TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#EU #AU

የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ቻርለስ ሚሼል ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ተወካይ ከሆኑት ከቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ ጋር ተገናኝተው መከሩ።

ቻርልስ ሚሼል እንደገለፁት ከሆነ ምክክሩ በትግራይ ግጭት ዙሪያ ሲሆን ፤ ዘላቂ እና ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት በሚደረግ አስቸኳይ ጥረት ላይ ነው ትኩረቱን አድርጎ የነበረው።

የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ፤ " የቀጠናውን መረጋጋት ለማረጋገጥ የአውሮፓ ህብረት ከአፍሪካ ህብረት ጋር በቅርበት ለመስራት ዝግጁ ነው " ብለዋል።

@tikvahethiopia
#AU

የአፍሪካ አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አዲስ አበባ መግባት ጀመሩ።

የአፍሪካ አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ለ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል።

የሕብረቱ ኮሚሽን የሚያዘጋጀው የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ጥቅምት 4 እና 5 ቀን 2014 ዓ.ም በአፍሪካ ሕብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል።

በስብሰባው ለመሳተፍ የላይቤሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲ-ማክስዌል ሳህ ኬማያ ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ገብተዋል።

በ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ የሕብረቱ 55 አባል አገራት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

የምክር ቤቱ ስብሰባ የአገራት መሪዎች፣ የአፍሪካ ሕብረት ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማኀበረሰብ ተቋማትና በሕብረቱ ስር የሚገኙ ተቋማት የሚያደርጉት በሶስተኛው አጋማሽ ዓመት ለሚያደርጉት ጥምር ውይይት አጀንዳዎች የሚቀርቡበት ነው።

Credit : ENA

@tikvahethiopia
#AU : የአፍሪካ ህብረት ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለውን ግጭት እየተሳተፉ የሚገኙ አካላት በመጨረሻ ወደ ጠረጴዛ ይመጣሉ የሚል ከፍተኛ ተስፋ እንዳለው አስታወቀ።

አፍሪካ ህብረት ይህን ያስታወቀው ፥ በህብረቱ የፖለቲካ ጉዳዮች እንዲሁም የሰላምና ደህንነት ኮሚሽነር ባንኮሌ አዶየ በኩል ነው።

ኮሚሽነሩ ለአል-ዐይን ኒውስ በሰጡት ቃል ፥ " በሰሜን ኢትዮጵያ ያለውን ግጭት መቋጫ እንዲያገኝ በህብረቱ በኩል ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው " ብለዋል።

የአፍሪካ ህብረት ከመጀመርያው አንስቶ ግጭቱን በትኩረት ሲከታተለው የነበረ ጉዳይ መሆኑን የገለፁት ኮሚሽነሩ የግጭቱን መጠን ከግምት ውስጥ በማስገባት “በቅርቡ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ተወካይ ተደርገው መሾማቸው” ህብረቱ ለጉዳዩ የሰጠውን ትኩረት የሚያመላክት ነው ብለዋል።

ህብረቱ በከፍተኛ ተወካዩ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ አማካኝነት የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት መፍትሄ እንዲያገኝ የኢትዮጵያ መንግስትን ጨምሮ ከተለያዩ አካላት ጋር እየመከረ መሆኑንም አሳውቀዋል።

እስካሁን እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች መሰረት “ሁሉም የግጭቱ ተዋናዮች በመጨረሻ ወደ ጠረጴዛ እንደሚመጡ ትልቅ ተስፋ አለን” ሲሉም ተናግረዋል።

የአፍሪካ ህብረት የሰሜን ኢትዮጵያን ግጭት እንዲፈታ በሶስት ቁልፍ ጉዳዮች እየመከረና በግጭቱ እየተሳተፉ ካሉ ኃይሎች ጋር እየተወያየ አንደሆነ ኮሚሽነሩ ጠቅሰዋል።

“ግጭቱን ማቆም፣ ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ ተደራሽነት እንዲኖር ማድረግ እና ዘላቂ የሆነ ፖለቲካ መፍትሄ ማባጀት” የሚሉ ዓበይት ነጥቦች ህብረቱ በኢትዮጵያ የተከሰተውን ግጭት እንዲቆም በተደጋጋሚ እና በቀጣይነት እየሰራባቸው የሚገኙ ጉዳዮች ናቸው ሲሉ ነው ኮሚሽነሩ የገለፁት።

Credit : አል ዐይን ኒውስ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ የሕብረቱ አባል አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ተወካዮች ተገኝተዋል። ሚኒስትሮች በስብሰባው ላይ ለመሳተፍ ትናትንና ከትናንት በስቲያ አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። የምክር ቤቱ ስብሰባ የአገራት መሪዎች፣ የአፍሪካ ሕብረት ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማኀበረሰብ ተቋማትና በሕብረቱ…
#AU : በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት የተካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በመምከር ትናንት ምሽት ተጠናቋል።

በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ለሁለት ቀናት የመከረው ስብሰባ ላይ የተሳተፉ የአፍሪካ አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችም ዛሬ ወደ አገራቸው ተመልሰዋል።

በ2 ቀኑ ውይይት የተዳሰሱት ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ አንኳር ጉዳዮች ናቸው።

Credit : ENA

@tikvahethiopia
ከሰሞኑን ተከታትለው የወጡት የተኩስ አቁም ጥሪዎች !

በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ከጀመረ ሰዓት አንስቶ የተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት ተኩስ እንዲቆም ጥሪ ሲያቀርቡ እንደነበር አይዘነጋም።

ከሰሞኑን ደግሞ የተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት በተከታታይ የተኩስ አቁም እና የድርድር ጥሪዎችን ሲያቀርቡ ተስተውሏል።

1ኛ. #ሩሲያ፦ በድጋሚ ተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ ጠይቃለች።

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች በአስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

ሩሲያ የኢትዮጵያን ጉዳይ እየተከታተለች እንደሆነ ገልፃለች ፤ ሰሞኑን በደሴ እና በኮምቦልቻ ከተሞች የተካሄዱት ጦርነቶች የሲቪል ዜጎችን ህይወት ጎድቷል ብለዋል።

ሩሲያ #የኢትዮጵያን_ግዛት_አንድነት መከበር ለድርድር የማይቀርብ እና ግጭቱን መፈቻ መንገድ ሊሆን እንደማይችል ታምናለች ብለዋል።

2ኛ. #ኬንያ ፦ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ ያለውን ግጭት ለማስቆም ኢትዮጵያውያን እንዲወያዩ አሳስበዋል።

ኬንያታ የኢትዮጵያ ተፋላሚ ወገኖች ድርድር ይጀምሩ ሲሉ ጠይቀዋል።

ህወሓት እና ኦነግ ሸኔ የፌደራል መንግስቱን ለመውጋት ቅንጅት መፍጠራቸው ጦርነቱ ሌላ መልክ እንዲኖረው እና እንዲራዘም እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በፌደራል መንግስቱ እና በህወሃት መካከል እስካሁን ትርጉም ያለው ድርድር አለመጀመሩ ጦርነቱ ከአንድ ዓመት በላይ እንዲቀጥል አድርጎታል ብለዋል ኡሁሩ።

ኬንያን ጨምሮ አፍሪካ እና ዓለም ሰላማዊ ኢትዮጵያን ማየት ይፈልጋል ያሉም ሲሆን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ተመካክሮ ለአገሩ ሰላም መፍትሄ እንዲፈልግ ጠይቀዋል።

3ኛ. #ኢጋድ ፦ የኢጋድ ዋና ፀሃፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጦርነት እንዲቆምና አስቸኳይ ተኩስ አቁም ላይ እንዲደረስ ጥሪ አቅርበዋል።

ዶ/ር ወርቅነህ ፥ እየከረረ መጥቷል ያሉትን የኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ በከፍተኛ ስጋት እየተከታተሉ እንደሆነ አስታውቀዋል።

ኢጋድ ጦርነቱ በተጀመረበት ወቅት ባለፈው ዓመት ሁኔታውን በማስመልከት ጥሪ ማቅረቡን ያስተወሱት ዶ/ር ወርቅነህ ጦርነቱ እንዲቆምና በአስቸኳይ ተኩስ አቁም እንዲደረግ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።

ሁሉም ወገኖች ከግጭት ተቆጥበው በመካከላቸው ያለውን መካረር እንዲያረግቡ እና ልዩነቶቻቸውን ለሃገሪቱ ብሎም ለቀጠናው በሚበጅ መልኩ በውይይት እና እርቅ እንዲፈቱ ጥሪ አቅርበዋል።

4ኛ. #ዩጋንዳ ፦ ፕሬዝደንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) አባል ሐገራት መሪዎች ጦርነቱ ሥለሚቆምበት ሁኔታ ለመነጋገር እንዲሰበሰቡ ጠይቀዋል።

5ኛ. #አሜሪካ ፦ ዛሬም (ጥቅምት 26) አሜሪካ በድጋሚ በኢትዮጵያ ተኩስ ይቆም ዘንድ ጥሪ አቅርባለች።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በኢትዮጵያ ያለው ግጭት ማብቃት አለበት ፤ አሁኑኑ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሰላም ድርድር መጀመር አለበት ብለል፤ ተኩስ እንዲቆምም ጠይቀዋል።

6ኛ. #AU ፦ የአፍሪካ ህብረት (AU) ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት በኢትዮጵያ ያለው ወታደራዊ ግጭት መባባስ እንዳሳሰባቸውና በቅርበትም እየተከታተሉት እንደሆነ ገልፀዋል።

ጦርነቱ በተቀሰቀሰበት ሰሞን ያወጡትን መግለጫ በማስታወስ የጦርነቱ ተሳታፊ ሁሉም ወገኖች የኢትዮጵያን ግዛት አንድነት፣ ብሄራዊ ሉዓላዊነት እንዲጠብቁ በድጋሚ አሳስበዋል።

በአገር ጉዳይ ላይ ሰላማዊ መፍትሄ ለመፈለግ ሁሉም ወገኖች ወደ ውይይት እንዲገቡም አሳስበዋል።

ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲቆም፣ የዜጎች ህይወትና ንብረት ሙሉ በሙሉ እንዲከበር፣ እንዲሁም የመንግስት መሠረተ ልማት እንዲከበር ጥሪ አቅርበዋል።

የጦርነቱ ተሳታፊ ወገኖች ደጋፊዎቻቸው በማንኛውም ማህበረሰብ ላይ የበቀል እርምጃ እንዳይወስዱ እንዲሁም ከጥላቻ ትርክቶች፣ ክፍፍልንና ግጭቶችን ከሚያበረታቱ ሁኔታዎች እንዲቆጠቡ እንዲያደርጉም አሳስበዋል።

በሌላ መረጃ ፦

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በስልክ መነጋገራቸውንና ለድርድር የሚሆን ማንኛውንም ድጋፍ እንደሚሰጡ እንደገለጹላቸው አሳውቀዋል።

ምንጭ፦ UN ፣ AU ፣ ኢጋድ ፣ አል አይን ኒውስ ፣ Daily Nation ፣ António Guterres (Twitter) ፣ BBC ፣ Antony Blinken (Twitter)

@tikvahethiopia
#AU

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የአፍሪካ ኅብረት አባል ሀገራት መሪዎች ተስማምተው የኅብረቱ ጉባኤ በአዲስ አበባ እንዲደረግ በመወሰናቸው በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል።

የኅብረቱን ጉባኤ በአካል በአዲስ አበባ ለማከናወን ያሳለፉትን ውሳኔ ኢትዮጵያ ታደንቃለች ብለዋል።

ዶ/ር ዐቢይ ፥ " ወንድማዊ አጋርነታችሁን በምንሻበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ የኮሮናን መስፋፋትንና ወቅታዊውን የጸጥታ ሁኔታ እንደ ምክንያት በማንሣት የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ በአዲስ አበባ እንዳይካሄድ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበሩ አካላት ተግባራቸው ኢትዮጵያን አሳዝኖ ነበር " ብለዋል።

አክለው ፥ " በዓመት ሁለት ጊዜ ከሚደረጉት የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤያት መካከል በኮሮና ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የመጀመሪያው ጉባኤ ከ3 ዓመት በኋላ ዳግም በአዲስ አበባ እንዲካሄድ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራትና ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ጋር በመሆን መንግስት ልዩ ልዩ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችን ሲያደርግ ቆይቷል። " ሲሉ አስረድተዋል።

ዶክተር ዐቢይ፥ " ጉባኤው እዚህ መካሄዱ የሚኖረውን ትርጉም የተገነዘቡና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያላትን ጠንካራ አቋም፣ ለአፍሪካ ኅብረት እውን መሆን ያበረከተችውን አስተዋጽኦ እና የአፍሪካ ጉዳዮች በአፍሪካውያን እንዲታዩ ያላትን የጸና መርሕ ከፍ ያለ ዋጋ የሰጡ የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤው በአዲስ አበባ መካሄዱን መርጠዋል። በዚህም ኢትዮጵያ ደስ ተሰኝታለች፤ እንኳን ደስ ያለን " ሲሉ ገልፀዋል።

* ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
#AU #SUDAN

የአፍሪካ ህብረት (AU) ኮሚሽን ሊቀ መንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሀመት ትላንት አዲስ አበባ ከገቡት የሱዳን ሉአላዊ የሽግግር ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) ጋር ተወያይተዋል።

ሊቀመንበሩ ፤ ውይይቱ የነበረው አሁን ላይ በሱዳን ስላለው አሳሳቢ ሁኔታ መሆኑን ገልፀዋል።

@tikvahethiopia
#AU

የአፍሪካ ህብረት ሰንደቅዓላማ ...

የአፍሪካ የራሱ ሰንደቅዓላማ ያልነበረው ሲሆን በ2004 ግን መለያ ሰንደቅዓላማ አዘጋጅቶ ነበር።

በ8ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እኤአ ጥር 29 እና 30 ቀን 2007 በአዲስ አበባ ሲካሄድ ነባሩን ሰንደቅዓላማ የሚተካ አዲስ የህብረቱ ሰንደቅዓላማ እንዲዘጋጅ ውሳኔ ተላለፈ።

በወቅቱ የሊቢያ መሪና የህብረቱ ሊቀመንበር ሙአመር ጋዳፊ የሚመራው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ኃላፊነቱን ወስዶ ለህብረቱ ሰንደቅዓላማ ንድፍ መስራት ለሚፈልጉ ጥሪ አቀረበ።

የኮሚሽኑን ጥሪ ተከትሎ ከ19 የአፍሪካ ሀገራት ከ100 በላይ ግለሰቦች፣ ከዳያስፖራ 2 ግለሰቦች ከ100 በላይ ንድፎችን አስገቡ።

የሰንደቅዓላማ ንድፎቹ በባለሙያዎች ተመዘኑ። በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት አሜሪካዊ የሆነው የግራፊክ ጠቢብ ያዴሳ ቦጂያ ያቀረበው ንድፍ አሸናፊ ሆነ።

ያሸነፈው የያዴሳ ንድፍ ሰንደቅዓላማ እንዲሆን እኤአ ጥር 31 ቀን 2010 በአዲስ አበባ በተካሄደው 14ኛው መደበኛ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ተወሰነ።

ያዴሳ ቦጂያ ያረቀቀውና አሁን በስራ ላይ ያለው የህብረቱ ሰንደቅዓላማ አረንጓዴ መደብ፣ በ55 ወርቃማ ኮከቦች የተከበበችና በነጭ የፀሐይ ጨረሮች ላይ ያረፈች አረንጓዴ የአፍሪካ ካርታን የያዘ ነው።

የአፍሪካ ካርታ በአረንጓዴ መወከሉ አህጉራዊ ተስፋን ለማሳየት ሲሆን፣ ነጭ የፀሐይ ጨረሮች ደግሞ አፍሪካውያንን ከተቀረው ዓለም ጋር በወዳጅነት፣ በጋራ የመኖር ግልፅ ፍላጎትን የሚያሳይ ነው።

አረንጓዴው የአፍሪካ ካርታ በ55 ወርቃማ ኮከቦች የተከበበ ሲሆን ተምሳሌትነቱ 55ቱን የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራትን፥ የአፍሪካን ፀጋዎችና ብሩህ ተስፋን የሚያሳይ ነው።

Credit : #ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም ውሳኔ አሳለፈ። መንግስት ባወጣው መግለጫ ፤ በአሁኑ ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ክልል ነዋሪዎች የሰብዓዊ እርዳታን ፍለጋ ወደአጎራባች ክልሎች እየተጓዙ መሆኑን አመልክቷል። እነዚህ ዜጎች የሰብዓዊ እርዳታው ከቀያቸው ሳፈናቀሉ ባሉበት እንዲርሳቸው ቢደረግ እንግልታቸውን እንደሚቀንስ በጽኑ እንደሚያምን አሳውቋል። በመሆኑም በከፍተኛ…
#AU #IGAD

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር የሆኑት ሙሳፋቂ መሃመት የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም መወሰኑን እንደሚያደንቁ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት የበትግራይ ክልል ሰብዓዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦትን ለማድረስ የወሰነው ውሳኔ ይደነቃል ብለዋል።

በተጨማሪ ፤ የትግራይ ክልላዊ መንግስት ለሰብዓዊነት ተብሎ ግጭት ለማቆም የተላለፈውን ውሳኔ ለመመልከት እና በአስቸኳይ ግጭት ለማቆም ማወጁን እንደሚያደንቁ ገልፀዋል።

ለጋሾች እና የሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች በትግራይ ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች የሚያደርጉትን ድጋፍ በእጥፍ እንዲያሳድጉም ጥሪ አቅርበዋል።

ሊቀመንበሩ ፤ ሁሉን አቀፍና በድርድር በሚመጣ የተኩስ አቁም ላይ ሁሉም ወገን እንዲደርስ ህብረቱ ጥረቱን እንደሚቀጥል አሳውቀዋል።

በህብረቱ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ከሁሉም ወገን እና ባለድርሻ አካላት ጋር በመስራት ግጭቱን በፍጥነት ለመቋጨት የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ሊቀመንበሩ አሳውቀዋል።

በሌላ በኩል የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ማቆሙን አድንቀዋል ፤ የትግራይ ክልል መንግስትም ውሳኔው ንለማክበር እና ግጭት ለማቆም በመወሰን ምላሽ በመስጠቱ አድንቀዋል።

ለትግራይ ክልል እና ሌሎች በድርቅና በምግብ እጦት ለተጎዱ ክልሎች ሰብዓዊ እርዳታ በተጠናከረ መልኩ እንዲደረግ ዓለም አቀፍ አጋሮች የቻሉትን ሁሉ ጥረት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

ሁሉም ወገኖች ብሄራዊ ውይይት ጨምሮ ለዘላቂ ሰላም መስፈን ሁሉንም የሰላም አማራጮችን እንዲጠቀሙ ጠይቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
* Update የአሜሪካው የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ከኢትዮጵያ ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ጋር መነጋገራቸውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አሳውቋል። ሐመር በዚሁ ወቅት ጦርነት በአስቸኳይ ቆሞ ፤ በአፍሪካ ህብረት (AU) መሪነት ወደ ሰላም ድርድር ማምራት…
#AU #ETHIOPIA

የኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ኃላፊነት ተራዝሟል።

ለሰሜን ኢትዮጵያ ችግር ሰላማዊ መፍትሄ እንዲያፈላልጉ እና ችግሩ በሰላም መቋጫ እንዲያገኝ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው የተሾሙት የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ስልጣን / ኃላፊነት መራዘሙን ለመስማት ተችሏል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛን ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆን ተቀብለው አነጋግረዋል።

ሊቀመንበሩ ፤ ኦባሳንጆ የተሰጣቸው ኃላፊነት መራዘሙንም አመልክተዋል። በእሳቸው (በኦባሳንጆ) ላይ ያላቸው እምነት ሙሉ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጠዋል።

በተጨማሪ ፤ በኢትዮጵያ እና በቀጠናው ሰላም እና እርቅ እንዲመጣ ከሁለቱም ወገኖች እና ከዓለም አቀፍ ተዋናዮች ጋር የቀጠሉትን ግንኙነት አበረታታለሁ ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ከአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር ጋር ትላንት እዚሁ አዲስ አበባ ላይ መመካከራቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ትኩረቱን ያደረገው በአፍሪካ ህብረት በሚመራው የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የሰላም ንግግር በተመለከተ ሲሆን ይህንን ንግግር አሜሪካ እንዴት በተሻለ ሁኔታ መደገፍ እንደምትችል ምክክር መደረጉን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#AU_led_PeaceProcess

" መንግስት በአፍሪካ ህብረት ለሚመራው የሰላም ሂደት ቁርጠኛ ነው " - አቶ ደመቀ መኮንን

" የአውሮፓ ህብረት (EU) በአፍሪካ ህብረት የሚመራውን የሰላም ሂደት ይደግፋል " - ሪታ ላራንጂንሃ

ዛሬ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ከሆኑት ሪታ ላራንጂንሃ ውይይት አካሂደው ነበር።

በዚህም ወቅት አቶ ደመቀ ፤ ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ህብረት ጋር ያላትን ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።

ምትክል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ በሰሜን ካለው ግጭት ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ እና የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን ስላደረገው የሰላም ግንባታ ጥረት ገለጻ እንዳደረጉ ተገልጿል።

አቶ ደመቀ ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በአፍሪካ ኅብረት ለሚመራው የሰላም ሂደት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸው ፤ ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የአውሮፓ ኅብረት ድጋፍ እንደሚያደርግ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

ሪታ ላርንጃንሃ በበኩላቸው የአውሮፓ ህብረት ከኢትዮጵያ ጋር ስትራቴጂካዊ አጋርነቱን ለማጠናከር ፍላጎት እንዳለው ተናግረዋል።

ዳይሬክተሯ ፤ የአውሮፓ ህብረት በአፍሪካ ኅብረት የሚመራውን የሰላም ሂደት እንደሚደግፍ ገልፀው ፤ የሰላም ሂደቱን መደገፍ በሚፈለግ ጊዜ ለመርዳት ህብረቱ ፍላጎት እንዳለው አፅንኦት ሰጥተዋል።

መረጃው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AU

በአፍሪካ ህብረት (AU) መሪነት በደቡብ አፍሪካ የሚካሄደው የሰላም ንግግር በሎጅስቲክስ ምክንያት መራዘሙን ሮይተርስ የዲፕሎማቲክ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ የዲፕሎማቲክ ምንጭ ቀጠሮ የተያዘለት የሰላም ንግግር መራዘሙ ከሎጂስቲክስ ዝግጅት ጋር የተያያዘ መሆኑን ገልጸው እስካሁን አዲስ ቀን እንዳልተቆረጠ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት በአፍሪካ ህብረት የቀረበውን  የሰላም ንግግር ግብዣ መቀበላቸው እና የሰላም ንግግሩ ከነገ ጥቅምት 8/2022 ጀምሮ በደቡብ አፍሪካ እንደሚካሄድ ተገልጾ እንደነበር ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#ከሰሞኑን - ሰሜን ኢትዮጵያ !

ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተያያዘ ዛሬን ጨምሮ ባለፉት ቀናት ከኢፌድሪ መንግስት ፣ ከአሜሪካ መንግስት ፣ ከተመድ ፣ ከአውሮፓ ህብረት እንዲሁም ከአፍሪካ ህብረት የተሰጡ መግለጫዎች እና ወቅታዊ መረጃዎች ፦

➦ አሜሪካ ባወጣችው መግለጫ ፤ በባለፈው ዓመት ነሃሴ ወር አጋማሽ ላይ " ህወሓት / TPLF " በአማራ ክልል በ " ቆቦ " አካባቢ ዘመቻ ማካሄዱንና በዚህም ጦርነቱ #ዳግም_ለመቀስቀሱ አስተዋፆ ማድረጉን ይህን ተከትሎ ተጨማሪ የሰብአዊ መብት ረገጣ እና ግፎች ተጋላጭነት ከፍ እንዳደረገ ገልፃለች። አሜሪካ የኢትዮጵያ መከላከያ እና የኤርትራ መከላከያ በጋራ የሚያካሂዱትን ወታደራዊ ጥቃት እንዲያቆሙ እና ኤርትራ ጦሯን ከ " ሰሜን ኢትዮጵያ " እንድታስወጣም ጥይቃለች።

                           --------------------

➦ የአፍሪካ ህብረት ( #AU ) ኮሚሽን ሊቀ መንበር ፤ ሙሳ ፋኪ በሰሜን ኢትዮጵያ ውጊያ ውስጥ ያሉ አካላት " ያለምንም ቅድመ ሁኔታ " የተኩስ አቁም እንዲያደርጉ አሳስበው የሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎቶች ወደ ነበሩበት አንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት በደቡብ አፍሪካ ወደ ተጠራው " የሰላም ድርድር " እንዲመጡ ፋኪ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

                          --------------------

➦ የተመድ ዋና ጸኃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፤ " በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ከቁጥጥር ውጪ እየሆነ ነው። " ሲሉ ተናግረው ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።

" አሁን በኢትዮጵያ ባለው ሁኔታ የማህበራዊ ትስስር እየተበጣጠ ነው ፤ የሲቪሎች ህይወት እየቀጠፈና ውድመት እያስከተለ ያለው ጦርነት ማብቃት አለበት ብለዋል።

" የኤርትራ ኃይሎች ከኢትዮጵያ መውጣት አለባቸው " ያለቱ ጉተሬዝ በትግራይ ክልል ያለው ግጭት አሁኑኑ ማብቃት አለበት ብለዋል።  አሁን በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ወታደራዊ መፍትሄ የለውም ሲሉ ተናግረዋል።

ጦርነቱ እንዲያበቃ ተመድ (UN) የአፍሪካ ህብረትን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑ አረጋግጠው " ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሁን ለሰላም መሰባሰብ አለበት ። " ብለዋል።

በተመሳሳይ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከኤርትራ ሰራዊት ጋር በመተባበር በትግራይ ክልል እያካሄዱት ያለውን  የጋራ ጥቃት እንዲያቆሙ ጠይቋል ፤  የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት ሙሉ በሙሉ ለቀው እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል።

ህብረቱ ህወሓት በአማራ እና አፋር አጎራባች ክልሎች ያለውን ጦርነት እንዲያቆሙና ከወታደራዊ ዘመቻ እንዲቆጠቡ አሳስቧል።

                        --------------------

➦ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፤ " በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ከቁጥጥር ውጪ የወጣ ነገር የለም፤ ሁሉም ነገር በታቀደው መሰረት እየሄደ ነው " ብለዋል።

መንግስት የአፍሪካ ሕብረት ( #AU ) የሰላም ውይይቱ የሚካሄድበትን ቀን እስኪያሳውቅ በመጠባበቅ ላይ ይገኛልም ብለዋል።

" አንዳንዶች በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረው ግጭት ከቁጥጥር ውጪ ሆኗል በሚል እየተጠቀሙበት ያለው አገላለጽ ከእውነት የራቀ ነው " ሲሉ  ገልፀዋል።

" ግጭቱ ወደ አማራና አፋር ክልሎች ተስፋፍቶ ነበር አሁን ያ ነገር የለም፤ የመከላከል እርምጃው በታሰበው መልኩ እየሄደ ይገኛል " ያሉ ሲሆን የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦትና #መሰረታዊ_አገልግሎት እንደሚጀመር አሳውቀዋል።

                        --------------------

➦ ዛሬ ጥቅምት 8 የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መንግስት ባወጣው መግለጫ የመከላከያ ሠራዊት በከተሞች ውስጥ ምንም ዓይነት ጦርነት ሳያካሂድ ፦
- ሽሬ፣ 
- አላማጣ
- ኮረም ከተሞችን እንደተቆጣጠረ ገልጿል።

በመግለጫው ላይ ፤ " የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተከተለው ጥብቅ ወታደራዊ ዲሲፕሊን፣ የሕወሐትን ፕሮፓጋንዳ ሲያስተጋቡ የነበሩ አካላትን ሟርት ያመከነ ነው። " ሲልም ገልጿል።

ከልዩ ልዩ የርዳታ ድርጅቶች ጋር በመሆን መከላከያ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ላይ ርዳታ እንዲደርስ በቂ ዝግጅት መደረጉን የገለፀው መንግስት እርዳታ የማድረሱ ስራ የሽሬ አውሮፕላን ማረፊያን መጠቀምን እንደሚጨምር ገልጿል።

በተጨማሪ በሰሜን ጎንደር ወደ ሽሬ የሚወስደውን እና ከኮምቦልቻ - ደሴ- ወልድያ- ቆቦ- አላማጣ ያለውን መንገድ ለመክፈት እየሠራ መሆኑም አሳውቆ ይሄንን ሥራ የሚያሣልጥ ኮሚቴ ከሚመለከታቸው አካላት ተወጣጥቶ ሥራ ጀምሯል ብሏል።

እነዚህ ሥራዎች ቴክኒካዊ የሆኑ ጥናቶችን እና ግጭት በነበረባቸው አካባቢዎች አገልግሎቶችን ለማስጀመር የሚያስችሉ መሠረታዊ ሥራዎችን ይጨምራል ሲልም አሳውቋል።

                             --------------------

➦ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ህወሓት ለ3ኛ ተከታታይ ጊዜ " ጦርነቱን ሆን ብሎ " በመቀስቀሱ ​​በሰሜን ኢትዮጵያ ላለው ወቅታዊ ሁኔታ ብቸኛ ተጠያቂ ነው ያለ ሲሆን ህወሓት ጊዜ እና ቦታ ከተሰጠው ይህን እንደገና ያደርጋል ብሏል።

በሌላ በኩል መንግስት ከ " ህወሓት " ነፃ ባወጣቸው እና በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ላይ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደርስ ከድጋፍ ከሚያደርጉ አካላት ጋር አብሮ እንደሚሰራ እና የሰብዓዊ ድጋፍ ሰራተኞችን ደህንነት እንደሚያረጋግጥ አሳውቋል።

ምንጭ፦ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መ/ቤት ፣ የአፍሪካ ህብረት ትዊተር ገፅ ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ድረገፅ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የመንግስት ኮሚኒኬሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በደቡብ አፍሪካ የሚካሄደው የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት የሰላም ንግግር ዛሬ ተጀምሯል። የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ቃል አቀባይ ቪንሰንት ማግዌንያ ፤ የሰላም ንግግሩ እስከ እሁድ ጥቅምት 20 እንደሚዘልቅ አሳውቀዋል። ፕሬዝዳንት ራማፎሳ የደቡብ አፍሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስት እና ህወሓት መካከል የሚካሔደውን የሰላም ንግግር እንድታስተናግድ በመመረጧ ክብር…
#AU

የ " ኢትዮጵያ መንግስት " እና የ " ህወሓት " ን የሰላም ንግግር በተመለከተ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ ማህማት መግለጫ አውጥተዋል።

በመግለጫው ምን አሉ ?

- የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት #ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት የተገናኙበት የሰላም ንግግር ዛሬ በደቡብ አፍሪካ ተጀምሯል።

- በሰላም ንግግሩ ላይ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (IGAD)
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ፣ የአሜሪካ መንግስት ተወካዮች በታዛቢነት እየተሳተፉ ነው።

- ደቡብ አፍሪካ የሰላም ንግግሩን ለማስተናገድ ፍቃደኛ ስለሆነች ለሀገሪቱ መንግስት እና ለፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፖሳ ምስጋና አቅርበዋል።

- ሙሳ ፋኪ ማሀመት የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የኢትዮጵያን ጥቅም ባስጠበቀ ሁኔታ ሰላምን ለማስፈን እና ለግጭቱ ዘላቂ ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲገኝ ለማስረግ ባሳዩት ቁርጠኝነት ይበልጥ እንደተበረታቱ ገልፀዋል።

- የአፍሪካ ህብረት " የሰላም ንግግር " ተሳታፊ ወገኖች ኢትዮጵያ፤ በኢትዮጵያውያን ባለቤትነት እና በአፍሪካ ህብረት መሪነት ሰላም እንዲሰፍን ፣ የተረጋጋችና አንድነቷ የተጠበቀ እንድትሆን ህብረቱ ድጋፉን እንደሚቀጥል ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #AU #AddisAbaba

አዲስ አበባ ከአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ጋር በተያያዘ እንግዶቿን ተቀብላ እያስተናገደች ትገኛለች።

የጸጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል፤ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት አድርጌያለሁ፤ ስምሪትም በመውሰድ ስራ ላይ እገኛለሁ ብሏል።

በጉባኤው ለመሳተፍ ከተለያዩ ሀገራት የመጡና አሁንም የሚመጡ መሪዎችን እና ዲፕሎማቶችን ደህንነት  ለመጠበቅ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አመልክቷል።

- በሆቴሎች፣
- በመዝናኛ እና በገበያ ስፍራዎች
- እንግዶቹ ከቦታ ቦታ በሚንቀሳቀሱባቸው አካባቢዎች ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሆነም አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ወንጀሎች እንዳይፈፀሙ እና ምንም አይነት የደህንነት ስጋት እንዳይኖር ከፀጥታ አካላቱ ጋር ተቀናጅተው በመስራት እንደወትሮው ሁሉ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንዲያደርጉ የጋራ ግብረኃይሉ ጠይቋል፡፡

በተለይ #መንገዶች_ዝግ በሚደረጉበት ወቅት አሽከርካሪዎች እና እግረኞች #በትዕግስት በመጠበቅ ወይም ሌሎች አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም ለሀገር ገፅታ ግንባታ ላይ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርቧል።

አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙና የፖሊስ አገልግሎት ለማግኘት በስልክ ቁጥር ፦
👉 011-111-01-11፣
👉 011-552-63-03፣
👉 011-552-40-77፣
👉 011-554-36-78
👉 011-5-54-36-81 እንዲሁም በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ መስመሮች ጥቆማ መስጠት ይቻላል ተብሏል።

@tikvahethiopia
#AU #ETHIOPIA #AddisAbaba

እስካሁን  ወደ አዲስ አበባ የገቡ መሪዎች እነማን ናቸው ?

ለ36ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ የሀገራት መሪዎች አዲስ አበባ እየገቡ ይገኛሉ።

እስካሁን የገቡ ፦

- የናይጀሪያው ፕሬዝዳንት ሙሃመዱ ቡሃሪ
- የኬኒያ ፕሬዚደንት ዊሊያም ሩቶ
- የሞሪታኒያ ፕሬዝዳንት ሙሀመድ ኦልድ ጋውዛኒ
- የኬፕቬርዴ ፕሬዚደንት ጆሴ ማሪያ ፔሬ
- የሞዛምቢክ ፕሬዝዳንት ፋሊፔ ኒዪሲ
- የቻድ ፕሬዝዳንት መሃማት ዴቢ
-  የማዕከላዊ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ፋውስቲን አርቻንጄ ቶውድራ
- የኮንጎ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ዴኒስ ሳሶው ንጌሶ
- የሩዋንዳ ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ
- የሌሴቶ ፕሬዚዳንት ሳም ማትኬኔ

በተጨማሪም ፦ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣  የዑጋንዳ እና የደቡብ ሱዳንና የሊቢያ ምክትል ፕሬዚዳቶች እና የሌሎች የአፍሪካ አገራት መሪዎች እዚህ አዲስ አበባ ይገኛሉ።

Photo Credit : ENA

@tikvahethiopia
#AU

ኮሞሮስ የ2023 የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበርነትን #ከሴኔጋል በይፋ ተረክባለች።

36ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ዛሬ በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተጀምሯል።

በጉባዔው መክፈቻ መርሐግብር የወቅቱ የሕብረቱ ሊቀ መንበር ሴኔጋል ለኮሞሮስ ሊቀ መንበርነቷን በይፋ አስረክባለች።

የኮሞሮስ ፕሬዚዳንት አዛሊ አሱማኒ ከፕሬዜዳንት ማኪ ሳል የሊቀመንበርነቱን ቦታ የተረከቡ ሲሆን 2023ን የህብረቱ ሊቀመንበር ሆነው ያገለግላሉ።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia