#Update

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።

ዶ/ር ሊያ በመግለጫቸው በአፋር እና በአማራ ክልሎች በህወሓት የወደሙ የጤና ተቋማትን መልሶ ሥራ ለማስጀመር በተደረገ እንቅስቃሴ እስካሁን 64 የሚሆኑ የጤና ተቋማት በድጋሚ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ መቻሉን መናገራቸውን ዋልታ ዘግቧል።

በሁለት ክልሎች ላይ የወደሙ የጤና ተቋማትን መልሶ ሥራ ለማስጀመር እና ለማደራጀት በተለያዩ መንገዶች የሀብት ማሰባሰብ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል ዶ/ር ሊያ ታደሰ በመግለጫቸው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሥርጭት በከፍተኛ ሁኔታ በመሰራጨት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ህብረተሰቡ ለኮቪድ-19 ወረርሽኝን የመከላከያ እንደሁም የመቆጣጠሪያ መንገዶችን መተግበሩ ላይ ከፍተኛ መዘናጋት እያሳየ እንደሆነ አመልክተዋል።

@tikvahethiopia