TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ችሎት ! አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ እንዲገደል ቦታ አመቻችታለች ተብላ በሽብር ወንጀል የተከሰሰችውን እና የክሱ አንቀጽ ተቀይሮ በዋስ የተፈታችው ላምሮት ከማል የመከላከያ ማስረጃ የለኝም በአቃቢህግ ማስረጃ ይፈረድብኝ ስትል ፍርድ ቤቱን መጠየቋ ተሰምቷል። በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 2ኛ ይግባኝ ሰሚ ችሎት የተከሰሰችበት የሽብር ወንጀል ተቀይሮ አደጋ ላይ ያለ ሰውን በቸልተኝነት ያለመርዳት የወንጀል ህግ…
ችሎት !

አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ በሽጉጥ በተመታበት ወቅት በቸልተኝነት እርዳታ እንዳያገኝ ባለማድረግ ወንጀል ላምሮት ከማል ጥፋተኛ ተባለች።

የጥፋተኝነች ፍርዱን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የፀረሽብርና የህገመንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።

ከሳሽ ዓቃቢህግ ተከሳሿ ከአንድ የኦነግ ሸኔ አባል ጋር ሜክሲኮ አካባቢ በመገናኘት መንግስትን ከስልጣን ለማውረድ ታዋቂ ሰዎችን ለማስገደል ማቀዳቸውንና ከነዚህ ታዋቂ ሰዎች መካከል አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ መሆኑን ግለሰቡ ገልጿላት አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ እንዲገደል ቦታ እንድታመቻች በተነጋገሩት መሰረት የግድያ ቦታ አመቻችታለች ብሎ ክስ አቅርቧባት የነበረ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ግን የተከሰሰችበት ወንጀል በቂ ማስረጃ አልቀረበም ሲል በነጻ አሰናብቷት ነበር።

ዓቃቢህግ በውሳኔው ቅር በመሰኘት ለጠቅላይ ፍርድ ቤት 2ኛ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ይግባኝ ያለ ሲሆን ይግባኙን የመረመረው የጠቅላይ ፍርድ ቤት የስር ፍ/ቤት ነጻ በማለት የሰጠውን ውሳኔን በመሻር አርቲስት ሀጫሉ በሽጉጥ በተከሳሽ ጥላሁን ያሚ ተመቶ ደም ሲፈሰው በቸልተኝነት እርዳታ እንዲያገኝ ባለማድረግ የወንጀል ህግ አንቀጽ 575 ንዑስ ቁ1 በመተላለፍ እንድትከላከል ትዛዝ ሰቶ ነበር።

ይህን ትዕዛዝ ተከትሎ ለመደበኛ ፍርድ ቤት ተከሳሿ መከላከያ ማስረጃ የለኝም ዓቃቢህግ ባሰማው ማስረጃ ይፈረድብኝ ማለቷን ተከትሎ ፍ/ቤቱ ዛሬ በቸልተኝነት ሰውን ባለመርዳት በወንጀል ህግ አንቀጽ 575 ንዑስ ቁ1 በመተላለፍ የጥፋተኝነት ፍርድ ተሰቶባታል።

ተከሳሿ 1 ገጽ ቅጣት ማቅለያ በጽሁፍ አቅርባለች።

ፍ/ቤት የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት በይደር ቀጥሯል። ተከሳሽ ላምሮት ከማል የቅጣት ውሳኔ እስኪሰጥ እስከ ነገ ፖሊስ ጣቢያ እንድትቆይ ታዟል።

ምንጭ፦ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

@tikvahethiopia
" ከማሽከርከራችሁ በፊት የተሽከርካሪያችሁን ደህንነት ፈትሹ ፤ ተገቢውን ጥንቃቄም አድርጋችሁ አሽከርክሩ " - ፖሊስ

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በደረሰ የትራፊክ አደጋ በአንድ ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደረሰ።

በዛሬው ዕለት በደብረ ማርቆስ ከተማ ከጠዋቱ 1፡4ዐ ላይ ቀበሌ ዐ5 ልዩ ቦታው ታቦቱ መውረጃ መስቀለኛ መንገድ አካባቢ ከከተማው ወደ ኬላ መስመር ይጓዝ የነበረ ኮድ (3) የሰሌዳ ቁጥር 20975 የሆነ የህዝብ ማመላለሻ አይሱዙ ተሽከርካሪ ልጆችን ትምህርት ቤት ለመሸኘት ከመንገድ ውጭ በቆመች አንድ ግለሠብ በሁለት እግሯ ላይ ከባድ ጉዳት አድርሷል።

ተጎጂዋ ደ/ማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል ገብታ የህክምና እርዳታ እየተደረገላት ይገኛል።

አሽከርካሪው አደጋውን ካደረሠ በኃላ በመሠወሩ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋል አስፈላጊውን ክትትል እያደረገ መሆኑን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታውቋል።

የደ/ማርቆስ ፖሊስ አሽከርካሪዎች ከማሽከርከራቸው በፊት የተሽከርካሪያቸውን ደህንነት እንዲፈትሹ እና ተገቢውን ጥንቃቄ አድርገው እንዲያሽከረክሩ መልዕከት አስተላልፏል።

@tikvahethiopia
#Bank_of_Abyssinia

ወደ ሃገር ቤት በ " ካሽ ጎ " ገንዘብ ለመላክ አስበዋል ? ቪዛ ካርድ ወይም ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው ማስተላለፍ ይችላሉ፡፡

ይከፈል የነበረው የ1.5% የመላኪያ ክፍያ በነፃ መደረጉን ስንገልጽሎት በደስታ ነው። የአቢሲንያ ባንክን ትክክለኛ የቴሌግራም ቻነል ይቀላቀሉ https://publielectoral.lat/BoAEth
#አቢሲንያ #የሁሉም_ምርጫ
#MinistryFinance

በሀገሪቱ 🇪🇹 ኢኮኖሚ ላይ የደረሰውን ጉዳት መልሶ ለመገንባት የሚያስችል እና ዜጎች ለማቋቋም የሚውል አዲስ በጀት ሊያጸድቅ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ በጠ/ሚ ጽ/ቤት በተዘጋጀው " የአዲስ ወግ " መርሃ ግብር ላይ መስሪያ ቤታቸው በጦርነት ምክንያት የተጎዳውን ኢኮኖሚ ለማካካስ ብሎም መልሶ ለመገንባት ተጨማሪ በጀት እንደሚጠይቅ ተናግረዋል፡፡

የሚያስፈልገው ገንዘብን በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ተሰርቶ ረቂቁ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረቡን አስታውቋል።

አቶ አህመድ ሽዴ በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርብም የገለፁ ሲሆን ከጸደቀ በቀጥታ ወደ ስራ እንደሚገባ መናገራቸድን አል ዓይን ድረገፅ አስነብቧል።

#አልዓይን

@tikvahethiopia
#Amhara #Tigray #Afar

የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ 🇪🇹 በግጭት በተጎዱ ክልሎች ላለው የጤና እና ሰብዓዊ ፍላጎቶች ምላሽ እየሰጠ መሆኑን አሳውቋል።

የዓለም ጤና ድርጅት አካላት ከ2 ቀን በፊት #በአማራ ክልል የወደሙ ሆስፒታሎችን በአካል የተመለከቱ ሲሆን የ2 ሚሊዮን ሰዎችን አስቸኳይ የጤና ፍላጎት ለማሟላት ወደ 100 ሜትሪክ ቶን የሚጠጋ መድሀኒትና የህክምና ቁሳቁሶችን እንዳስረከቡ ድርጅቱ ገልጿል።

ተጨማሪ የህክምና ቁሳቁሶች ወደ #አፋር#ትግራይ እና ሌሎችም ክልሎች መላኩን ድርጅቱ አመልክቷል።

@tikvahethiopia
#Afar #Tigray #Amhara

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ምክትል ቃል አቀባይ የሆኑት ፈርሐን ሐቅ በሰሜን ኢትዮጵያ አንዳንድ መሻሻሎች መኖራቸውን የሚያመላክቱ ሪፖርቶች መኖራቸውን ገልፀዋል።

አሁንም ግን ከሰሞኑን በአካባቢው በተከሰተ ግጭት ሳቢያ ያለው ሁኔታ ተለዋዋጭ እንዲሁም ሊገመት የማይችል ነው ብለዋል።

ቃል አቀባዩ ፥ በአማራ እና አፋር ክልል ተፈናቅለው የነበሩ አንዳንድ ነዋሪዎች ወደ ቄያቸው እየተመለሱ መሆናቸውን በአካባቢው ከሚገኙ ባልደረቦቻችን ተረድተናል ብለዋል።

በአካባቢው ባለው የተደራሽነት ችግር የተመላሾችን ቁጥር ለማወቅ አዳጋች መሆኑን ገልፀዋል።

በአፋር እና ትግራይ ምዕራባዊ ክፍል አሁንም የሚፈናቀሉ አንዳንድ ሰዎች መኖራቸውን አመልክተዋል።

ቃል አቀባዩ ፥ በስፍራው ያሉት የሰብዓዊ ድጋፍ አጋሮቻችን እኤአ ከታህሳስ 15-17 ባሉ ጊዜያት ውስጥ የአየር ድብደባ መካሄዳቸውን ፤ ብዙ ሰዎች መሞታቸውን እና ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑን ተናግረዋል ብለዋል። ይሁን እንጂ ድርጊቱን ከገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ እንዳልተቻለ አስረድተዋል።

ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ በአፋር በኩል ወደ ትግራይ መቐለ የደረሰ ምንም አይነት እርዳታ የጫነ ተሽከርካሪ አለመኖሩን ተናግረዋል።

በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው በርካታ ተግዳሮት አሁንም ድረስ ያለ መሆኑን ጠቁመው ሁሉም ወገኖች ግጭት አቁመው የእርዳታ አቅርቦት እና የእርዳታ ሰራተኞች ወደ ትግራይ ፣ አፋር እና አማራ ክልሎች በነፃነት እንዲቀሳቀሱ እንዲደረግ ጥሪ እናቀርባለን ማለታቸውን ቬኦኤ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#Update

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።

ዶ/ር ሊያ በመግለጫቸው በአፋር እና በአማራ ክልሎች በህወሓት የወደሙ የጤና ተቋማትን መልሶ ሥራ ለማስጀመር በተደረገ እንቅስቃሴ እስካሁን 64 የሚሆኑ የጤና ተቋማት በድጋሚ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ መቻሉን መናገራቸውን ዋልታ ዘግቧል።

በሁለት ክልሎች ላይ የወደሙ የጤና ተቋማትን መልሶ ሥራ ለማስጀመር እና ለማደራጀት በተለያዩ መንገዶች የሀብት ማሰባሰብ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል ዶ/ር ሊያ ታደሰ በመግለጫቸው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሥርጭት በከፍተኛ ሁኔታ በመሰራጨት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ህብረተሰቡ ለኮቪድ-19 ወረርሽኝን የመከላከያ እንደሁም የመቆጣጠሪያ መንገዶችን መተግበሩ ላይ ከፍተኛ መዘናጋት እያሳየ እንደሆነ አመልክተዋል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ : ወደ ድብድብና ቡጢ መሰናዘር የተቀየረው የጋና ፓርላማ ክርክር 👊

ከቀናት በፊት ሰኞ በጋና ፓርላማ በኤሌክትሮኒክ ግብይት ላይ ሊጣል በታቀደ ታክስ ላይ ፓርላማው ለሁለት ተከፍሎ ከፍተኛ ክርክር ሲደረግ ነበር።

ይኸው ክርክር ወደ ከፍተኛ ፍጥጫ ተቀይሮ ተከራካሪዎቹ ወደ ድብድብ እና ቡጢ🤜 🤛መሰናዘር አድርሷቸዋል ፤ የፓርላማው ክስተት ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኖ ነው ያለፈው።

በዚህ ጥል አንድ ሰው መጎዳቱ ተሰምቷል።

@tikvahethiopia
#UPDATE

" ሰራዊቱ ባለበት እንዲቆይ ተወስኗል " - ዶ/ር ለገሰ ቱሉ

የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ መግለጫ ሰጥተዋል።

ዶ/ር ለገሰ፥ " በጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የተመራው 'ዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት' በአሸባሪው ሃይል የተወረሩ አካባቢዎችን በማስለቀቅና ተልዕኮውን በማሳካት የመጀመሪያው ምዕራፍ ተጠናቋል" ሲሉ አሳውቀዋል።

በዘመቻው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ታላቅ ጀብዱ የሰሩበትና በታሪክ ወርቃማ ሆኖ የሚጻፍ ስራ የሰሩበት ነው ያሉ ሲሆን የአማራና አፋር ክልል የፀጥታ ሃይሎችም የራሳቸውን ጥረት አድርገው አኩሪ ድርሻ ተወጥተዋል ሲሉ ተናግረዋል።

"አሁን ላይ የጠላት መሻት፣ ፍላጎትና የማድረግ አቅም ክፉኛ ተመቷል ያሉት ሚኒስትሩ፥ "ይሁን እንጂ የጠላት ሃይል ፍላጎት ዳግም እንዳይቀሰቀስ መንግስት በቀጣይ በጥናት ላይ ተመስርቶ እርምጃ ይወስዳል" ብለዋል።

የወገን ሃይል ጥንካሬውን ይዞ እንዲቀጥል ጠንካራ ስራ ይሰራል ሲሉ የተናገሩት ሚኒስትሩ ህብረተሰቡ እስከዛሬ ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

ዶ/ር ለገሰ፥"ወራሪውን ሃይል በገባበት የደመሰሰው የመከላከያ ሰራዊትም ባለበት እንዲቆይ ተወስኗል" ሲሉ አሳውቀዋል።

"ለዚህም ከዚህ ቀደም በትግራይ ክልል ካጋጠሙ ችግሮች መማር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ በተጠና መልኩ የፀጥታ ሃይሉ እርምጃ እንዲወስድ እንዲሁም በሽብር ቡድኑ ሴራና ወጥመድ ላለመግባት በማሰብ ነው ውሳኔው የተወሰነው" ሲሉ አስረድተዋል።

በምዕራብ አማራ ካለው ሁኔታ ጋር በተያያዘ መንግስት ወደፊት መረጃዎችን እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

ሚኒስትሩ፥ "በኦሮሚያ ክልል በንጹሃን ላይ በአሸባሪው ሸኔ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን ለመከላከል መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳል" ሲሉ ማስገንዘባቸውን ፋና ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#Attention

የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዝ ዛሬ ማምሻውን ባደረገው ስብሰባ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ አፈጻጸሙን ገምግሟል፡፡

ዕዙ ከግምገማው በኃላ የተለያዩ ትዕዛዝትን አስተላልፏል።

* ከላይ ያንብቡ !

@tikvahethiopia
#ALERT🚨

በሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 3,793 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋገጠ።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ከተደረገው 13,147 የላብራቶሪ ምርመራ 3,793 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓት የ5 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

በሌላ በኩል ፤ ኦሚክሮን የተሰኘው የኮቪድ-19 አዲሱ ዝርያ ኢትዮጵያ ውስጥ መከሰት አለመከሰቱን ለማረጋገጥ ናሙና በመውሰድ ምርምር እየተካሄደ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ዛሬ አስታውቀዋል።

@tikvahethiopia
#NewsAlert

የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ (ዩኤኢ) ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስጋት ጋር በተያያዘ ከኬንያ፣ #ኢትዮጵያ ፣ ታንዛኒያ እና ናይጄሪያ ወደ ሀገሯ የሚገቡ መንገደኞችን አገደች።

እግዱ ከታህሳስ 16 ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ነው።

እግዱ ወደ ተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ከመምጣታቸው 14 ቀናት በፊት በአራቱ ሀገራት የነበሩ ተጓዦችን እንዳይገቡ ማገድን የሚያካትት ነው።

ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ወደ እነዚህ ሀገራት የሚደረገው በረራ በተያዘለት መርሃ ግብር ይቀጥላል ተብሏል።

የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ዜጎችና የመጀመሪያ ደረጃ ዘመዶቻቸው (FDR) ፣ ወርቃማ ቪዛ (የረጅም ጊዜ የመኖሪያ ቪዛ) ያላቸው ፣ በእነዚህ ሀገራት መካከል ያሉ የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች እንዲሁም ኦፊሴላዊ ልዑካን ከአዲሱ የጉዞ ህግ / እገዳ ነፃ መሆናቸው ተናግሯል።

ነገር ግን ከመነሳታቸውን ከ48 ሰዓት በፊት የኮቪድ-19 ምርመራ ተመርምረው ነፃ መሆናቸው የሚያረጋግጥ ውጤት ማቅረብ ፣ ኤርፖርት ላይ ፈጣን የPCR ምርመራ በስድስት ሰዓት ውስጥ ማድረግ እንዲሁም ዩኤኢ ሲደርሱ ኤርፖርት ላይ የPCR ምርመራ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ዜጎችና የመጀመሪያ ደረጃ ዘመዶቻቸው ፣የረጅም ጊዜ የመኖሪያ ቪዛ ያላቸው እና የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች የ10 ቀን ኳራንቲን እና ወደ ሀገር በገቡ በ9ኛው ቀን የPCR ምርመራ ማድረግ አለባቸው ተብሏል።

የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ዜጎች ወደ አራቱ የአፍሪካ ሀገራት እንዳይጓዙ የተከለከሉ ሲሆን ክልከላው የሀገሪቱ የድንገተኛ ህክምና ጉዳዮች ፣ ይፋዊ ልዑካን እንዲሁም ከሶኮላርሺፕ ጋር በተያያዘ የሚጓዙትን አይጨምርም።

ምንጭ፦ https://www.wam.ae/en/details/1395303005869

@tikvahethiopia
#Awaqi

⚡️ምንም ቢሆን ምንም ⚡️
አላማችንን ለማሳካት ወደፊት እንራመድ ✊🏾
.
.
የተለያዩ ለወጣቶች የተዘጋጁ የህይወት ክህሎቶችን እና የስራ እድሎችን ለማግኘት አዋቂን ይቀላቀላሉ 👇🏾

Follow @awaqiethiopia

👇🏾Join our Telegram Channel
https://publielectoral.lat/+oIKaBr97Xn40OGM0
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AGOA

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ኢትዮጵያ ፣ ማሊ እና ጊንን ከAGOA እንዲሰረዙ ፈርመዋል።

ከእኤአ ከጥር 1 ጀምሮ ተፈፃሚ ይሆናል።

ኢትዮጵያ የተሰረዘችው ከትግራይ ጦርነት ጋር በተያያዘ ተፈፅሟል ለተባለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው ፤ በተጨማሪ ከህወሓት ጋር ለድርድር እንድትቀመጥ ለማስገደድ በማለም ጭምር ነው።

አሜሪካ ፥ ኢትዮጵያን ጨምሮ ማሊን እና ጊኒን ከAGOA የሰረዘችው ፍላጎቶቼን ማሟላት አልቻላችሁም በሚል ነው።

ከመሰረዟ በፊትም የሁለት ወራት የማሰቢያ ጊዜ ገደብ ሰጥታ ነበረ።

ምንም እንኳን ኢትዮጵያ በAGOA ላይ እንድትቆይ ከፍተኛ ተሰሚነት ያላቸው ኮንግረስ መሪዎች ለባይደን ደብዳቤ ቢፅፉም እሳቸው ግን ኢትዮጵያን ከAGOA ሰርዘዋታል።

ኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት ያህል ከቆየችበት የAGOA ተጠቃሚነት እንዳትሰረዝ የኢትዮጵያ አሜሪካውያን የዜጎች ካውንስል ከፍተኛ ግፊት ሲያደርግ ነበር።

የፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ውሳኔ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሰራተኞችን እንዲጎዱ የሚያደርግ ነው።

ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት ኢትዮጵያን AGOA ተጠቃሚነት ውጭ ማድረግ፤ ከግጭቱ ጋር ምንም አይነት ግንኙት የሌላቸውን ከ200 ሺህ በላይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የበርካታ ሴቶች ኑሮ ላይ ተጽእኖ እንደሚኖረው ማሳወቋ ይታወሳል።

በግበዓት አቅርቦት ሰንሰለት የሚሳተፉትን የ1 ሚሊዮን ሰዎች ህይወት በእጅጉ እንደሚጎዳው መግለጿ አይዘነጋም።

AGOA ምንድነው?

African Growth and Opportunity Act (AGOA) የግብይት ስርዓት ነው፤ ይህ የግብይት ስርዓት የተወሰኑ የብቃት መስፈርቶችን የሚያሟሉ ከሳሃራ በታች የሚገኙ የአፍሪካ ሀገራት ሸቀጦችን ያለቀረጥ ለአሜሪካ ገበያ እንዲሸጡ የሚፈቅድ ነው።

@tikvahethiopia