ቆይቷል።

ረቡዕ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም ውይይት ያደረገው የዩኒቨርሲቲው ሴኔት፣ በሰኔ ወር መጨረሻ ለተማሪዎቹ ጥሪ እንዲደረግ መወሰኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተቋሙ ለማረጋገጥ ችሏል፡፡

በዚህም #ከሐምሌ_ወር አጋማሽ ጀምሮ ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን በዩኒቨርሲቲው በመገኘት መከታተል ይጀምራሉ ተብሏል፡፡

ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁም ፣ ትምህርት ሚኒስቴር #በልዩ_ሁኔታ ፈተና እንደሚያዘጋጅላቸው ለማወቅ ተችሏል።

የሬሜዲያል ተማሪዎቹ ያለትምህርት በመቀመጣቸው ከፍተኛ የሆነ ጫና እየደረሰባቸው በመሆኑ መፍትሄ እንዲፈለግላቸው ተደጋጋሚ ጥሪ ሲያቀርቡ እንድነበር አይዘነጋም።

More ➡️ @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#BahirDarUniversity ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ለ2016 የሪሚዲያል ተማሪዎቹ ጥሪ ሊያደርግ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በፀጥታ እና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች በ2016 ዓ/ም አዲስ ለተመደቡለት የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች እስካሁን ድረስ ጥሪ ሳያደርግ ቆይቷል። ረቡዕ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም ውይይት ያደረገው የዩኒቨርሲቲው ሴኔት፣ በሰኔ ወር መጨረሻ ለተማሪዎቹ ጥሪ እንዲደረግ መወሰኑን ቲክቫህ…
#BahirDarUniversity

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለሬሜዲየል ተማሪዎች ጥሪ አደረገ።

በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ለመከታተል ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ሐምሌ 22 እና 23 ቀን 2016 ዓ/ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በ " ፖሊ ካምፓስ " ፤ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ደግሞ በ " ግሽ ዓባይ ካምፓስ " ሪፖርት እንዲያደርጉ ተብሏል።

Via @tikvahuniversity