TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ምርጫ2013

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከጥቂት ደቂቃ በኃላ መግለጫ ይሰጣል።

መግለጫውን የሚከታተሉ የቲክቫህ አባላት በቦታው ይገኛሉ።

መግለጫውን በቀጥታ በ Voice Chat መከታተል እንደምትችሉ ከወዲሁ ለማሳወቅ እንወዳለን።

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ።

ቦርዱ በተለያዩ ምክንያቶች የሁሉንም የምርጫ ክልሎች ውጤት በአስር ቀናት ውስጥ መግለጽ እንዳልቻለ አስታውቀዋል።

- የመደመር ሂደቶች አለመጠናቀቅ፣
- በትራንስፖርት ችግር ወደ ማዕከል ውጤት ተጠቃሎ አለመድረሱ
- የፖለቲካ ፖርቲዎች አቤቱታ ባቀረቡባቸው የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ማዕከል ተጠቃሎ አለመድረስ ለመዘግየቱ በምክንያትነት አንስተዋል።

ለቦርዱ ውጤት አያድርሱ እንጂ ምርጫ ክልሎቹ በአካባቢያቸው የምርጫ ውጤት የተለጠፈ መሆኑን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።

እስካሁን የ26 ምርጫ ክልሎች ውጤት ገና ለቦርዱ ጽሕፈት ቤት እንዳልደረሰ ገልፀዋል።

በአፋር ክልል 7 እና በአዲስ አበባ 8 ምርጫ ክልሎች ውጤት ካላሳወቁት መካከል ይገኙበታል፡፡

ከላይ ባለው Voice Chat 'Join' በማለት በቀጥታ ማዳመጥ ትችላላችሁ::

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

ተጨማሪ #የተረጋገጡ የምርጫ ውጤቶችን የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ እያሳወቁ ይገኛሉ።

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

(ሰኔ 28 ቀን 2013 ዓ/ም)

ውድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከደቂቃዎች በኃላ መግለጫ ይሰጣል።

መግለጫውን የሚከታተሉ የቤተሰባችን አባላት በቦታው ተገኝተዋል።

መግለጫውን በVoiceChat መከታተል እንደምትችሉ ከወዲሁ እናሳውቃለን።

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013 አጫጭር መረጃዎች ፦

- ምርጫ ቦርድ የተጠቃለለ የምርጫ ውጤት በዚህ ሳምንት አሳውቃለሁ ብሏል። ከዚህ ቀደም ለቦርዱ ያልደረሱ 30 የምርጫ ውጤቶች አሁን ላይ ተጠቃለው ገብተዋል።

- የቁጫ ምርጫ ክልል የድምጽ ቆጠራ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባሉበት በአዲስ አበባ እየተደረገ ነው።

- ኦሮሚያ ክልል ነገሌ የምርጫ ክልል ድምፅ ባልተሰጠባቸው 30 የምርጫ ጣቢያዎች በቀጣይ ሀሙስ ድምጽ ይሰጣል።

- የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዜዳንት እና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ምርጫ በተወዳደሩበት ኦሮሚያ ክልል ጎማ ቁጥር 2 በሰፊ ድምፅ አሸንፈዋል።

- ዛሬ ይፋ በተደረጉ የተረጋገጡ የምርጫ ውጤቶች የአብኑ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተወዳደሩበት በአማራ ክልል ባህርዳር ከተማ ምርጫ ክልል ማሸነፋቸው ተገልጿል።

- ከምርጫው ቀን አንስቶ ከቆጠራ እና ድመራ ጋር በተያያዘ በ153 የምርጫ ክልሎች 31 ፓርቲዎች፣ 7 የግል ተወዳዳሪዎች በጽሁፍ፣ ስልክና በSMS አቤቱታ አቅርበዋል። ምርጫ በተካሄደባቸው በሁሉም ክልሎች ቅሬታ ቀርቧል።
• በአማራ ክልል 49 ምርጫ ክልሎች፣
• በደቡብ ክልል 40 ምርጫ ክልሎች
• በአዲስ አበባ ከተማ በሁሉም ምርጫ ክልሎች
• በአፋር ክልል በ21 ምርጫ ክልሎች በርካታ ቅሬታ የቀረቡባቸው ናቸው።

#SolainaShimeles #NEBE

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

በዛሬው ዕለት በነገሌ ምርጫ ክልል ለህዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤቶች የሚወዳደሩ ዕጩዎች ምርጫ እየተካሄደ ነው።

ምርጫው ከጠዋት 12 ሰዓት ጀምሮ ነው እየተካሄደ ሚገኘው።

ለምርጫው ከ150 በላይ ታዛቢዎችና የምርጫ አስፈጻሚዎች መመደባቸውን ተገልጿል።

በምርጫ ክልሉ ለሁለቱም ምክር ቤቶች ሁለት በግል፣ አንድ ከኢዜማ እንዲሁም አራት ከብልጽግና ፓርቲ ዕጩዎች ለውድድር ቀርበዋል። #ENA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከ20 ደቂቃ በኃላ የምርጫውን ውጤት ይፋ ያደርጋል። NB : ውድ የቲክቫህ ቤተሰቦች ምርጫ ቦርድ ውጤት በሚያሳውቅበት ሰዓት የ"Voice Chat" ዳግም የሚጀምር ይሆናል። @tikvahethiopia
#ምርጫ2013

ከ20 ደቂቃ በኋላ ይጀምራል ተብሎ የነበረው የምርጫ 2013 ውጤት መግለጽ መርኃግብር መዘግየት ገጥሞታል።

ምክንያቱን ለማወቅ ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።

በአሁን ሰዓት የዕለቱ የክብር እንግዳ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በአዳራሹ ተገኝተዋል።

የውጤት ማሳወቁ ሂደት ተጀምሯል። ከላይ በ Voice Chat ያዳምጡ።

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

በምርጫ ላይ 2013 በምርጫ አስፈፃሚነት ሀገራቸውን ያገለገሉ ዜጎች ክፍያ እንደዘገየባቸው ጠቁመዋል።

የምርጫ አስፈፃሚዎች " ክፍያ ዘገየብን ፤ ለመዘግየቱ ምክንያት ምንድነው ? መቼ ነውስ ክፍያው የሚፈፀምልን ?" ሲሉ ጥያቄያቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ልከዋል።

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ምላሽ የጠየቅናቸው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የኮሚኒኬሽ አማካሪ የሆኑት ወይዘሪት ሶሊያና ሽመልስ ክፍያው የዘገየው ፥
- ንብረት ርክክብ መጠናቀቅ ስላለበት፣
- የበጀት መዝጊያ ስለሆነም መልሶ መከፈት ስላለበት፣
- የመጨረሻው ክፍያ ስለሆነ
- በድምፅ መስጫ ቀን ሰው ስለተጨመረ ቁጥሩ ብዙ በመሆኑ ነው ብለዋል።

ወ/ሪት ሶሊያና ፥ የምርጫ አስፈፃሚዎች ክፍያ እንደተለመደው እንደሚከፈል የገለፁልን ሲሆን መታገስ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስድስተኛውን አጠቃላይ ምርጫን በዋናነት ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ማስፈፀሙ ይታወሳል።

- በመራጮች ምዝገባ ሂደት ላይ በታዪ ጉልህ ግድፈቶች፣
- በመራጮች ምዝገባ ላይ በቀረቡ አቤቱታዎችን ለማጣራት ጊዜ በማስፈለጉ
- ከጸጥታ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች የተነሳ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ድምፅ አሰጣጥ ያልተደረገባቸው ቦታዎች እንዳሉ ይታወቃል።

በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድ ቀሪ ምርጫ ያልተከናወነባቸው የምርጫ ክልሎችን፣ የምርጫው ሂደት ያለበትን ሁኔታ እና የመሳሰሉትን በመገምገም ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

* ውሳኔዎቹን ከላይ በተያያዘው ምስል ያንብቡ።

@tikvahethiopia