#AU
የ " ኢትዮጵያ መንግስት " እና የ " ህወሓት " ን የሰላም ንግግር በተመለከተ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ ማህማት መግለጫ አውጥተዋል።
በመግለጫው ምን አሉ ?
- የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት #ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት የተገናኙበት የሰላም ንግግር ዛሬ በደቡብ አፍሪካ ተጀምሯል።
- በሰላም ንግግሩ ላይ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (IGAD)
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ፣ የአሜሪካ መንግስት ተወካዮች በታዛቢነት እየተሳተፉ ነው።
- ደቡብ አፍሪካ የሰላም ንግግሩን ለማስተናገድ ፍቃደኛ ስለሆነች ለሀገሪቱ መንግስት እና ለፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፖሳ ምስጋና አቅርበዋል።
- ሙሳ ፋኪ ማሀመት የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የኢትዮጵያን ጥቅም ባስጠበቀ ሁኔታ ሰላምን ለማስፈን እና ለግጭቱ ዘላቂ ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲገኝ ለማስረግ ባሳዩት ቁርጠኝነት ይበልጥ እንደተበረታቱ ገልፀዋል።
- የአፍሪካ ህብረት " የሰላም ንግግር " ተሳታፊ ወገኖች ኢትዮጵያ፤ በኢትዮጵያውያን ባለቤትነት እና በአፍሪካ ህብረት መሪነት ሰላም እንዲሰፍን ፣ የተረጋጋችና አንድነቷ የተጠበቀ እንድትሆን ህብረቱ ድጋፉን እንደሚቀጥል ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል።
@tikvahethiopia