TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
በትግራይ እና አማራ አዋሳኝ ስፍራ ምን ተፈጠረ ? በትግራይ ክልል እና በአማራ ክልል የራያ ወረዳ አዋሳኝ አከባቢዎች በትጥቅ የተደገፈ ግጭት እንደነበረ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመስማት ችሏል። የካቲት 6 / 2016 ዓ.ም የተቀሰቀሰው መጠነኛ ነው የተባለው ግጭት በሀገር መከላከያ ሰራዊት ጥረት ሊቆም እንደቻለ ነው የተነገረው። ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የአላማጣ ከተማ ነዋሪ ለመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ…
" ችግሩ በሰላማዊ መንገድ የፌደራል መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ እንዲፈታ ፍላጎታችን ነው " - አቶ ኃይሉ አበራ

ከሰሞኑን #በአማራ እና #በትግራይ ክልሎች መካከል ተቀሰቀሰ የተባለውን ለአጭር ጊዜ የቆየ የተኩስ ልውውጥ በተመለከተ በአማራ ክልል በኩል ያለውን ሁኔታ አስመልክቶ በአሁን ሰዓት በአማራ ክልል ስር እየተዳደረ ያለው የአላማጣ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የሆኑት አቶ ኃይሉ አበራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አቶ ኃይሉ አበራ ምን አሉ ?

- በባላ አቅጣጫ ማሮ በሚባል ቦታ ከእኛ ሚሊሻ ጋ ገጠሙ። ተመትተው ተመልሰዋል አሁን ላይ ቦታውን ለቀዋል።

- ወደ ሁለት ቀበሌዎች ወረራ ለማድርግ ሙከራ አድርገው ነበር። በመጀመሪያ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የሰላም ጥሪ ነበር እየተላለፈ የከረመው፣ አሁን ግን እሳቢያቸው የነበረው በወረራ ቦታውን ይዘው ‘እንደራደራለን’ አይነት፣ በተፈናቃይ ስም ግጭት መፍጠር ነው።

* የጉዳት መጠንን በተመለከተ ፦ " እኛ ጋር የደረሰ ጉዳት የለም። እነሱ ግን ሊያጠቃ የመጣ ምንጊዜም ተመትቶ ነው የሚሄደው። የተወሰኑት ተመተው ሂደዋል። " ብለዋል።

- አላማጣን፣ ኮረምን ለመውረር እንዲሁ በጡሩባ እና በጩኽት የሚለቅ ህዝብ መስሏቸው ነበር። ሕዝቡ ማዕበል ሆኖ ነው የወጣው ከዚህ በኋላ የሰላሙን ጥሪ የማይቀበሉት እና ሰላሙን የማይፈልጉት ከሆነ አሁን እኛ ህዝባዊ አድርገነዋል።

* የመፍትሄ ሀሳብን በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተነሳው ጥያቄ ፦ " ችግሩ በሰላማዊ መንገድ የፌደራል መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ እንዲፈታ ፍላጎታችን ነው። 'አይ የለም ህዝቡ ወደ ሚፈልገው መሆን አይችልም፣ እኔ ብቻ ነኝ የምወስንልህ' የሚል እሳቤ የሚቀሳቀስ ከሆነ እሱ የሚቻል አይደለም። ፋሽኑም ግዜውም አልፎበታል። አሁን ላይ ወደ ኋላ የሚመልስ ኃይል የለም። Already ሁሉም ተደራጅቷአል። " ብለዋል።

- የትግራይ ፖለቲከኞችም ሀይ ሀይ የሚሉትን ዲያስፖራ ቆም ብለው ሊያስቡ ይገባል። ' አይ የለም የትግራይ ሉዐላዊ ግዛት ' እያሉ በወረራ የያዙትን ቦታ 'በኃይል እናስመልሳለን' የሚሉ ከሆነ ግን ከዚህ በኋላ የሚኖረው ሕዝባዊ ነው። ሕዝባዊ ከሆነ ደግሞ አደጋው የከፋ ነው የሚሆነው። በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ቀውስ ነው ሊፈጠር የሚችለው። ይህንን እንዲያስቡበት ነው የምናስገነዝበው።

- እኛ የማንንም መብት አንጋፋም የትኛውንም ሰው በማንነቱ ምክንያት የምናደርስበት ጉዳት የለም። ሊወርና ሊገድል ኃይል ከመጣ ግን ህዝብን መቆጣጠር አይቻልም። ስለዚህ ነገሮች ከቁጥጥር ውጭ ከመሆናቸው በፊት ቆም ብለው ቢያስቡ ይሻላል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 9 ቀን 2016 ዓ/ም
አላማጣ

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ይሄ ' የአማራ አዋሳኝ ' የሚባለው ቀልድ መቆም ያለበት ነው " - አቶ ረዳዒ ኃለፎም

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ረዳዒ ሀለፎም ሰሞኑን ስለነበረው የተኩስ ልውውጥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አቶ ረዳዒ ሀለፎም ምን አሉ ?

- ግጭቱ ራያ አላማጣ ሳይሆን ጨርጨር አካባቢ ነው። ይሄ የአማራ አዋሳኝ የሚባለው #ቀልድ ደግሞ መቆም ያለበት ነው።

- የትግራይ መሬት ነው ጨርጨር። ጨርጨር ትግራይ እንጂ አማራ ሆኖ አያውቅም። አሁንም አይደለም። እዚያው የአማራ ታጣቂዎች አሉ። እነዛ የአማራ ታጣቂዎች በእኛ ሚሊሻዎች ላይ የፈጸሙት ጥቃት ነው። የአጭር ጊዜ ተኩስ ልውውጥ ነበር ቁሟል አሁን ግጭቱ የለም።

* ጉዳዩን በተመለከተ ምን እየተሰራ እንደሆነ ለቀረበ ጥያቄ ፦ " በእኛ በኩል (በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርም) ከላይ ከሚመለከታቸው የፌደራሉ መንግሥትም የተወሰነ ንግግር እየተደረበት ነው " ብለዋል።

* የመፍትሄ ሀሳብን በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተነሳው ጥያቄ ፦

" የመጀመሪያው ነገር ሕገ መንግሥቱን ማክበር ነው። የአዋሳኝ ጉዳይ አይደለም መሀል ትግራይ ላይ ነው ችግሩ እየተፈጠረ ያለው። ወረው በኃይል ከያዙት መሬት ላይ ነው አሁን ደግሞ መልሰው ጥቃት እየፈጸሙ ያለት። ይሄ ትክክል አይደለም። ለማናችንም የሚጠቅም ነገር አይደለም።

መሆን ያለበት ጥያቄ ያለው አካልም በሕጉ መሠረት ካልሆነ በቀር የሆነ አጋጣሚ ተጠቅሞ ‘ጉልበት አለኝ፣ ይጠቅመኛል’ ብሎ ባሰበ ጊዜ የኃይል አማራጭ የሚወስድ ከሆነ፣ ቢያንስ የሕዝቦች ዘላቂ ወዳጅነትና መቀራረብ የሚያረጋግጥ አይደለም። ከዚህ መቆጠብ ነው ያለብን " ብለዋል።

- የፌደራል መንግሥት ሲቪሊያንን የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት ድሮም ቢሆን በውሉም በተመሳሳይ ፤ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖም ከመከላከያ ሰራዊት ውጪ ያሉ ታጣቂዎች ከትግራይ ክልል እንዲወጡ ውሉም ያስገድዳል። አለመውጣታቸውም ብቻ ሳይሆን በየትኛውም የአማራ ታጣቂዎች ባሉበት አካባቢ ሴቶች እየተደፈሩ ናቸው። ሰብዓዊ መብቶች እየተረገጡ ናቸው። ብዙ ጥፋቶች እየተፈጸሙ ናቸው። ስለዚህ ውሉን በአግባቡ ተግባሪዊ ማድረግና በቁጥጥር ሥር መስራት ከተቻለ ብቻ ነው ወደ ሰላም ማምራት የምንችለው።

- በአማራ ክልል እየተፈጸሙ ያሉት ትክክል ስላልሆኑ አደብ መያዝ ያስፈልጋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 8/2016 ዓ/ም
መቐለ

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
#ሆሣዕና

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2016 ዓ/ም ሆሣዕና በዓል አስመልክተው በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተገኝተው ትምህርት፣ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል።

ቅዱስነታቸው ፤ የዛሬው የሆሣዕና በዓል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙት እና የሚከተሉት ህዝብ በተለይ አእሩግ እና ሕጻናት " ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም ሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም " በማለት ጌታችንን መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል መሆኑን አስረድተዋል።

ቅዱስ ፓትርያርኩ ሰሙነ ህማማትንም  አስመልክተው ለመላው ምዕመናን አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ቅዱስነታቸው ፦

" ሰሙነ ሕማማትን እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አስጀምሮ እንዲያስፈጽመን ለብርሃነ ትንሳዔው እንዲያበቃን እግዚአብሔር አምላካችንን እንለምነዋለን።

ሰሙነ ሕማማትን ሁላችንም በየአካባቢያችን ባለው ቤተክርስቲያን ተገኝተን ሰሞነ ሕማማትን ፣ ስግደቱን ፣ ጸሎቱን፣ ልመናውን በሕብረት ወደ እግዚአብሔር አምላካችን እንጸልያለን።

በጸሎታችን ደግሞ ያለውን ችግር ሁሉ እንዲያስወግድልን ፦
- #ሰላሙን
- #ፍቅሩን
- #አንድነቱን እንዲሰጠን የሁላችንም ጸሎትና ምኞት ነውና እግዚአብሔር አምላካችን ከዚያ ያድርሰን ሰሙነ ሕማማቱን በሰላም ያስፈጽመን። "

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
" ሆሣዕና '' (የዐብይ ጾም 8ኛ ሳምንት)

ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሁዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣዔ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ነው።

ሆሣዕና ማለት የቃሉ ትርጉም  " እባክህ አሁን አድን " ማለት ነው።

ዕለቱ ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም ሽማግሌዎች እና ሕፃናት '' ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም '' በማለት በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት ነው፡፡ 

ይህ ዕለት በቤተክርስቲያን ውስጥ ዘንባባ ተይዞ፣ እየተዘመረ እጅግ ልዩ በሆነ ሁኔታ ይታሰባል።

በዐብይ ጾም ከሰርክ ሆሣዕና ጀምሮ እስከ ትንሣዔ ሌሊት ያሉት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡

በዚህ ጊዜ በተለይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት ካህናት መስቀል በእጃቸው አይዙም፣ አያሳልሙም ፣ ይፍቱኝ ተብሎ ወደካህን አይቀረብም፤ ይህ ሳምንት የጌታን የመጨረሻው ስቃይ የሚታሰብበት ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል። የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ  9 እስከ ሐምሌ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት…
#AddisAbaba

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብ (ኦንላይን) ከሚሰጥባቸው ከተሞች አንዱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስለመሆኑ ተሰምቷል።

ይህን ተከትሎ የፈተና ቅድመ ዝግጅት ተግባራት ላይ ያተኮረ ውይይት ዛሬ ሲካሄድ ውሏል።

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊው ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ፤ " የ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በከተማው በኦንላይን ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው " ብለዋል።

ለፈተናው ኮምፒዩተሮች፣ ላፕቶፖችና ታብሌቶችን ጨምሮ ሌሎች ግብአቶችን የማሟላት ስራ ተጀምሯል ተብሏል።

የግል ትምህርት ቤቶች ለፈተናው የሚያስፈልጉ ግብአቶችን ከወዲሁ እንዲጀምሩ ጥሪ ቀርቧል።

ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ማሳወቁ ይታወሳል።

ሙሉ በሙሉ ፈተናው በኦንላይን ባይሰጥም  በተመረጡ ከተሞች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የቀሩት ተማሪዎች በተለመደው ሁኔታ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በወረቀት ይፈተናሉ።

እስካሁን በየትኞቹ ከተሞች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን ይወስዳሉ የሚለው አይታወቅም። በምን አግባብ ተማሪዎቹ እንደሚመረጡም ለጊዜው በይፋ የሚታወቅ ነገር የለም።

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ  9 እስከ ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ🚨

“ በጀኔተር ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ የ1 ሰው ሕይወት አልፏል ” - አቶ ንጋቱ ማሞ

ትላንት ምሽት 3:03 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ማርያም ማዞሪያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በእሳት አደጋ የ1 ሰው ሕይወት ማለፉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያው አቶ ንጋቱ ማሞ በሰጡት ቃል፣ “ ኤሌክትሪክ በመቋረጡ ጀነሬተር ለማስነሳት ነዳጅ በመጨመር ላይ የነበረ የ26 ዓመት የሆቴል ሠራተኛ በጀነሬተሩ ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ ወዲያው ሕይወቱ አልፏል ” ብለዋል።

“ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች በስፍራው ፈጥነው ቢደርሱም በጀነሬተሩ ላይ በተፈጠረው ከፍተኛ እሳት አስቀድሞ ሕይወቱ  አልፏል ” ነው ያሉት።

አቶ ንጋቱ፣ “ በጄኔሬተር የነዳጅ ታንከር ውስጥ ነዳጅ ከተጨመረ በኋላ #ቫልቩ በአግባቡ መዘጋቱን ማረጋገጥ ፣ እንዲሁም ጄነሬተሩ አስቀድሞ አገልግሎት ሲሰጥ ከቆየና ግለት ካለ ነዳጅ ከመጨመር መቆጠብ ያስፈልጋል ” ሲሉ አስገንዝበዋል።

በሌላ በኩል ፥ የበዓል ስራዎች እንቅስቃሴዎች አሁንም ድረስ ያልጠተናቀቁ በመሆኑ ህብረተሰቡ ከኮሚሽን መስሪያ ቤቱ እየተላለፉ ያሉ የጥንቃቄ መልዕክቶች እንዲተገብር አሳስበዋል።

የእሳትና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች ሲያጋጥሙ ፣ እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎት ማህበረሰቡ በኮሚሽኑ ስልክ #በ939 ላይ ፈጥኖ ደውሎ እንዲያሳውቅ ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪ መረጃ ፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በስሊንደር ፍንዳታ ምክንያት የ1 ሰው ህይወት ማለፉን ገልጿል።

የድሮው ቄራ አካባቢ ትላንት ቀን 9:30 በአነስተኛ መጠጥ ቤት ውስጥ ድስት ተጥዶበት በነበረ ስሊንደር ላይ በተፈጠረው ፍንዳታ ዕድሜው 30 ዓመት የሚገመት 1 ሰው ህይወቱ ያለፈ ሲሆን በ3 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ህክምና ተወስደዋል።

ፖሊስ በበዓል ወቅት የምንጠቀማቸውን ምግቦች ስናበስል #ከሲልንደር_አጠቃቀም ጋር በተያያዘ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #አዲስአበባ

ዛሬ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ ' ከፖሊስ ስራ ' ጋር በተያያዘ ሜክሲኮ አካባቢ በሚገኘው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዋና መስሪያ ቤት ፕሮግራም አለ።

ይህ ተከትሎ መንገዶች ተዘግተዋል።

የተዘጉት መንገዶች ፦
- ከልደታ በላይኛው መንገድ  ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከአፍሪካ ህብረት  ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከጠማማ ፎቅ  በንግድ ምክር ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከገነት መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከሰንጋ ተራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከዲአፍሪክ ሆቴል ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከቡናና ሻይ በላይኛው መንገድ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ ሲሆኑ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ ሆነው እንደሚቆዩ ነው የአዲስ አበባ ፖሊስ ያሳወቀው።

በመሆኑም ፦
° በስራ ላይ ምትገኙ አገልግሎት የምትሰጡ አሽከርካሪዎች ፣
° ወደ ስራ እየገባችሁ ያላችሁ ሰራተኞች
° ከስራ ወጥታችሁ ወደ የቤታችሁ እየሄዳችሁ ያላችሁ ነዋሪዎች ይህን መረጃ ተመልክታችሁ አማራጭ መንገድ ተጠቀሙ።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
#ግንቦት20

ነገ የደርግ መንግሥት የወደቀበት የግንቦት 20 በዓል ይከበራል።

በዓሉ በተለይ ኢህአዴግ ስልጣን ላይ በነበረበት ዓመታት በሀገር ደረጃ ስራ እና ትምህርት ተዘግቶ በድምቀት ሲከበር ቆይቷል።

ካለፉት 6 ዓመታት ወዲህ ግን በዓሉ የነበረውን ድምቀት አጥቶ ተቀዛቅዟል። ያም ቢሆን ግን የተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በዕለቱ ዝግ ይሆናሉ።

የዘንድሮው የግንቦት 20 በዓልስ ?

በቅርቡ ይፋ የተደረገው እና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ገና ያልጸደቀው " የሕዝብ በዓላት እና የበዓላት አከባበር ረቂቅ አዋጅ " ተከብረው በሚውሉ ብሔራዊ ባላት ውስጥ ግንቦት 20ን አላካተተም።

በእርግጥ አሁን ላይ ባለውም አዋጅ ሳይካተት እንደ ብሔራዊ በዓል ሲከበር ነው የቆየው።

በዓሉ በሕግ በዓልነቱ ታውቆ አከባበሩም ተዘርዝሮ ያልወጣ ቢሆንም እንደ ብሔራዊ በዓል ሲከበር ቆይቷል ፤ በዕለቱም ሰራተኞች የእረፍት ጊዜ ያገኛሉ።

ከዚህ በተያያዘ በርካቶች " ስለ ነገው በዓል ግልጽ ይሁንልን " ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ብሎ ያሰባቸውን አካላት " ነገ ግንቦት 20 ስራ ተዘግቶ ነው የሚውለው ? "  ሲል ጠይቋል።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " አዲሱ የበዓላት ሕግ ገና አልጸደቀም፤ ስለዚህ ዝግ ነው " ሲሉ አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

በተጨማሪም " ነገ በሚከበረው የግንቦት 20 በዓል መስሪያ ቤት ዝግ ነው ወይስ ክፍት ? " ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ደሲሳ ጥያቄ አቅርቦላቸዋል።

እሳቸውም ፤ " በካላንደር ላይ የተለወጠ ነገር ስለመኖሩ እርግጠኛ አይደለሁም። ካላንደር ይዘጋዋል " ብለዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው፣ " ካላንደር እንደሚዘጋው ነው የምናውቀው ለምን እንዳወዛገበ አይገባኝም " ሲሉ አክለዋል።

አንዳንድ መስሪያ ቤቶች ሠራተኞች ሥራ እንዲገቡ ጠርተዋል መጥራት ይችላሉ ? ለሚለው ጥያቄ በሰጡት ምላሽም ፣ " መስሪያ ቤቶች በራሳቸው ውሳኔ ሥራዎችን ሊያቅዱ ይችላሉ። ከሠራተኞቻቸው ጋር ተስማምተው " ብለዋል።

አክለው " መጥራት ይችላሉ ማን ይከለክላቸዋል። አብዛኞቻችን ሥራ የምንውልበት ጊዜ ይኖራል። ያ ማለት ግን ያንን አፍርሰው ሳይሆን መስሪያ ቤቶች፣ ሠራተኞች በፈቃዳቸው ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" እሁድም እኮ ሠራተኛ የምናስገባበት ወቅት አለ። እንጂ ከዚያ ያለፈ የተለዬ ነገር የለም " ነው ያሉት።

በሌላ በኩል ፥ የአሜሪካ ኤምባሲ ነገ የደርግ መንግሥት የወደቀበትን #የግንቦት_20 በዓል ምክንያት በማድረግ ሙሉ ቀን ስራ ዝግ ሆኖ እንደሚውል አሳውቋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ° " በርካታ መሰረታዊ ሸቀጥ የያዙ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ጣቢያዎች ተንቀሳቅሰዋል " - መንግሥት ° " የዋጋ ጭማሪ ቁጥጥር የአንድ ሰሞን ወሬና ወከና ሆኖ በዛው ጨምሮ እንዳይቀር ተከታተሉልን ፤ከዚህ ቀደም በዘይት የሆነውን አይተናል። ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም " - የ4 ልጆች እናት ሰራተኛ (ከአ/አ) የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ተደረገ ከተባለበት ጊዜ አንስቶ መሰረታዊ በሚባሉ…
🔈 #የዜጎችድምጽ

የ4 ልጆች እናት ሰራተኛ ፦

" እኔ ደመወዜ አንድም ጊዜ ሳይጨምር ይኸው ዘይት ጨምሮ ጨምሮ በሺህ ቤት ገብቷል። እንዴት መኖር እንዳለብኝ አልገባኝም።

ደመወዘኔን ምኑን ከምኑ እንደማደረገው ጠፍቶብኛል።

የሆነ ነገር በተፈጠረ ቁጥር የሚጨምረው ዋጋ ቁጥጥሩ የአንድ ሰሞን ወሬና ወከባ ይሆንና ዋጋው በዛው ጨምሮ ጣራ ነክቶ ይቀራል ፤ ይህ ከዚህ በፊት በዘይት አይተነዋል።

ነጋዴው አያዝንልን፣ የመንግስትም ሰዎች ተገቢና ዘላቂ ቁጥጥር አያደርጉልን ፣ የሚመጣው ሁሉ ግን እኛ ላይ ያርፋል።

እንደ ከዚህ ቀደሙ ' ዋጋ ጨመረ. ' ተብሎ ቁጥጥሩ የአንድ ሰሞን ግርግር ሆኖ በዛው ዋጋ ሁሉ ተሰቅሎ እንዳይቀር መደረግ ያለበት ሁሉ ይደረግ ፤ ኑሮው በጣም ከብዶናል። "

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ለጥንቃቄ_ከጠቀማችሁ

1. በአዲስ አበባ ከተማ የሜትር ታክሲ አገልግሎት የምትሰጡ ወንድም እህቶቻችን እባካችሁ ጥንቃቄ አድርጉ።

ማክሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ገደማ ወደ ጎተራ ማሰለጫ መውረጃ ወይም በተቃራኒ ወደ ቄራ የሚወስደው መስቀለኛ መንገድ አካባቢ አንድ አገልግሎት ሰጪን 3 ተሳፋሪ መስለው የገቡ ወንበዴዎች መሃል አስፓልት ፣ በብዛት መኪና በሚመላለስበት መንገድ ላይ ከውስጥ እቃ ይዘው ሲሮጡ መመልከቱን አንድ የቤተሰባችን አባል መልዕክት አጋርቶናል።

ሹፌሩ ከመኪና ውስጥ አልወረደም ነበር። ምናልባት ቢወርድ ሌላ የነሱ ተባባሪዎች መኪናውን ይዘው ለመጥፋት አስበውም ሊሆን ይችላል ብሏል።

እነዚህ 3 ሰዎች ሁለቱ ከኋላ አንዱ ከፊት የነበሩ ሲሆን በፍጥነት የመኪናውን በር ከፍተው እቃ ይዘው ሲሮጡ ነው የተመለከታቸው።

" ፈጣሪ ነው የሚጠብቀን ነገር ግን በተለይ ምሽት ላይ ስንሰራ የምንጭናቸውን ሰዎች ፦
- ማንነት፣
- ስልክ ቁጥር ፣
- የምንሄድበትን ቦታ ፣
- የሰዎቹን ሁኔታ ድርጊታቸውን፣
- ንግግራቸውን በደንብ እንከታተል። ውስጣችን ጥሩ ስሜት ካልተሰማውም ይቅርብን " ብሏል።

ህይወታቸውን ለማሻሻል፣ ቤተሰባቸውን ለመደገፍ ፣ ልጆቻቸውን ለማኖር ሲሉ ብርድ እና ፀሀይ እየተፈራረቀባቸው ቀን ፣ ምሽት ፣ ለሊት ሳይሉ የሚሰሩ ወገኖቻችንን ፈጣሪ ከክፉ ይጠብቃቸው።

ዘራፊዎችም ዛሬ ላይ ተይዘው ነገ የሚለቀቁ ከሆነ ከወንብድና ተግባራቸው ስለማይመለሱ እጅግ ጠንካራ ቅጣት ሊጣልባቸው ይገባል።

የሰረቁበትን ቀን እንዲረግሙ የሚያደርግ ቅጣት ሊጠብቃቸው ይገባል።

ሰው ለልጆቹ ፣ ለቤተሰቦቹ ለራሱ ህይወት ሲል ከባድ ዋጋ እየከፈለና በሰላም ጥሩ ሰራተኛ ዜጋ ሆኖ ሀገሩን ህዝቡን እያገለገለ ካለ በበቂ ሁኔታ ከወንጀል ሊጠበቅ ይገባዋል።

2. በመኪና ተደራጅተ የሚዘርፉ ዛራፊዎች አሁንም በከተማው አሉ።

በቅርቡ ፥ መካኒሳ አካባቢ አንድ ግለሰብ በገዛ ሰፈሩ ያውም ጠዋት ላይ በ " ቪትዝ " ተሽከርካሪ የመጡ ወንበዴዎች አንገቱን በማነቅ ንብረቱን ዘርፈው መሬት ላይ ጥለውት ጠፍተዋል።

" አውቶብስ ተራ " አካባቢ በተመሳሳይ አንድ ወጣት በ ' ቪትዝ ' ተሽከርካሪ ላይ በመሆንና ውሃ በመድፋት " ና እንጥረግልህ " በማለት ለመዝረፍ ሙከራ አድርገዋል ፤ ምንም እንኳ ክፉ ሃሳባቸው ባይሳካም።

እነዚህ ባለመኪና ወንበዴዌች ምናልባት ብዙ ቦታ መሰል ተግባራትን እየፈጸሙ ይሆናል።

ከወራት በፊት ሩወንዳ አካባቢ ለሊት በ ' DX መኪና ' ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ወንበዴዎች አንድን ግለሰብ ሞባይል ስልክ በገጀራ አስፈራርተው መዝረፋቸውን ነግረናችሁ ነበር።

መኪና የምታከራዩ ወይም መኪና ለሰው የምትሰጡት ሰዎችም ጥንቃቄ አድርጉ ማነው ፣ ለምን አገልግሎት እየተጠቀመ ነው የሚለውን አጣሩ።

ፖሊስ ይህንን ጉዳይ ከምንጩ ለማድረቅ መስራት አለበት።

በከተማው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመንገድ ትራፊክ መብራት ላይ ስርቆት በጅጉ ቀንሷል። ይህ አበረታች ተግባር ጭራሽ መኪና ይዘው ለዝርፊያ በተሰማሩ አካላት ላይም መቀጠል አለበት።

ሰዎች ቀንም ይሁን ማታ ሳይሳቀቁ መንቀሳቀስ እንዲችሉ መደረግ አለበት። ህግ ቀን ቀን ብቻ የሚሰራ ማታ የማይሰራ እስኪመስል ድረስ ዘራፊዎች የሚያደርጉን እንቅስቃሴ መገታት መቻል አለበት።

3. የጸጥታ አካላትን የሚመስል ልብስ ለብሰው የሚዘርፉም አሉ።

አንድ የቤተሰባችን አባል በመንገዱ የገመጠውን አጋርቶናል።

ድርጊቱ የተፈጸመው በዚህ ወር  አለርት ሆስፒታል አካባቢ ነው።

መኪናውን እያሽከረከረ በሚሄድበት ወቅት የጸጥታ ኃይል ልብስ የሚመስል የለበሱ በግሩፕ የተሰባሰቡ ሰዎች (8-10) ድቅድቅ ያለ ጨለማ ውስጥ ሆነው ሊያስቆሙት ይሞክራሉ።

ነገር ግን እውነተኛ እና ትክክለኛ የጸጥታ አካላት ሰዎች እንዳልሆኑ ይጠረጥራል። ምክንያቱም ከዚህ ቦታ በፊት (ብዙም ሳይርቅ) ሌላ የደህንነት ፍተሻ ተፈትሾ ነበር።

እንዚህ ሰዎች ቁም ያሉት ቦታ ድቅድቅ ጨለማ እና የሚያስፈራ ስለነበር ወደፊት ትቷቸው ሲሄድ ሁለት የተጎዱ ሰዎች መሬት ላይ ተኝተው ተመልክቷል። ሌላ መኪና ስላልነበረና ለህይወቱም በመስጋቱ በፍጥነት ከቦታው ርቆ ሄዷል።

ምናልባት እነዚህ ሰዎች ለፍተሻ ብለው መኪናቸውን አስቁመዋቸው ዘርፈዋቸው ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬውን ገልጿል።

የፖሊስ የደህንነት ፍተሻ በጣም አስፈላጊ ቢሆንም ከየትኛውም አካል ፍቃድ ሳያገኙ ለመሰል እንቅስቃሴ የሚሰማሩ ካሉ አጥንቶ እርምጃ መውሰድ ይገባል። የማያዳግም አስተማሪ ቅጣትም መቀጣት ይገባል።

ሌላው የየትኛውም የሀገሪቱ የጸጥታ ልብስ በሲቪል ሰዎች / አባል ባልሆኑ ሰዎች እየተለበሰ በማኛውም መንገድ ሚዲያ ላይም ጭምር መታየት የለበትም። ሁሉም ሰው ለፍቶ ነው የክብር ልብሱን የሚለብሰውና ማንም እየተነሳ የጸጥታ ልብስ እየለበሰ መታየት ሌላውም ይህን እንዲለማመድ መደረግ የለበትም ፤ ልብሱም መከበር አለበት።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

#ቲክቫህኢትዮጵያ
#አዲስአበባ

@tikvahethiopia