#UPDATE

" ሰራዊቱ ባለበት እንዲቆይ ተወስኗል " - ዶ/ር ለገሰ ቱሉ

የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ መግለጫ ሰጥተዋል።

ዶ/ር ለገሰ፥ " በጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የተመራው 'ዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት' በአሸባሪው ሃይል የተወረሩ አካባቢዎችን በማስለቀቅና ተልዕኮውን በማሳካት የመጀመሪያው ምዕራፍ ተጠናቋል" ሲሉ አሳውቀዋል።

በዘመቻው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ታላቅ ጀብዱ የሰሩበትና በታሪክ ወርቃማ ሆኖ የሚጻፍ ስራ የሰሩበት ነው ያሉ ሲሆን የአማራና አፋር ክልል የፀጥታ ሃይሎችም የራሳቸውን ጥረት አድርገው አኩሪ ድርሻ ተወጥተዋል ሲሉ ተናግረዋል።

"አሁን ላይ የጠላት መሻት፣ ፍላጎትና የማድረግ አቅም ክፉኛ ተመቷል ያሉት ሚኒስትሩ፥ "ይሁን እንጂ የጠላት ሃይል ፍላጎት ዳግም እንዳይቀሰቀስ መንግስት በቀጣይ በጥናት ላይ ተመስርቶ እርምጃ ይወስዳል" ብለዋል።

የወገን ሃይል ጥንካሬውን ይዞ እንዲቀጥል ጠንካራ ስራ ይሰራል ሲሉ የተናገሩት ሚኒስትሩ ህብረተሰቡ እስከዛሬ ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

ዶ/ር ለገሰ፥"ወራሪውን ሃይል በገባበት የደመሰሰው የመከላከያ ሰራዊትም ባለበት እንዲቆይ ተወስኗል" ሲሉ አሳውቀዋል።

"ለዚህም ከዚህ ቀደም በትግራይ ክልል ካጋጠሙ ችግሮች መማር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ በተጠና መልኩ የፀጥታ ሃይሉ እርምጃ እንዲወስድ እንዲሁም በሽብር ቡድኑ ሴራና ወጥመድ ላለመግባት በማሰብ ነው ውሳኔው የተወሰነው" ሲሉ አስረድተዋል።

በምዕራብ አማራ ካለው ሁኔታ ጋር በተያያዘ መንግስት ወደፊት መረጃዎችን እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

ሚኒስትሩ፥ "በኦሮሚያ ክልል በንጹሃን ላይ በአሸባሪው ሸኔ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን ለመከላከል መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳል" ሲሉ ማስገንዘባቸውን ፋና ዘግቧል።

@tikvahethiopia