TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AxumUniversity

ማሕበረሰብ ኣክሱም ዩኒቨርሲቲ ጉዕዞ ናብ ወፍሪ መኸተ ወራር ዕስለ አንበጣ!

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ የአምበጣ መንጋ የመከላከል ዘመቻ ላይ ለመሳተፍ ጉዞ እያደረጉ ይገኛሉ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AxumUniversity

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ የ2012 ተመራቂዎች የቲክቫህ አባላት እስካሁን አለመጠራታቸውን ከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና ውስጥ እንደከተታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።

ተማሪዎቹ በትግራይ ክልል ያለውን ከባድ ሁኔታ ቢረዱም ለዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተሰጠው አይነት መፍትሄ በፍጥነት ተግባራዊ ይደረጋል ብለው ቢጠብቁም እስካሁን ምንም እንደሌለ ገልፀዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ጉዳይ የሚከታተለው የሀገር አቀፍ ተማሪዎች ህብረት የአስክሱም ዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች ጉዳይ ከዚህ በፊት ልክ እንደዓዲግራት መፍትሄ ያገኘ መሆኑን ገልጿል።

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የ2012 ተመራቂ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ጨርሰው በመውጣታቸው የዓዲግራት እንዲሁም የአክሱም ተማሪዎች መቐለ ገብተው ትምህርታቸውን እንዲጨርሱ በMoSHE አቅጣጫ ተቀምጧል።

በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረትም የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መቐለ ዩኒቨርሲቲ ገብተዋል።

ለአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እስካሁን ጥሪ አልተደረገም።

ተማሪዎችን ለመጥራት ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በማስተባበር ላይ በመዘግየቱ ነው እስካሁን የቆየው።

ተመራቂ ተማሪዎችን ለመጥራት ስራዎች እየተሰሩ ፣ ዝግጅቶችም እየተደረጉ መሆኑን ተገልጿል።

በMoSHE አቅጣጫ መሰረት የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አጠናቀው የሚመረቁት መቐለ ዩኒቨርሲቲ ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AxumUniversity

ለአክሱም ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጥሪ ተደረገ።

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎችን ጥር 20 እና 21 በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ኹሓ ካምፓስ ተቀብሎ እንደሚያስተምር አስታውቋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ገብረእየሱስ ብርሃነ የመማር ማስተማር ሂደትን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን ለመግለጫ ሰጥተዋል።

ፕሮፌሰሩ ፥ ተማሪዎችም ሆኑ ወላጆች የደህንነት ስጋት ሳይገባቸው በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ተመራቂዎቹ መገኘት እንዳለባቸው በመግለጽ ጥሪ አቅርበዋል።

በቀጣይም ሌሎች ተመራቂ ላልሆኑ ተማሪዎች ጥሪ በማድረግ ዩኒቨርሲቲው የሚያስተምር መሆኑንም ገልጸዋል። ~ ENA

@tikvahethiopia
#AxumUniversity

አክሱም ዩኒቨርስቲ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሳቢያ የደረሰበት ጉዳት 15 ቢሊዮን ብር እንደሚገመት ማስታወቁን " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ዘግቧል።

ላለፉት 19 ወራት ትምህርት መስጠት አቁሞ የቆየው ዩኒቨርስቲው፤  ሊያከናውነው ላቀደው ዳግም ግንባታ የድጋፍ ጥሪ አቅርቧል።

የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ገብረእየሱስ ብርሃነ የሰጡት ቃል ፦

- ዩኒቨርስቲው በጦርነቱ ሳቢያ በደረሰበት #ውድመት እና #ዘረፋ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር የሚያስችሉት ቁሳቁሶች እና መሳሪያዎች አጥቷል።

- ሙሉ ለሙሉ የተዘረፉ እና ከወደሙ የዩኒቨርስቲው ንብረቶች ውስጥ ኮምፒውተሮች፣ የላብራቶሪ መሳሪያዎች፣ ሰርቨሮች እና የቢሮ በሮች ይገኙበታል።

- ዩኒቨርስቲው ከጦርነቱ በፊት የነበሩት 60 ገደማ ተሽከርካሪዎች ተዘርፈው እና ተቃጥለው አሁን በስራ ላይ የሚገኘው #አንድ_መኪና ብቻ ነው።

- በጥር ወር ላይ በተደረገ ዳሰሳ የደረሰው ውድመት 15 ቢሊዮን ብር ይደርሳል።

- ጉዳት የደረሰባቸውን ንብረቶች በተወሰነ መልኩ በመተካት ወደ ስራ ለመግባት ታቅዷል።

- ለሚያከናውነው ዳግም ግንባታ እና ጥገና ስራ የገንዘብ እና የማቴሪያል ድጋፍ እንዲደረግልን  ጠይቀናል። የድጋፍ ጥሪው ለዓለም አቀፍ እና ለሀገር በቀል አጋር ድርጅቶች፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ነው።

- ዩኒቨርስቲው የሚያገኘውን ድጋፍ በፌደራል መንግስት ከሚመደበለት በጀት ጋር በማጣመር በአጭር ጊዜ ውስጥ የመማር ማስተማር አገልግሎቱን ለመስጠት ታቅዷል። 

- ቁሳቁሶችን በተወሰነ መልክ ቅድሚያ እየሰጠን ካስገባን፤ የግዢ ሂደቱ ፈጣን ከሆነ፤ ተማሪዎችን #በሶስት_ወር ውስጥ ማስገባት እንችላለን። በትግራይ ክልል የሚኖሩ እና ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ትምህርት ያቋረጡ የዩኒቨርስቲው ተማሪዎችን ትምህርት ማስጨረስ ላይ ትኩረት ይደረጋል።

አክሱም ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ከፌደራል መንግስት በጀት ባይለቀቅለትም፤ በስሩ ለሚገኘው የጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 43 መምህራንን ለመቅጠር ከ2 ሳምንት በፊት ማስታወቂያ አውጥቷል።

የቅጥር ሂደቱ የሚፈጸመው በትምህርት ሚኒስቴር ተፈቅዶ፣ በጀት ሲለቀቅ መሆኑ ተገልጿል።

ከፌደራል መንግስት የሚለቀቀው በጀት፤ ለዩኒቨርስቲው ሰራተኞች ደመወዝ ለመክፈል እና ትምህርት ለማስጀመር ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

#አራት_ሺህ ገደማ የሚሆኑት የዩኒቨርስቲው መምህራን እና ሰራተኞች ከሐምሌ 2013  ዓ.ም. ወር ጀምሮ #ደመወዝ_አለማግኘታቸውን ዩኒቨርስቲው አስታውቋል።

Credit : www.ethiopianInsider.com

@tikvahethiopia
#AxumUniversity

በጦርነት ምክንያት አክሱም ዩኒቨርሲቲ አቁሟቸው ነበሩትን አገልግሎቶች ማስጀመሩን ለማወቅ ተቸሏል።

ዩኒቨርሲቲው ለቀድሞ ተማሪዎቹ ፦
➭ ኦፊሽያል ትራንስክሪፕት
➭ ስቱደንት ኮፒ
➭ ጊዚያዊ ሰርተፊኬት
➭ የዲግሪ ማረጋገጫ
➭ እንግሊዝኛ የማስተማሪያ ቋንቋነት ማረጋገጫ መስጠት መጀመሩን ገልጿል።

በመሆኑም የቀድሞ ተመራቂዎች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በዩኒቨርሲቲው በአካል በመገኘት አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

በሌላ በኩል ፥ አክሱም ዩኒቨርሲቲ በሁለት ወይም በሦስት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ኦሪጅናል ዲግሪ መስጠት እንደሚጀምር አሳውቋል።

አክሱም ዩኒቨርሲቲ ባለፉት ዓመታት በትግራይ ጦርነት ምክንያት የተቋረጠውን የመማር ማስተማር ስራ ለማስጀመርና ተማሪዎቹን ለመቀበል ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ ለማወቅ ችለናል።

More : @tikvahuniversity