TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#JustinTrudeau #OlusegunObasanjo

የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መዕክተኛ እና የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ጋር ተነጋግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ትሩዶ ልዩ መልዕከተኛው በሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን ግጭት እንዲያበቃ እና በሁሉም አካላት መካከል ውይይት እንዲፈጠር ለማበረታታት የሚያደርጉትን ጥረት በደስታ ተቀብለዋል።

ለግጭቱ ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት በአፍሪካ መሪነት ለሚደረገው የሽምግልና ጥረቶች ያላቸውን ጽኑ ድጋፍ እና ካናዳ በዚህ ረገድ የአፍሪካ ህብረትን ስራ ለመደገፍ ያላትን ዝግጁነት አረጋግጠዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግጭቱ ለተጎዱ ወገኖች ያለ ምንም እንቅፋት ሰብዓዊ ዕርዳታ በማድረስ ሂደት ላይ ያሉ ተግዳሮቶች እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።

ሰላማዊ ዜጎችን መጠበቅ፣ ህይወት ማዳንና የሰብአዊ መብት መከበርን ማረጋገጥ እንደሚገባ አሳስበዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#JustinTrudeau #OlusegunObasanjo የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መዕክተኛ እና የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ጋር ተነጋግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ትሩዶ ልዩ መልዕከተኛው በሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን ግጭት እንዲያበቃ እና በሁሉም አካላት መካከል ውይይት እንዲፈጠር ለማበረታታት የሚያደርጉትን ጥረት በደስታ ተቀብለዋል።…
#DrAbiyAhmed #JustinTrudeau

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ከካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጋር የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ አስታውቀዋል።

ውይይቱ በወቅታዊ ሀገራዊ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ እንደ ካናዳ ያሉ ወዳጅ ሀገራት የሚሰጧትን ድጋፍ እንደምታደንቅ ገልፀዋል።

የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ፥ ትላንት ከሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ጋር በተያያዘ ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መዕክተኛ እና የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ጋር መነጋገራቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia