TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሶማሌላንድ

በሶማሌላንድ ግዛት በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎችና በተቃዋሚ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት በርከታ ሰዎች ሰላም ፍለጋ ወደ #ኢትዮጵያ እየገቡ ናቸው።

እስካሁን ግጭት የሸሹ ከ83 ሺ በላይ የሶማሌላንድ ነዋሪዎች ወደ ኢትዮጵያ ድንበር በመዝለቅ በሶማሌ ክልል መስፈራቸው ተነግሯል።

የተመድ የስደተኞች ኮሚሽንን ዋቢ በማድረግ #ሪፖርተር ጋዜጣ እንዳስነበበው "ላስካኑድ" በምትባለው ከተማ በተከሰተው ግጭት፣ የበርካታ የሶማሌላንድ ነዋሪዎችን ሕይወት የተቀጠፈ ሲሆን በርካታ ሴቶችና ሕፃናት ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል፤ ዶሎ ዞን እየገቡ ናቸው።

እንደ ኮሚሽኑ መረጃ ፦

- እስከ  ቅዳሜ የካቲት 11 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ 14 ሺሕ የሚሆኑ አዳዲስ አባወራዎች (ወይም 83 ሺሕ ግለሰብ ስደተኞች) ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል።

- ስደተኞቹ በዶሎ ዞን፤ ቦህ፣ ገልሃሙርና ዳኖድ በተባሉ 3 ወረዳዎች ተጠልለው ይገኛሉ።

- አብዛኞቹ ስደተኞች ባለፈው ሳምንት ነው ወደ ኢትዮጵያ የገቡት።

- ስደተኞች በ3 ወረዳዎች በ13 ቦታዎች ሠፍረው የሚገኙ ሲሆን የተወሰኑት በትምህርት ቤትና መሰል የሕዝብ መገልገያ ሥፍራዎች ላይ ተጠልለዋል፤ ሌሎች ደግሞ ያለ መጠለያ ሜዳ ላይ ይገኛሉ።

- ከሶማሌ ክልል የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ቢሮ ጋር በመሆን ከ1,500 በላይ ለሆኑ በከፍተኛ ሁኔታ ለተጎዱ አባዎራዎች የተለያዩ ቁሳቁሶችና መሰል ድጋፎችን እየተሰጠ ነው።  ለተጨማሪ 9 ሺህ አባዎራዎች በቀጣይ ቀናት ድጋፍ ይደረጋል።

የሶማሌ ክልል፤ የስደተኞችን ወደ ኢትዮጵያ መግባት ያረጋገጠ ሲሆን ከተመድ የስደተኞች ኮሚሽን፣ ከዓለም አቀፍ ፍልሰት ድርጅት፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ጋር በመሆን የዳሰሳ ጥናት አካሂዷል።

ያንብቡ : telegra.ph/ER-02-22

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ #ሶማሌላንድ

በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ እና በሶማሌ ላንድ መካከል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሟል።

ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ የባሕር በር የምታገኝበትን መንገድ ይጠርጋል ተብሏል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ታሪካዊ ነው የተባለውን የመግባቢያ ሠንድ በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል፡፡

የኢፌዴሪ መንግሥት እና የሶማሌላንድ መንግሥት የፈረሙት የትብብር እና የአጋርነት መግባቢያ ሠነድ በተለያዩ ዘርፎች በቀጣይ ለሚኖራቸው ግንኙነቶች ማዕቀፍ  እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ጽኅፈት ቤት ይፋ ባደረገው መረጃ አሳውቋል።

የመግባቢያ ሠነዱ ፦
* የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት ፍላጎት ዕውን የሚያደርግ ፣
* የባሕር በር አማራጮቿን የሚያሠፋ
* የሁለቱን ወገኖች የፖለቲካ ፣ የዲፕሎማሲ ፣ የፀጥታ እና የኢኮኖሚ ትብብር የሚያጠናከር ነው ብሏል።

በተጨማሪም ሠነዱ ሀገራቱ በፖለቲካ እና በዲፕሎማሲው ዘርፍ የሚኖራቸውን ግንኙነት የሚጎለብትበትን አካሄድ የሚያካትት መሆኑን ገልጿል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በሰጥቶ መቀበል መርኅ እና ሀገሪቷ ለጋራ ጥቅም ከጎረቤቶቿ ጋር የመሥራት ፍላጎት እና አቋሟን መልሶ የሚያጸና እንደሆነም አመላክቷል፡፡

ሠነዱ ፤ አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እና ለአፍሪካ ቀንድ ትሥሥር የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑን ጠቁሟል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዛሬ በራዝ ገዟ ሶማሊላንድ ይፋዊ መግለጫ ወጥቷል። በዚህም መግለጫ ስምምነቱ ታሪካዊ ነው ተብሏል። ይህ ታሪካዊ ስምምነት ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ እውቅና በመስጠት በሊዝ የባህር በር / ለባህርኃይሎቿ የባህር መዳረሻ እንደምታገኝ መግለጫው ይገልጻል። " ስምምነቱ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ ነው " ያለው መግለጫው ለኢትዮጵያ የባህር ኃይል ተጠቃሚነት 20 ኪሎሜትር የባህር በር እንደሚሰጥ…
#Ethiopia #Seaport

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከሶማሊለንድ ጋር ስለተፈረመው ስምምነት ምን አሉ ?

- ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚ እንድትሆን በምክክር፣ በሰላማዊ መንገድ ብቻ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተለያዩ የዲፕሎማሲ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።

- ከሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጋር ብዙ ሞክረን ያልተሳካው ከሶማሊላንድ ጋር በተመሳሳይ መንገድ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል።

- መንግሥት አቋሙን ይፋ ካደረገ በኃላ ያሉ ሃብቶችን ከመጋራት አንፃር የነበረው ጉዳይ ጥርቶ ከወጣ በኃላ ዝርዝር ውይይት ሲካሄድ ነው የቆየው።

- ጉዳዩ መልክ እስኪይዝ በተወሰነ በጠባብ ቡድን፣ በመሪዎች ደረጃ እና በተወሰኑ አካላት ደረጃ እንዲያዝ እየበሰለ ሲሄድ ደግሞ ሁለቱም አካላት የየራሳቸውን አመራር እያሳተፉ የሚሄዱበት ሁኔታ እንዲፈጠር ተደርጓል።

- የወደብ ስምምነት ተጠቃሚነት በሊዝ አማካኝነት የሚፈፀም ነው።

- ይህ የስምምነት ማዕቀፍ ሶማሌለንድ እና ኢትዮጵያ አንዳቸው ጋር ያለውን ሃብት ለመጋራት በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እድል የሚያሰፋበት፣ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ ኢትዮጵያ ያላትን አቅምና ልምድ ለሶማሊላንድ የምታጋራበት ፤ የጋራ ጥቅማቸውን ማስጠበቅ የሚችሉበት አቅም ይገነባል።

- የስምምነቱ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ ሶማሌላንድ ውስጥ Military base እና Commercial maritime ሰፈር እንዲኖራት ይፈቅዳል። ይህ #በሊዝ የሚታሰብ ይሆናል። ለ50 ዓመት እና ከዛ በላይ #በማራዘም የሚካሄድ እንዲሆን ያደርጋል።

- ኢትዮጵያ አማራጭ ወደብን እድል ለማግኘት በርበራ ኮሊደርን የምታሰፋበት ፣ የመከላከያ አቅሟን አዲስ በምትከራየው ቦታ የምታጠናክርበት እድል ይሰጣል።

- ኢትዮጵያ ለሊዝ ተጠቃሚነቷ ቴሌኮም ይሁን፣ አየር መንገድ ይሁን ጥቅም በሚያስገኙ መሰረተ ልማቶች ላይ ድርሻ ትሰጣለች። ምን ያህል ነው ? የሚለው የሚከፈለው ሊዝም ምን ያህል ይሆናል ? የሚለው በዝርዝር ውይይቶች ይወሠናል።

- በጤና፣ በትምህርት ፣ በመከላከያ የሚሰሩት ዝርዝር ስምምነቶች በተናጠል ውይይት ይካሄድባቸዋል። ወደ ፓርላማ ሄደው የሚፀድቁ በርካታ ስምምነቶች ከዚህ ይፈልቃሉ።

- የጋራ የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱ አጠቃላይ ማዕቀፍ ሁለቱ አካላት በጋራ ተባብረው የሚያድጉበትን ማዕቀፍ ነው የሚያስቀምጠው። ዋና ዋና አንጓዎች ተቀምጠዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር የምታገኝበትን ዕድል በተጨባጭ ወደመሬት ለማውረድ እድል ይሰጣል።

- ስምምነቱ በ1 ወር ጊዜ ውስጥ ሂደቱ ያልቃል / ወደ ተግባር / ስራ ይገባል።

- ከሌሎች ሀገራት ጋር የጀመርናቸው አሉ #ከኤርትራ ጋር በዝርዝር ውይይት ተጀምሮ የሆነ ቦታ ላይ ነው የቆመው።

- ኢትዮጵያ አንድ ወደብ ፣ ሁለት ወደብ ፣ ሶስት ወደብ ሳይሆን ፤ ኢትዮጵያ አሁን ባለው ሁኔታ እያደገች ከሄደች ሁሉም ቀጠናዎች የሁሉም ጫፎች የኢትዮጵያን ምርቶች የሚያስገቡበት በር ያስፈልጋል።

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በማብራሪያቸው በስምምነቱ ሶማሊያ ልዓላዊ ግዛቴ ናት ለምትለው ራስ ገዟ #ሶማሌላንድ በይፋ የነፃ ሀገርነት እውቅናን ትስጠ እንደሆነ የተናግሩት አንዳች ነገር የለም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሀርጌሳ " ሀገራችንን አልሸጥንም " - ሙሴ ባሂ አብዲ ባለፉት ቀናት ኢትዮጵያ የነበሩት የራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት ዛሬ ሐሙስ ዕለት ወደ ሀርጌሳ ተመልሰዋል። ፕሬዚዳንቱ ሀርጌሳ ሲገቡ ህዝቡ ወደ አደባባይ ወጥቶ ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል። አደባባይ ወጥቶ ለተቀበላቸው ህዝብ ባሰሙት ንግግር ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ትልቅ ዋጋ ያለው መሆኑ…
#ኢትዮጵያ #ሶማሌላንድ

የኢትዮጵያ እና የሶማሌላንድ #የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ (MOU) ይዘት ምን ይላል ?

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፦

- #ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ስታደርግ እንደነበረው፤ ከሶማሌላንድም ጋር ከዚህ በፊት እንደነበረው አይነት ስምምነቶችን ያነሳና ይሄ ስምምነት ወደተሟላ ደረጃ መድረስ እንዳለበት ያስቀምጣል።

- ኢትዮጵያ አሁን ያለባትን ስጋት እንድትቀርፍ የህዝብ እድገቷን ፣ የኢኮኖሚ እድገቷን የሚመጥን አካባቢው ካለው የሁከት ተጋላጭነት የራሷን ደህንነት እንዲሁም የቀጠናውን ሰላም በማስጠበቅ ሂደት ሚና እንዲኖራት የሚያስችል እራሷ የምታለማውና የምትቆጣጠረው የተወሰነ የባህር በር ያስፈልጋታል የሚል ነው። ይህ ሚሊታሪ ቤዝ እና ማሪታይም / ኮሜርሻል አገልግሎት ነው።

- የሚሊታሪ እና የማሪታይም / ኮሜርሻል ቤዝ ቦታው አማካይ እንዲሆን ተሞክሯል።

- ቦታው በበርበራ እና በዛይላ መካከል የሚገኝ ስፍራ ነው። ለኢትዮጵያ ድንበር አጠር ያለና ለሚሰራውም መንገድ እና ባቡርም የቀለለ፣ ለጥበቃውም የተመቸ እንዲሆን ነው። " ሎጋያ " የተባለ ቦታ አለ ለድንበር ቅርብ እዛ ላይ እንሰጣችኃለን በሚል ተስማምተዋል።

- ርቀቱን በተመለከተ እነሱም እኛም ስንለው የነበረው ነበር አማካይ ላይ ተገናኝነትን በ20 ኪ/ሜ የሚሆን ቦታ ቤዝ ይኖረናል በዓለም አቀፍ ህጉ ውሃውንም ይጨምራል ፣ ከውሃው ወደ መሬት ያለውንም እንዲሁ።

- ከድንበር ወደሚመሰረተው ቤዝ የሚሄድ መንገድ ይሰራል።

- ጊዜው 50 ዓመት እንዲሆና ሲያልቅ የሚራዘምበትን አማራጭ ያስቀምጣል።

ምንድነው ኢትዮጵያ የምትሰጣቸው ?

የመንግሥት ፖሊሲ ግልፅ እንዳደረገው ከቴሌኮም ፣ ከኃይል ማመንጫ ፣ ከአየር መንገድ ... ብቻ አዋጭ ከሆኑ ተቋማት #እራሳችን በምንመራበት መንገድ ለሀገርም በሚጠቅም መልኩ #ድርሻ መስጠት ነው። ይሄ ለሶማሌላንድም የሚሰራ ነው። ምናልባት ከኤርትራ ፣ ከኬንያ ፣ ከጅቡቲ ስምምነት ቢደረግ ይሄ ይሰራል።

ፈጥኖ መግባባት ላይ የደረሰው #ከሶማሌላንድ ጋር ስለሆነ ነው እንጂ ንግግሩ ከሁሉም ሀገራት ጋር ይቀጥላል። የአሁኑ ብቻ በቂ ስላልሆነ ከሌላውም ጋር እንነጋገራለን።

በ50 ዓመቱ መግባቢያ ስምምነት ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ድርሻ ይኖራቸዋል ብለናል። ድርሻው ስንትነው ? የሚለው ተዘርዝሮ አልተቀመጠም። እኛ ለእነሱ የምንከፍለው #ሊዝ / #ኪራይ ዋጋው ስንት ነው የሚለውን ገና አልጨረስንም። ስንጀምረው ስምምነት በሚሆን መንገድ ላይ ጀምረን እነዚህ ጉዳዮች ስላላለቁ ነው ወደ መግባቢያ ሰነድ (MOU) የተመለሰው።

ገና ዝርዝር ነገሮች ያስፈልጋሉ ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ትክክለኛ አቅሙ፣ በገበያ ዋጋ ሲተመን ስንት ነው የሚለው ዝርዝር ተሰርቶ ወደ ንግግር ይገባል። እኛ የምንሰጠው ስንትነው የሚለው በሊዝ ከሚገኘው ዋጋ አለመብለጡን ማረጋገጥ ያስፈልጋል።

አሁን #በቀጠናው በሊዝ የተከራዩ በርካታ ሀገራት አሉ ፤ ጅቡቲ እንኳን በደርዘን የሚቆጠሩ ሀገራት ቤዝ አላቸው በሊዝ የሚጠቀሙት ስለዚህ ትልቁን የሚከፍሉት ስንት ነው ? ለምን ? ትንሹን የሚከፍሉት ስንትነው ? ለምን ? አማካዩ ስንት ነው ? እኛ ካለን ቅርበትና ከምንሰጠው አገልግሎት ተያይዞ ስንት ነው የምንከፍለው የሚለው ይቀመጣል። ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ስንት ብንሰጥ ነው ተመጣጣኝ የሚሆነው የሚለው ዝርዝር ስራ ይፈልጋል። በዚህ ምክንያት ወደ MOU ተመልሷል።

በሌሎች ሴክተሮች ላይ የተሟላ ትብብር ማድረግ አለብን ፦
• በጤና ፣
• በትምህርት፣
• በውጭ ጉዳይ፣
• በከተማ ልማት
... በእነዚህ እራሳቸውን የቻሉ #ስምምነቶች መዘጋጀት አለባቸው ይሄም ገና አላለቀም።

በአጠቃላይ የመግባቢያ ሰነዱ ፦

* መሬት ከሶማሌላንድ በኪራን እንደምናገኝ
* መሬቱን እራሳችን እነምናለማው
* መሬቱን 50 ዓመታትን እንደምንገለገልበት ፤ እሱን የሚያስችል ክራዩንም የሚመጥን ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ ድርሻ #እንደምንሰጥ ይስቀምጣል።

ከዚህ ባለፈ ...

ለ30 ዓመታት #የተሟላ እውቅና ሳያገኙ ሀገር ሆነው ቆይተዋል። እውቅና ለማግኘት ይሞክራሉ ፤ ይሄን በተመለከተ የኢትዮጵያ አቋም ምን ይሆናል ? የሚለው ጉዳይ ይነሳል።

' ወደ ተሟላ ስምምነት ደርሶ፣ መሬቱን ተረክበን ሂደቱ ሲቋጭ እነሱ እውቅና ለማግኘት የሚያደርጉትን ጥረት በተመለከተ ኢትዮጵያ #አቋም_ትወስዳለች የሚል አመላካች ነገሮች ነው ያሉት ሰነዱ።  '

አሁን ላይ ስምምነት ሆኖ አልተረከብንም ፣ ስምምነት ሆኖ አልሰጠንም። #መስማማት እንዳለብን ግን ተስማምተናል ፤ እሱንም በመግባቢያ ሰነድ ፈርመናል።

#AmbassadorRedwanHussein

@tikvahethiopia
#ሶማሌላንድ

" ከአካባቢው ጋር በተያያዘ ሰፊ ሌላ ዓላማ ላላቸው #ግብፆች ምን አስጨነቀን ? " - አምባሳደር አብዱላሂ ሞሀመድ

ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ የተፈራረሙትን የመግባቢያ ስምምነት ለማጠናቀቅ " አሁን ከሁለቱም ወገኖች የቴክኒክ ኮሚቴ በመዋቀር ላይ ነው " ሲሉ በኢትዮጵያ የሶማሊላንድ ተወካይ አምባሳደር አብዱላሂ ሞሀመድ ተናገሩ።

አምባሳደር አብዱላሂ ይህን ያሉት ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ነው።

የሶማሊላንዱ ተወካይ ፦ " ጉዳዩን ለማጠናቀቅ አሁን ከሁለቱም ወገኖች የቴክኒክ ኮሚቴ በማዋቀር ላይ ነን። እና ይህ ቀድሞውኑ በሂደት ላይ እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ።

(ፊርማውን ትከትሎ) ግንኙነቶች ነበሩ። በሁለቱ ሀገሮች መካከል ጉብኝቶች ነበሩ።

የውጭ ጉዳይ እና የአለም አቀፍ ግንኙነት ሚኒስትራችን ባለፈው ሳምንት ነው የተመለሱት። እሳቸው እዚህ (አዲስ አበባ) ከእኔ ጋር ነበሩ። ዋና ተግባራቸውም ጉዳዩ መሠረት እንዲይዝ ከኢትዮጵያ አቻዎቻቸው ጋር ለመምከር ነበር።

ይዋል ይደር እንጂ ሁለቱ ኮሚቴዎች ወደ ስራ እንዲገቡ እናደርጋለን። ስለዚህ ይህ በጣም በቅርቡ ይከናወናል ብዬ አስባለሁ " ብለዋል።

ሶማሊላንድ አለምአቀፍ እውቅና ያገኘ ባይሆንም ባለፉት 30 ዓመታት ፦
* ራሱ የሚቆጣጠረው ድንበር ፣
* የራሱ ሰንደቅ ዓላማ ያለው
* ምርጫ ሲያካሂድ የነበረ ፣
* ሕዝቡንም ሲያስተዳድር የቆየ መንግሥት መሆኑን ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ከሶማሊያ እና ሌሎች ሀገሮች የተነሳውን ተቃውሞ እንዴት እንደሚመለከቱት የተጠየቁት አምባሳደሩ ፦ " የዓረብ ሊግ፣ ግብፅና ሶማሊያን በተመለከተ፣ በኔ እምነት በዚህ ረገድ ምንም ማድረግ የማይችሉ ይመስለኛል። ያለቀለት የተደመደመ ጉዳይ ነው። ከአካባቢው ጋር በተያያዘ ሰፊ ሌላ ዓላማ ላላቸው ግብፆች ምን አስጨነቀን " ብለዋል።

በመግባቢያ ስምምነቱ መሠረት ሶማሌላንድ በአፀፋው ምን ታገኝ እንደሆንም ተጠይቀው ፥ " ለሶማሌላንድ ዕውቅና መስጠት። ይህ እርግጥ ነው። የዚህ ፕሮግራምም አካል ነው። የስምምነቱም ክፍል እና አካል ነው " ብለዋል።

አምባሳደር አብዱላሂ ሶማሊያ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የቀጣናው አለመረጋጋት ምንጭ ናት ብለዋል።

ይልቁንም ሶማሊላንድ ለቀጣናው መረጋጋት ጉልህ ድርሻ ያላት መሆኑን ገልፀዋል።

" ኢትዮጵያም፣ ድንበሯም እንዲከበር እንጠብቃለን። ሁለተኛ ፣ ሶማሊላንድ በሕግ የፀና እውቅና ያለው ግዛት ሆኖ መታወቅ አለበት። ምክንያቱም እኛ የአካባቢው ጂኦ ፖለቲካዊ መረጋጋት አካል እና ባለድርሻ ነበርን። ባለፉት አመታት አልሸባብን እና ሽብርተኝነትን እየተዋጋን ነበር። " ብለዋል።

የሶማሊላንድ የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር አብዱላሂ ሞሀመድ ፤ " ሶማሊላንድ የሌሎች ሀገሮችም ድጋፍ አላት " ሲሉ ተናግረዋል።

" ሶማሊላንድ በቀጣዩ የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ይህንን ጉዳይ በሚገባ ትይዘዋለች " ያሉት አምባሳደሩ ፤ " ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ወዳጆችም አሉን። ከ5 የተለያዩ ክልሎች፤ ለጉዳያችን በጣም በጣም አዎንታዊ አመለካከት ያላቸው አባል ሀገራት (የአፍሪካ ሕብረት) አሉን። " ብለዋል።

" እኛ ሕጋዊ ጉዳይ አለን ፣ የሞራል ጉዳይም አለን ፣ የሚቀረው የፖለቲካ ጉዳይ ብቻ ነው። ለአካባቢው እና ለአህጉሪቱ የምናደርገው በጎ አስተዋፅኦ ተዘንግቷል። የትኛውም አካል የህዝባችን ውሳኔ ላይ ሊወስን አይችልም። ህዝባችን ሕዝበ ውሳኔ አድርጎል። 97.5 በመቶው ነፃ ሀገር መሆንን በመደገፍ ድምጽ ሰጥቷል " ሲሉ ሃሳባቸውን ደምድመዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ ቃለምልልስ እና መረጃ የዶቼ ቨለ ሬድዮ መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊያ መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት #ለማቋረጥ በመወሰን በአገሪቱ የሚገኙ የኢትዮጵያ አምባሳደር እና ዲፕሎማቶች ለቀው እንዲወጡ ማዘዟ ተሰምቷል። አዲስ አበባ ያሉትን አምባሳደሯንም ጠርታለች። የሶማሊያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሚኒስቴር ይፋ እዳደረገው በሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር…
#Update

" የቀን ህልም ነው ... ምንም የማይረባ ፤ እኛን አያሳስበንም " - ሶማሌላንድ

" የሶማሊያ መንግሥት አንዳች ስልጣን የለውም " - ፑንትላንድ

#ፑንትላንድ እና #ሶማሌላንድ የሶማሊያ ፌዴራል መንግሥትን ማስጠንቀቂያ ውድቅ አደረጉ።

የሶማሊያ መንግሥት ፤ #ኢትዮጵያ ከሶማሌላድ ጋር ያደረገችውን የመግባቢያ ስምምነት ምክንያት በማድረግና " በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ እየገባሽ ነው " በማለት ሞቃዲሹ ያሉት የኢትዮጵያ አምባሳደር በ72 ሰዓታት ውስጥ ከሀገሪቱ ለቀው እንዲወጡ አዟል።

ከዚህ ባለፈ ግን በሶማሌላድ ፣ #ሀርጌሳ እና በፑንትላንድ፣ #ጋሮዌ የሚገኙት የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤቶች በ7 ቀን እንዲዘጉ አስጠንቅቋል። ኢትዮጵያ ዲፕሎማቶችም በ1 ሳምንት ውስጥ ሀገር ለቀው እንዲወጡ አዟል። ካልሆነ ወደሌላ እርምጃ ገባለሁ ብሏል።

ለዚህ ማስጠንቀቂያ ፑንትላንድ እና ሶማሌላንድ ምላሽ ሰጥተዋል። የሶማሊያ ፌዴራል መንግስትን ማስጠንቀቂያም ውድቅ አድርገዋል።

ዛሬ ምሽት ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ሶማሊኛ ክፍል አጭር ቃላቸውን የሰጡት የሶማሌላንድ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚንስትር አምባሳደር ሮዳ ጃማ ፥ " የቀን ህልም ነው፤ ...ምንም የማይረባ ፤ እኛን አያሳስበንም " ሲሉ ማስጠንቀቂያውን አጣጥለዋል።

የሶማሊያ መንግሥት ስልጣኑ በቪላ ሱማሊያ እና በሙቃዲሾ ዘሌን ቤዝ የተወሰነ መሆኑን በመግለጽ " በውስጥ ጉዳዩ ላይ ቢያተኩር ነው የሚሻለው ... ከአቅሙ በላይ በሆነ ጉዳይ ጊዜ ማባከኑን ማቆም አለበት " ብለዋል።

የፑንትላንድ የማስታወቂያ ሚኒስትር ማህሙድ አይዲድ ድሪር  በበኩላቸው " የሶማሊያ ፌደራል መንግስት በጋሮዌ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት የመዝጋት አንዳችም ስልጣን የለውም " ብለዋል።

@tikvahethiopia
#CPPI #WorldBank

የዓለም ባንክ ከኤስ ኤንድ ፒ ግሎባል ማርኬት ኢንተለጀንስ ጋር የሚያዘጋጀው የኮንቴይነር ወደብ የአፈጻጸም መለኪያ (Container Port Performance Index - CPPI) የ2023 ደረጃ ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርጓል።

ይህ መለኪያ ወደቦች የመረከብ አቀባበላቸውንና እንዴት እንደሚያስተናግዱ በአጠቃላይ ያላቸውን የስራ ቅልጥፍና እና አፈጻጸም የሚለካ ነው።

በዚህም ከ409 ወደቦች የራስ ገዟ #ሶማሌላንድ " #በርበራ " ወደብ 106ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

የሶማሊያ ፤ " #ሞቃዲሾ " ወደብ ደግሞ 166ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

የ " #ጅቡቲ " ወደብ ከመጨረሻ ተርታ 379ኛ ደረጃ ላይ ነው የተቀመጠው።

በዚህ የዓለም ባንክ የአፈጻጸም መለኪያ የበርበራ ወደብ ከሞቃዲሾ እና ጅቡቲ ወደቦች የተሻለ ደረጃ ተሰጥቶታል።

በአጠቃላይ ዓለም አቀፍ ደረጃ ከተሰጣቸው ከ405 ወደቦች በመጨረሻ ተርታ ማለትም 379 ላይ የተቀመጠው የጅቡቲ ወደብ በሀገሪቱ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ ፈጥሯል።

የጅቡቲ ወደብ በ2022 ከዓለም የተሰጠው ደረጃ 26ኛ ሲሆን በ2023 መለኪያ 379ኛ ላይ መቀመጡ ጅቡቲን አላስደሰተም።

ሀገሪቱ " የ2023 ደረጃ አሰጣጥ ምክንያታዊነት የጎደለው በመሆኑ ያሳስበናል " ያለች ሲሆን " ምን አይነት ሳይንስ ነው የሚያብራራው በዓለም ደረጃ ከ350 በላይ ነጥብ መጣል ? " ስትል ጠይቃለች።

በአንድ ዓመት ውስጥ እንዲህ ያለው ደረጃ መሰጠቱ በመለኪያው ላይ የተዓማኒነት ጥያቄ እንደሚያስነሳ ገልጻለች።

ጅቡቲ ፥ " ደረጃ አሰጣጡ ነጻ እና ከተእጽኖ የጸዳ ነው ወይ ? " ስትል ጠይቃ " ለማንኛውም አድሏዊም ሆነ አልሆነ ጅቡቲ ከሰሃራ በታች እና ምስራቅ አፍሪካ ትልቁ እና ቀልጣፋ ማዕከል ናት " ብላለች።

ሙሉ ዶክመንቱን በዚህ ያግኙ ➡️ CPPI 2023

#WorldBank

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሶማሊያ ?

ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ #ሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች ወዲህ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት አሻክራለች።

የሀገሪቱ ፕሬዜዳንትም በየጊዜው በተለይ ወደ ግብፅ ሲመላለሱ ነው የከረሙት።

በቅርብ ደግሞ ግብፅ ሄደው ከፕሬዜዳንት አልሲሲ ጋር ወታደራዊ ስምምነት ፈጽመው ነው የመጡት።

ትላንት ደግሞ የጦር መሳሪያዎችን የጫኑ ሁለት የግብጽ የጦር አውሮፕላኖች በሞቃዲሾ ገብተዋል።

ጥይት እና የተለያዩ መሳሪያዎች ናቸው ተብሏል።

የዲፕሎማቲክ ምንጮች ግብፅ ለሶማሊያ ያደረገችው ወታደራዊ ድጋፍ ነው ብለዋል።

ግብፅ በሶማሊያ በሰላም ማስከበር ስም ወታደሮቿን ለማሰማራትም ጠይቃለች።

ቪድዮ፦ ሀሩን ማሩፍ

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ ፦ ይህ #ድብድብ ከሶማሊያ ተገንጥላ ራሷን በምታስተዳድረው #ሶማሌላንድ ፓርላማ ውስጥ የተከሰተ ነው።

ምንድነው የተፈጠረው ?

ዛሬ የፓርላማ አባላቱ ሞሃመድ አቢብ በተባለ የፓርላማ አባል ያለመከሰስ መብት መነሳት ጉዳይ አስቸኳይ ስብሰባ ነበራቸው።

ሞሀመድ አቢብ እጅግ የሚታወቁና አውዳል ላይ ብዙ ተከታይ ያላቸው ፖለቲከኛ ሲሆኑ ገዢዎችን በመኮነን ለውጥ እንዲመጣ የሚታገሉ ናቸው ይባልላቸዋል።

የሶማሌላንድ መንግሥት እኚህን ፖለቲከኛ ከዛሬ 3 ቀን በፊት ከተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ፣ ዱባይ ሲመለሱ ሀርጌሳ ኤርፖርት ላይ ጠብቆ አስሮ እስር ቤት አስገብቷቸዋል።

ያሰራቸው በሀገር ክህደት እና የሶማሌላንድ ሪፐብሊክን ከሚቃወሙ ቡድኖች ጋር አብረዋል በሚል ነው።

ይህ በደጋፊዎቻቸው ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል።

መንግሥት ፓርላማውን አስቸኳይ ስብሰባ አስቀምጦ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ በጠቅላይ አቃቤ ሕግ የውሳኔ ሀሳብ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም ከተገኙት 57 አባላት ውስጥ 51 አባላት ተቃውመዋል።

ታዲያ በዚህ ጉዳይ ላይ ነው ፓርላማ ውስጥ ክርክር ሲደረግ በሁለት አባላት መካከል የለየለት ድብደብ እና የቡጢ መሰነዛዘር፣ እቃ መወራወር የደረሰ መነጋገሪ ክስተት የተከሰተው።

ተደባዳቢ የፓርላማ አባላቱ መጎዳታቸው ተነግሯል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia