TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ° " በርካታ መሰረታዊ ሸቀጥ የያዙ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ጣቢያዎች ተንቀሳቅሰዋል " - መንግሥት ° " የዋጋ ጭማሪ ቁጥጥር የአንድ ሰሞን ወሬና ወከና ሆኖ በዛው ጨምሮ እንዳይቀር ተከታተሉልን ፤ከዚህ ቀደም በዘይት የሆነውን አይተናል። ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም " - የ4 ልጆች እናት ሰራተኛ (ከአ/አ) የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ተደረገ ከተባለበት ጊዜ አንስቶ መሰረታዊ በሚባሉ…
🔈 #የዜጎችድምጽ

የ4 ልጆች እናት ሰራተኛ ፦

" እኔ ደመወዜ አንድም ጊዜ ሳይጨምር ይኸው ዘይት ጨምሮ ጨምሮ በሺህ ቤት ገብቷል። እንዴት መኖር እንዳለብኝ አልገባኝም።

ደመወዘኔን ምኑን ከምኑ እንደማደረገው ጠፍቶብኛል።

የሆነ ነገር በተፈጠረ ቁጥር የሚጨምረው ዋጋ ቁጥጥሩ የአንድ ሰሞን ወሬና ወከባ ይሆንና ዋጋው በዛው ጨምሮ ጣራ ነክቶ ይቀራል ፤ ይህ ከዚህ በፊት በዘይት አይተነዋል።

ነጋዴው አያዝንልን፣ የመንግስትም ሰዎች ተገቢና ዘላቂ ቁጥጥር አያደርጉልን ፣ የሚመጣው ሁሉ ግን እኛ ላይ ያርፋል።

እንደ ከዚህ ቀደሙ ' ዋጋ ጨመረ. ' ተብሎ ቁጥጥሩ የአንድ ሰሞን ግርግር ሆኖ በዛው ዋጋ ሁሉ ተሰቅሎ እንዳይቀር መደረግ ያለበት ሁሉ ይደረግ ፤ ኑሮው በጣም ከብዶናል። "

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM