TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ዩጋንዳ የኢቦላ መከላከያ ክትባት መስጠት ጀመረች፡፡ በዩጋንዳ የተጀመረው ክትባት በኢቦላ ምክንያት 1ሺህ 800 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡባት ኮንጎ ውስጥም እንደሚጀመር ታውቋል፡፡ ዩጋንዳ በተደጋጋሚ የኢቦላ ቫይረስ ሲከሰትባት፣ የዜጎቿን ህይወትም ስትነጠቅ ቆይታለች፡፡ ክትባቱ በሀገሪቱ ምዕራባዊ ክፍል እስከ 8 መቶ ሰዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ታውቋል፡፡ ድጋፉ የተገኘውም በለንደን የስነ ንጽህና ትምህርት ቤት እና በድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን እንደሆነ ተዘግቧል፡፡

Via #CGTN/AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሱዳን

የሱዳን ተቃዋሚ ሃይሎች አምስት ሲቪል የሉአላዊ ምክር ቤት አባላትን መምረጣቸው ተገለፀ። በሱዳን ተቃዋሚዎች ጥምረት የመረጧቸው የኡአላዊ ምክር ቤቱ አባላቱ በዛሬው እለት ቃለ መሃላ ይፈጽማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ተነግሯል። ከወታዳራዊ ሽግግር ምክር ቤት፤ መሪውን አብደል ፈታህ አልቡራን፣ ምክትላቸውን ሞሃመድ ሃማዳን ዳጋሎ እና የወታዳራዊ ሽግግር ምክር ቤት ቃል አቀባይ ሌተናል ጀኔራል ያሰር አል አታን ይጨምራል ነው የተባለው፡፡

Via #CGTN/#FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ለአፍሪካውያን ሴት የሥራ ፈጣሪዎች የቡድን 7 አባል ሃገራት 251 ሚሊየን ዶላር መመደባቸው አስታውቀዋል።

Via #CGTN/AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UPDATE

የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ተቃዋሚያቸው የነበሩት ሪክ ማቻርን የሀገሪቷ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት አድርገው ሾመዋል፡፡

የሪክ ማቻር ሹመት የተሰማው ሁለቱ አካላት የብሄራዊ አንድነት መንግስት ለመመስረት ከስምምነት መድረሳቸውን ተከትሎ ነው።

#CGTN #ENA
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#NewsAlert

በካሜሮን ለመጀመሪያ ጊዜ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ መገኘቱን የሀገሪቱ መንግሥት ገልጿል፡፡ የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ዛሬ ዓርብ የካቲት 27/2012 ዓ.ም ነው የመጀሪያው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ መገኘቱ የተረጋገጠው፡፡

ቫይረሱ የተገኘበት ግለሰብ የፈረንሳይ ዜግነት ያለው የ58 ዓመት ጎልማሳ ነው፡፡ ግለሰቡ ካሜሩን መዲና ያውንዴ ከገባ በኋላ የቫይረሱ ተጠቂ መሆኑ ሲረጋገጥ በቀጥታ ወደ ለይቶ ማቆያ ገብቶ በከተማው ማዕከላዊ ሆስፒታል ሕክምና እየተከታተለ መሆኑን ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው፡፡

#CGTN #AMMA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ማጠቃለያ አጫጭር መረጃዎች፦

- አውሮፓ ውስጥ ብቻ በኮሮና ቫይረስ ተጠቅተው የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ15,000 በልጧል።

- ደቡብ አፍሪካ መንግሥት ሙሉ ለሙሉ እንቅስቃሴን የማገድ አዋጅ ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ ማድረግ ይጀምራል።

- በፈረንሳይ በ24 ሰዓት ውስጥ ተጨማሪ 365 የኮቪድ-19 ሞት ተመዝጓል አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርም 1,696 ደርሷል።

- በዩናትድ ኪንግደም የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር 11,658 ደርሷል። የሟቾች ቁጥርም ወደ 578 ከፍ ብሏል።

- የG20 አገራት በኮሮናቫይረስ ምክንያት የተዳከመውን የዓለም ኢኮኖሚ ለመደገፍ 5 ትሪሊዮን ዶላር ወደ ዓለም ገበያ ፈሰስ ለማድረግ ቃል ገብተዋል።

- በአሜሪካ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ከ80,000 ተሻግሯል። በአሜሪካ ያሉ ተጠቂዎችም ከጣልያን በልጠዋል። በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች ቁጥርም 1,163 ደርሷል።

- ኡጋንዳ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎቶችን አግዳለች። የንግድ ተቋማት ድርጅቶቻቸውን እንዲዘጉ መንግሥት ውሳኔ አስተላልፏል።
 
- በአውሮፓ ከጣልያን ቀጥላ በኮሮና ቫይረስ ክፉኛ እየተጎዳች የምትገኘው ስፔን በ24 ሰዓት 498 ሰዎችን አጥታለች። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርም 4,145 ደርሰዋል።

- በመላው ዓለም የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር 524,007 ደርሷል፤ 23,670 ሰዎች ሞተዋል። 123,322 ሰዎች አገግመው ከሆስፒታል ወጥተዋል።

#CGTN #BBC #AFP
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
" ኢትዮጵያ የአገሪቱን መረጋጋትና ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም ግለሰብ አትታገስም " - ቢልለኔ ስዩም

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ፅ/ቤት የፕሬስ ሴክሬተሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ኢትዮጵያ ውስጥ በቁጥጥር ስር ስለዋሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ሰራተኞች ጉዳይ ለCGTN አፍሪካ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር።

ቢልለኔ ፥ “ተመድ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ውክልና ትክክለኛ የአገሪቱን ህግ አክበረው የሚሰሩ እንዳሉ ሁሉ የተሰጣቸውን ሃላፊነትና መብት ላልተገባ ተግባር በማዋል ለአሸባሪ እገዛ የሚያደርጉ አሉ” ብለዋል፡፡

ቢልለኔ ፥ "ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአሸባሪው ህወሃት እገዛ እንደሚያደርጉ የሚጠረጠሩትን በመያዝ ምርመራ ይደረጋል " ያሉ ሲሆን እነዚህ ተጠርጣሪዎች ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ቢልለኔ ፥ “ኢትዮጵያ የአገሪቱን መረጋጋት እና ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም ግለሰብ አትታገስም” ያሉ ሲሆን " ሁሉም ከህግ በታች ነው " ሲሉ አስገንዝበዋል።

Credit : #CGTN #ENA

@tikvahethiopia
#OlusegunObasanjo

ኢትዮጵያ 🇪🇹 " ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ " ለሚለው መርህ ባላት እምነት እና ቁርጠኝነት የአፍሪካ ህብረት በኢትዮጵያ ሰላም እንዲሰፍን ለሚያደርገው ጥረት አክብሮት እንዳላት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ሃላፊ ቢልለኔ ስዩም ተናገሩ፡፡

ቢልለኔ ይህን ያሉቱ ከCGTN አፍሪካ ጋር በነበራቸው ቆይታ ነው።

ሰሞኑን በኢትዮጵያ ተገኝተው ሰላምን ስለማምጣት የተወያዩት የናይጄሪያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኦሊሴንጉን አባሳንጆ በአፍሪካ ህብረት የተወከሉ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልእክተኛ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

የአፍሪካ ህብረት አህጉራዊ ችግሮችን ለመፍታት ስላለው ውሳኔ ኢትዮጵያ አክብሮት እንዳላት ገልፀው፤ ኦባሳንጆ በትልቅነታቸው፣ በአገር መሪነታቸውና የተለያዩ ወገኖችን ወደ ሰላም ለማምጣት በሚያደርጉት ጥረት ትክክለኛ ውክልናና ጥረታቸውም እንደሚሳክ እናምናለን ብለዋል፡፡

Credit : #CGTN #ENA

@tikvahethiopia
የቤጂንግ እና የዋሽንግቶን ውጥረት ?

አሜሪካ እና ቻይናን ውጥረት ውስጥ የከተታቸው የታይዋን ጉዳይ ነው።

ቻይና ታይዋን #ወደ_እናት_አገሯ መመለስ ያለባት አፈንጋጭ ግዛቷ እንደሆነች ነው የምታስበው

ይህንንም ለማሳካት ወደፊት ቤይጂንግ ኃይል መጠቀምን እንደ አንድ አማራጭ ታየዋለች። 

አሜሪካ ደግሞ ከቻይና ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላት ሲሆን፣ ከታይዋን ጋር ግን “ይፋዊ ያልሆ ጠንካራ” ዲፕሎማሲያዊ ግንኙት አላት ይባላል።

ረጅም ጊዜ ይሄ ጉዳይ ሲንከባለል እና በቻይና እና አሜሪካ መካከል ምልልስን ሲፈጥር ቆይቷል።

አሁን ግን የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋን እንደሚጎበኙ ማሳወቃቸው የለየት ውጥረትን ፈጥሯል።

ፔሎሲ በአገሪቱ የሥልጣን አርከን ውስጥ ከፕሬዝዳንቱ እና ከምክትላቸው ቀጥሎ ሦስተኛ ሰው ናቸው።

ቻይና ፔሎሲ ታይዋንን ከጎበኙ እስከ ወታደራዊ እርምጃ ድረስ ልትወስድ እንደምትችል ሲነገር ነበር።

ምንም እንኳን ቻይና የአሜሪካዋ 3ኛ ሰው ታይዋንን እንዳትጎበኝ ብታስጠነቅቅም ከጥቂት ሰዓት በፊት ታይዋን ደርሰዋል።

አቀባበልም ተደርጎላቸዋል።

የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉብኝቱን ለቻይና ክብር አለመስጠታቸው ማሳያ ነው ፤ ለቻይና ተገንጣይ ቡድኖች እውቅና መስጠት ነው ብሏል።

ሚኒስቴሩ በፔሎሲ ውሳኔ ማዘኑን አስታውቋል፡፡

ለሉአላዊነትና ደህንነትን ለማስጠበቅ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።

ለሚመጣው መዘዝ አሜሪካ እና ታይዋን ሃላፊነቱን ይወስዳሉ ብሏል።

#RT #CGTN #BBC

@tikvahethiopia
#China

ኢትዮጵያ ፣ ኤርትራ እና ሱዳን ስለ ቻይና-ታይዋን ጉዳይ ምን አሉ ?

#ኢትዮጵያ

ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰሞኑን የቻይና-ታይዋን ጉዳይ የተከሰተውን ውጥረት በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ለኢዜአ ተናግረዋል።

አምባሳደር መለስ ፤ ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ስታራምድ የቆየችውን የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋሟን እንዳጸናች መሆኑን ተናግረዋል።

" የኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ያሉት " አምባሳደር መለስ፤ " ከቻይና ጋር በነበረን ግንኙነት ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስታት አፅንተው የያዙት አቋም ነው " ብለዋል።

አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያ ለ #አንድ_ቻይና ፖሊሲ ፅኑ አቋም አላት ያሉ ሲሆን ፖሊሲውን ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸው የተመድና የአፍሪካ ህብረት የሚያራምዱት አቋም መሆኑን ገልፀዋል።

#ሱዳን

ሱዳን ለአንድ ቻይና መርህ ድጋፏን እንደምትሰጥ አሳውቃለች። ታይዋንም የቻይና ግዛት አካል መሆኗን ገልጻለች።

ሱዳን ፤ ቻይና ሉዓላዊነቷን እና የግዛት አንድነትዋን በመጠበቅ ረገድ የምታደርገውን እንቅስቃሴ እንደምትደግፍም አስታውቃለች።

#ኤርትራ

ኤርትራ የአሜሪካ አፈጉባዔ ወደ ታይዋን ያደረጉት ጉዞ ከዓለም አቀፍ ህግና መርህ ያፈነገጠ ነው ብላለች።

የአፈጉባኤዋ ድርጊት የቻይና መንግስት ሉዓላዊነት ደንቦችን እና ድንጋጌዎች እንዲሁም " የአንድ-ቻይና " ፖሊሲ የሚጻረር እና የቻይናውያን ውህደት ሂደትን የሚያደናቅፍ ነው ስትል ገልፃለች።

ኤርትራ፤ አሜሪካ ቻይናን ለመቆጣጠርና ለመያዝ ጥረት እያደረገች ነው ብላ ድርጊቱ አጸያፊ ነው ብላለች።

#CGTN #ENA #AlAIN #Shabait

@tikvahethiopia