TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#AFCON2021 ⚽️ ኢትዮጵያ 🇪🇹🇨🇲 ካሜሮን 🗓 ዛሬ ጥር 5 / 2014 ዓ/ም ⌚️ ማታ 1:00 🏟️ ፖል ቢያ ስታድየም 📍 ካሜሩን - ያዉንዴ 🖥 ሱፐር ስፖርት / ስካይ ስፖርት እና ኢቲቪ መዝናኛ ድል ለሀገራችን ኢትዮጵያ ! #HanaG. More : @tikvahethsport
#AFCON2021

ሀገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው የመጀመሪያ ጎሏን አስቆጠረች።

ኢትዮጵያ ከካሜሮን ጋር ፍልሚያዋን እያደረገች ትገኛለች።

ጨዋታው ከተጀመረ ጥቂት ደቂቃዎች የተቆጠረ ሲሆን በዳዋ ሆቴሳ አማካኝነት በዘንድሮ ውድድር የመጀመሪያ ጎል አስቆጥራለች።

ጨዋታው 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ቀጥሏል።

በስፖርት ገፃችን ተከታተሉ : @tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
#AFCON2021 ሀገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው የመጀመሪያ ጎሏን አስቆጠረች። ኢትዮጵያ ከካሜሮን ጋር ፍልሚያዋን እያደረገች ትገኛለች። ጨዋታው ከተጀመረ ጥቂት ደቂቃዎች የተቆጠረ ሲሆን በዳዋ ሆቴሳ አማካኝነት በዘንድሮ ውድድር የመጀመሪያ ጎል አስቆጥራለች። ጨዋታው 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ቀጥሏል። በስፖርት ገፃችን ተከታተሉ : @tikvahethsport
#AFCON2021

#ኢትዮጵያ እና #ካሜሮን መካከል እየተደረገ የሚገኘው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ፍልሚያ የመጀመሪያ አጋማሽ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ተጠናቋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ በመጀመሪያ አጋማሽ አስደሳችና እጅግ ማራኪ የሚባል እንቅስቃሴ አሳይታለች።

በዘንድሮ ውድድርም የመጀመሪያ ጎል አስቆጥራለች።

ድል ለእናት ሀገራችን ኢትዮጵያ ይሆን ዘንድ እንመኛለን።

More : @tikvahethsport
#ETHIOPIA

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቅርቡ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው 35ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እየተደረገ ባለው ዝግጅት ዙሪያ ከህብረቱ አባል ሀገራት ጋር መክሯል።

ሚኒስቴሩ እንዳስታወቀው ለአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶች ለጉባኤው እየተደረገ ስላለው ዝግጅት ማብራሪያ ተሰጥቷል።

ለጉባኤው ስኬት የሚያስፈልጉ ሁሉንም ነገሮች ከማዘጋጀት ባለፈ የተሳታፊዎች ጤንነት መጠበቅን ለማረጋገጥ የኮቮድ-19 ምርመራ እና ክትባት መስጫ የጤና ማእከላት በመንግስት መቋቋማቸውን ነው የገለፀው። 

የአፍሪካ ሀገራት ለኢትዮጵያ ላሳዩት አጋርነትም ምስጋናውን አቅርቧል። 

በዛሬው የጉባኤውን ዝግጅት አስመልክቶ በተደረገው ገለፃ ላይ ስለተነሱት ጉዳዮችም ለየሀገሮቻቸው መንግስታት እንዲያሳውቁም አሳስቧል።

ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
#AFCON2021

ሀገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ 2ኛ ጨዋታ በካሜሮን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች።

More : @tikvahethsport
#ALERT🚨

የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦

• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 10,073
• ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 2,131
• ህይወታቸው ያለፈ 👉 19
• ከበሽታው ያገገሙ 👉 835
• ፅኑ ታማሚዎች 👉 433

ዛሬ እና ትላንት በድምሩ የ43 የሰዎች ህይወት አልፏል።

@tikvahethiopia
" ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ጨዋታ አቁሙ !! " - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ምን አሉ ?

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፦

" ... እሱ ውጭ ሆኖ ወይም ደግሞ ጥግ ይዞ ወይም ህወሓት አዲስ አበባ ይጋባል ብሎ ሻንጣ ሲያዘጋጅ የቆየ መከላከያን ሊገመግም ይፈልጋል።

በዚህ ወጣ፣ በዚህ ወረደ፣ ይሄን አላደረገም፣ እንዲህ ነው እንዲያ ነው እያለ ይገመግማል።

ለምሳሌ መከላከያ ለምን ጠላት ወደ አማራ ክልል እንዲሰፋ አደረገ ይልሃል ፤ ጦርነት እግር ኳስ ይመስለዋል። ሁለቱ ቡድኖች የሆነ ስታዲየም ተሰርቶ እዛ ውስጥ ተገብቶ በግራ እና ቀኝ በሜትር ተሰምሮ እና ተለክቶ እዛ ውስጥ የምትጋጠም አድርጎ የሚያስብ አለ።

ጦርነት የእግር ኳስ ግጥሚያ አይደለም። አጥር የለውም። ልክ እንደእግር ኳስ ስታዲየም አጥር የለውም። ከአጥሩ ለምን ወጣህ የሚል ህግ የለውም። ሲመችህ ጠላትን ትገፋለህ 400 ኪ/ሜ ታስለቅቀዋለህ፤ ሳይመችህ ደግሞ እስኪመችህ ትከላከላለህ።

ጦርነትን እንደ አዲስ አበባ ስታዲየም ተከልሎለት የምትገጥም የሚደረግ ግጥሚያ አድርጎ የሚረዳ ሰው ነገሮችን የሚረዳበት መንገድ በጣም ደካማ ነው ወይም ሆን ብሎ ነው ለማበጣበጥ ሊሆን ይችላል። ሆን ብሎ ለማበጣበጥ ደግሞ ግንባር ቀደም ተዋናይ TPLF ነው፤ ወገን መስሎ፣ አማራ መስሎ፣ ኦሮሞ መስሎ ሰራዊቱን ለመገምገም ይሞክራል።

ሰራዊት ለመገምገም ቢያንስ 40 ዓመት ሰራዊት ውስጥ ማገልገል አለብህ። ጦርነት ለመገምገም ጦርነት ማወቅ አለብህ፤ ሳይንስ ጥበብ ማወቅ አለብህ። ወጥተህ ወርደህ የሰራዊትን ስነልቦና ማወቅ አለብህ።

ብድግ ብሎ የማንም እንትን ... Balloon ሲፈነዳ የሚደነግጥ ሰው ሰራዊት መገምገም የለበትም። ሰራዊት የመጨረሻ ምሽግ ነው። የሉአላዊነት የመጨረሻ ምሽግ ነው። ሰራዊት ብሄር የለውም። ሰራዊት ኢትዮጵያዊነት ነው ያለው።

ሰራዊት ውስጥ ገብተህ በፈተፈትክ ቁጥር ፣ ለማጋጨት በሰራህ ቁጥር ፣ በብሄር በከፋፈልከው ቁጥር ፣ በጓደኛ አንዱን ከፍ አድርገህ አንዱን ዝቅ ባደረከው ቁጥር ሀገር ላይ ነው አደጋ የምትፈጥረው። በነገራችን ላይ የኛ ሰራዊት ለእንደዚህ አይነት ነገር ፣ ለአሉባልተኛ ቦታ የለውም፤ ቦታ አይሰጥም። የተገነባባት መሰረቱ ግንቡ ጠንካራ ነው። ለዛ ምቹ አይደለንም እኛ። ለጎጥ፣ ለብሄርተኝነት ምቹ አይደለንም።

እኛ ብሄር የለንም ብለን ቃል ገብተናል፣ ለኢትዮጵያዊነት ነው የምንሞት ያለነው። ለኢትዮጵያዊነት ነው ሰው 48 ሰዓት ሳይበላ ሳይጠጣ የሚዋጋ ያለው። ለሀገሩ ነው። ኢትዮጵያን ከመበታተን ለማዳን ነው። እኛ እንደኢትዮጵያ ነው የምናስበው።

ለመተቸትም እውቀት ያስፈልጋል። ያለእውቀት የሚተች ወይ ጠላት ነው ሆን ብሎ ለመከፋፈል፣ ለማዳከም፣ ሞራሉን ለማድቀቅ ፣ አመራሩን ለመከፋፈል ጠላት የሚሰራው ነው በአብዛኛው እሱ ነው ብዬ ገምታለሁ። ሌላው ይሄን በማድረግ ትርፍ የሚገኝ እየመሰለው ሊሆን ይችላል ወይ ሌላው ሲያራግብ ጠላት ሲያራግብ የእሱ ወገን ያራገበ መስሎት እያሟሟቀ ይሆናል።

ተውት መከላከያን ! መከላከያ ለእያንዳንዳችን ዋስትና ነው። ስለዚህ ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ጨዋታ አቁሙ፤ sensitive የሆነ ቦታ እየመረጥክ የምትጫወተው ጨዋታ የጠላት ጨዋታ ነው። ተው !! ተው !! አሁን በኃላ በማያገባው ገብቶ የመከላከያን ህልውና የሚፈታተን ነገር ላይ የተሳተፈ ከሆነ እራሳችንን ለመከላከል እንገደዳለን "

@tikvahethiopia
#MIAM

በመላው አለም በኬሚካል ምርት አንቱታን ካተርፉ አገራት አለም አቀፍ የጥራት ደረጃቸዉን ያሟሉ የኬሚካል ምርቶችን ለአገር ውስጥ ገበያ እናቀርባለን።

Tel: 📞 +251911546231
📞 + 251930115522

📩 ፡ millionamakele@gmail.com

JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL
https://publielectoral.lat/MIAMPOLYMERS
#JustinTrudeau #OlusegunObasanjo

የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መዕክተኛ እና የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ጋር ተነጋግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ትሩዶ ልዩ መልዕከተኛው በሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን ግጭት እንዲያበቃ እና በሁሉም አካላት መካከል ውይይት እንዲፈጠር ለማበረታታት የሚያደርጉትን ጥረት በደስታ ተቀብለዋል።

ለግጭቱ ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት በአፍሪካ መሪነት ለሚደረገው የሽምግልና ጥረቶች ያላቸውን ጽኑ ድጋፍ እና ካናዳ በዚህ ረገድ የአፍሪካ ህብረትን ስራ ለመደገፍ ያላትን ዝግጁነት አረጋግጠዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግጭቱ ለተጎዱ ወገኖች ያለ ምንም እንቅፋት ሰብዓዊ ዕርዳታ በማድረስ ሂደት ላይ ያሉ ተግዳሮቶች እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።

ሰላማዊ ዜጎችን መጠበቅ፣ ህይወት ማዳንና የሰብአዊ መብት መከበርን ማረጋገጥ እንደሚገባ አሳስበዋል።

@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ለተፈናቃይ ወገኖች 2 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የምግብ ድጋፍ አደረገች።

ቤተክርስቲያኗ ህወሓት በከፈተው ጦርነት ምክንያት ተፈናቅለው በደባርቅ ከተማ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ወገኖች ነው 2 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የፊኖ ዱቄት ድጋፍ ያደረገችው።

የስዊድን እና አካባቢው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ፣ የሰሜን ጎንደር ዞን እና የጅማ ዞን አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ እና ሌሎች አባቶች ደባርቅ ከተማ በሚገኘው የተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያ ተገኝተው ድጋፉን አስረክበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በአማራ ክልል በሁሉም አካባቢዎች ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ ስታደርግ ቆይታለች፤ ወደፊትም የተጎዱ ወገኖችን መደገፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች።

ፎቶ ፦ EOTC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MeskelSquare መስቀል አደባባይን በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ተወያየ። ሰሞኑን በመስቀል አደባባይ የተደረገውን የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች መንፈሳዊና የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ላይ የተነሱ የመብትና የይዞታ ጉዳዮች ዙሪያ እንዲሁም አንቲባ አዳነች አቤቤ አስተላለፉት የተባለውን መልዕክት ተከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 3 ረፋድ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ጉባኤ አካሒዷል። በጉባኤውም ላይ ከፍ ሲል የተገለጸውን…
#Update

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የጤና ችግር አጋጥሟቸው ሆስፒታል መግባታቸው ተገልጿል።

ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 6 በመስቀል አደባባይ ጉዳይ ሊያደርግ ያሰበው ስብሰባ በቅዱስነታቸው አለመገኘት ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉ ተነግሯል።

ቅዱስነታቸው ፥ በገጠማቸው የጤና ችግር ምክንያት ሆስፒታል ስለገቡና ቅዱስነታቸው በመንበራቸው ላይ በሌሉበት ሁኔታ ጉባኤውን ማካሔድ ስለማይቻል የቅዱስ ፓትርያርኩ ጤና እስከሚመለስ ድረስ ጉባኤው ላልተወሰነ ጊዜ የተላለፈ መሆኑን የቤተክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ገልጿል።

@tikvahethiopia
ዶ/ር ቴድሮስ ምን አሉ ? የአፋር እና የአማራ ክልል ባለስጣናት ምን መለሱ ?

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ፦

" 7 ሚሊዮን ህዝብ የሚኖርበት ክልል ከአንድ አመት በላይ ሙሉ በሙሉ ከበባ ውስጥ ሆናል።

በዚህ ምክንያት ህዝቡ ምንም አይነት የምግብ አቅርቦት፣ የህክምና ፣ ኤሌክትሪክ፣ የቴሌፎን ፣ የመገናኛ አገልግሎት አያገኝም።

በመድሃኒት አቅርቦት እጥረት ምክንያት ሰዎች እየሞቱ ነው። በምግብ እጥረት ምክንያት እንደዚሁ ብዙዎች ህይወታቸውን ያጣሉ ከዚያ በላይ በየቀኑ የሚሰነዘረው የድሮን ጥቃት ሰዎችን እየገደለ ነው " ብለዋል።

የአፋር ክልል አዳአር ወረዳ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዶ አሊ ፦

" የዓለም ምግብ ፕሮግራምን ጨምሮ የተለያዩ አካላት ወደትግራይ በአፋር #አብዓላ በኩል የምግብ እርዳታ ሲጓጓዝ ቆይተዋል።

በቅርብ ጊዜ በአካባቢው ያለውን ሁኔታ ዓለም ያውቀዋል።

መጀመሪያ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል የሚገባበት አማራጭ መንገድ የለም፤ ለምን ? በአፋር አብአላ በኩል ያለውን ጦርነት እራሳቸው ከፍተው በአብአላ በኩል ጦርነት እያካሄዱ ነው እነሱ። በቆቦም በኩል ጦርነት እየተካሄደ ነው።

እናስገባ ቢባል እንኳን ሁሉም መግቢያ በሮቹ በአፋር በኩል ነበር እስከዛሬ የሚገባላቸው እርዳታ የሚገባው በዛ በኩል እራሳቸው ጦርነት ከፍተው ወረራ አድርገው በአብዓላ ከተማ እስካሁን ድረስ በመድፍ እየደበደቡ ስለሆነ እርዳታ የሚገባበት አማራጭ የለም።

እሱ (ዶ/ር ቴድሮስ) ለህወሓት ፕሮፖጋንዳ ነው እንዲህ የሚያደርገው እንጂ የመግቢያ መንገዶቹ በሙሉ የጦርነት ቀጠና እንደሆኑ ያውቃል። " ብለዋል።

የአማራ ክልል አደጋ መከላከል ምግብ ዋስትናና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘላለም ልጅዓለም ፦

" ህወሓት ቀበሌ ከምትገኝ የጤና ኬላ ጀምሮ እስከ ትልልቅ ሆስፒታሎች ድረስ የሚችለውን ዘርፎ መውሰድ የማይችለውን አገልግሎት እንዳይሰጥ አድርጎ አውድሟል።

ይሄ እንግዲህ መላው የዓለም አቀፍ ተቋማት በግላጭ የሚያውቁት ነው። ይህን እንኳን ሲያወግዙ አይሰማም።

በተመሳሳይ ጠላት ከወጣ በኃላ እነዚህ አካባቢዎች ከፍተኛ የመድሃኒት ችግር ፣ አገልግሎት ለማስጀመር የሚያስችል ቁመና ላይ አይደሉም ያሉት ጤና ተቋማቱ መልሶ ለማቋቋም እንኳን የዓለም ጤና ድርጅት አንድም አስተዋጽዖ እያበረከተ አይደለም " ብለዋል።

ያብቡ : https://telegra.ph/WHO-01-14-2
#ሹመት

ኢንጅነር የኋላሸት ጀመረ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር በመሆን ተሾሙ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ኢንጅነር የኋላሸት ጀመረ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አድርገው ሹመዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጥር 3 ቀን 2014 ጀምሮ ነው ኢንጅነር የኋላሸት ጀመረን የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አድርገው የሾሟቸው።

@tikvahetiopia
ፎቶ : 350 የሶማሊያ ወታደሮች ' መሰረታዊ የኮማንዶ ስልጠና ' ከኳታር የተውጣጡ የስልጠና ባለሞያዎችን በማካተት እየተሰጠ መሆኑን የቱርክ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ለወታደሮቹ ስልጠናው እየተሰጠው የሚገኘው በቱርክ የፀረ-ሽብርተኝነት ስልጠና እና መለማመጃ ማዕከል (Isparta) ዕዝ ውስጥ ነው።

ቱርክ እና ኳታር በሶማሊያ በፖለቲካ ውስጥ እንዲሁም በወታደራዊ ዘርፍ ላይ ተፅእኖ እንዳላቸው ይነገራል።

@tikvahethiopia
#Update

የደሴ - ወልዲያ የኤሌክትሪክ መስመር ጥገና እየተገባደደ ነው።

ፍተሻው በስኬት ከተጠናቀቀ እስከ ወልዲያ ድረስ ያሉት ከተሞች በሰዓታት ውስጥ ኤሌክትሪክ ሊያገኙ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል።

ተቋሙ እስከዛሬ ድረስ በተከናወነው ጥገና ጉዳት የደረሰበት መስመርና ምሰሶ ከ97 በመቶ በላይ ተጠናቋል ብሏል።

ቀሪ ሥራዎችን በርብርብ በማጠናቀቅ እስከ ወልዲያ ድረስ ያሉት ከተሞች ማምሻውን አልያም እስከ ነገ እኩለ ቀን ድረስ መብራት እንዲያገኙ ይደረጋል ሲል አሳውቋል።

@tikvahethiopia