TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"... የ2ኛው ዓመት የውሃ ሙሌት #ነሃሴ መጨረሻ ላይ ይጠናቀቃል" -ኢንጅነር ጌዲዮን አስፋው

የህዳሴ ግድብ ተደራዳሪና የባለሙያዎች ቡድን ሰብሳቢ ኢ/ር ጌዲዮን አስፋው ለኢዜአ በሰጡት ቃል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 2ኛው ዙር የውሃ ሙሌት እየተከናወነ ያለው ሶስቱ አገሮች በፈረሙት የመርህ ስምምነት መሰረት መሆኑን አሳውቀዋል።

ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን እ.ኤ.አ. በ2015 በመሪዎቻቸው አማካኝነት በሱዳን ካርቱም የህዳሴ ግድቡን ድርድር አስመልክቶ የመርሆች ስምምነት ተፈራርመዋል።

የመርህ ስምምነቱ አስር አንቀጾችን ያካተተ ሲሆን የሶስቱንም አገሮች ፍትሃዊና ምክንያታዊ የውሃ አጠቃቀም ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ይታወቃል።

በዚህም ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳን በተስማሙት የመርህ ስምምነት መሰረት ሁለተኛው ዙር የግድቡ የውሃ ሙሌት እየተከናወነ ኢንጅነር ጌዲዮን አስፋው ገልፀዋል።

በታላቁ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ላይ የሶስቱ አገሮች ባለሙያዎች የተስማሙባቸው ነጥቦች የተቀመጡ መሆኑን አስታውሰው አገሮቹ በዚሁ መሰረት መስማማታቸውን አስረድተዋል።

ግብጽና ሱዳን በመርሆች ስምምነት ውስጥ ሁለት ጥናቶች እንዲካሄዱ የሚያስቀምጥ ቢሆንም ግብጽ እና ሱዳን ጥናቱ እንዳይካሄድ ሲያስተጓጉሉ ነበር ብለዋል።

አገሮቹ ስምምነቱን ከተፈራረሙ በ15 ወር ውስጥ ሁለት (2) ጥናቶችን ማከናወን እንዳለባቸው ቢያስቀምጥም ጥናቶቹ እንዳይካሄዱ ግብጽና ሱዳን በያዙት ግትር አቋም ሳይሳካ ቀርቷል ነው ያሉት።

አለም አቀፉ ማህበረሰብ ግብጽ እንዲሁም ሱዳን የግድቡን ውሃ ሙሌት በተመለከተ የሚሰጡትን የተዛባ መረጃ ሊመረምር እንደሚገባም ገልጸዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/ENA-07-07

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
በአዲስ አበባ የኣሸንዳ በዓል መቼ ይከበራል ?

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፤ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ የ2015 ዓ.ም የአሸንዳ በአል አከባበር መርሃ ግብር ይፋ አድርጓል።

በዚሁ መሰረት፤ በዓሉን #ነሃሴ_28 ቀን 2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ለማክበር እቅድ መያዙ ገልጿል። የሚደረግ የጊዜ ለውጥ ካለ አስቀድሞ የሚገለፅ መሆኑንም አስተዳደሩ አሳውቋል።

የበዓሉ መርሀግብር ምን ይመስላል ?

- ነሃሴ 13 / 2015 ዓ/ም በአሜሪካ ፣ በአውሮፓ ፣ በአፍሪካ ፣ በኤስያ ፣ በሩቅ ምስራቅና በሌሎች የሚኖሩ ዳያስፓራ በጋራ ያከብራሉ ይህንን ከመቐለ ከሚካሄደው የቀጥታ ስርጭት ይተሳሰራል።

- ነሃሴ 15 የጎደና የካርኒቫል ትርኢትና ሰማእታት የሚያስታውስ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት ይከናወናል።

- ከነሃሴ 16 እስለ ነሃሴ 24 በሁሉም የትግራይ አከባቢዎች የኣሸንዳ ልጃገረዶች የጎደና ጨዋታ ይካሄዳል።

- ነሃሴ 28 በአዲስ አበባ ከተማ የሚከበር ሲሆን ፤ የሚደረግ የጊዜ ለውጥ ካለ አስቀድሞ  የሚታወቅ ይሆናል።

- ከአገር ውጭ ከነሃሴ 16 ጀምሮ ይከበራል።

ከዚህ ውጭ የሚካሄድ የኣሸንዳ በዓል ዝግጅት የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር እውቅና የሌለው መሆኑን  የትግራይ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ በይፋ አሳውቋል።

በሌላ በኩል  ፤ የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ኣፅብሃ ገ/እግዚአብሔር  በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ፤ ቢሮው ከነሃሴ 18 በፊት የኣሸንዳ በዓል በአዲስ አበባ እንዲከበር እውቅናና ድጋፍ የሰጠው ድርጅት የለም ብለዋል። " እውቅናና ድጋፍ ተሰጥቶኛል " በሚል በቢሮው ስም የሚንቀሳቀስ ካለ ህዝቡ ለቢሮው ጥቆማ እንዲሰጥ ሃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopia