TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሙሉ_መግለጫ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዮች ላይ የተሰጠ የአቋም መግለጫ!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥንታዊት፣ ታሪካዊትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆኗ መጠን አገራችን ኢትዮጵያ አሁን ከደረሰችበት የሥልጣኔና የእድገት ደረጃ ከመድረሷ በፊት ብራና ዳምጣ፣ ቀለም በጥብጣና ፊደል ቀርጻ ትምህርትና ሥልጣኔን ያስጀመረች፣ የመጀመሪያው ዩኒቨርሲቲና የትምህርት ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሥርዓቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ መዋቅራዊ አደረጃጀት ገና ሳይኖረው ፍርድ እንዳይጓደልና ደሃ እንዳይበደል በማሰብ የፍትሐ-ነገሥት መምህራኖቿን በዳኝነት መድባ የፍትሕ ሥርዓትን የመሠረተች፣ ዜጎችን በሥነ-ምግባርና በግብረ-ገብነት ትምህርት ኮትኩታ በማሳደግ ሀገር ወዳድ ትውልድ በማፍራት መሠረት የጣለች፣ በውጭ ወራሪ ኃይል የሀገር ሉዓላዊነት በተደፈረ ወቅት የእምነቱ ተከታይ ምእመናኖቿና አገልጋይ ካህናቶቿ እንዲሁም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የእምነታችን መገለጫ የሆነውን የቃልኪዳኑን ታቦት ይዘው በየጦር ግንባሩ በመሰለፍና በመሰዋት እንኳንስ ሕዝቦቿ ምድሪቱም ለወራሪ ጠላት እንዳትገዛ በማውገዝ የሀገር ሉዓላዊነት ያስከበረችና ኢትዮጵያ ሀገራችን ከሌሎች አፍሪካ አገራት በብቸኝነት ቅኝ ገዥዎች ያልደፈሯት አገር ተብላ በታሪክ ድርሳናት እንድትመዘገብ ግንባር ቀደም ሚና የተጫወተች የሀገር ባለውለታ እናት ቤተ ክርስቲያን መሆኗን እንኳንስ እኛ ልጆቿ ይቅርና የታሪክ ምሁራን ዘወትር በየአደባባዩ የሚመሰክሩት በብዕር ሳይሆን ለነጻነት በተከፈለ በአበው አባቶቻችን ደም የተጻፈ አኲሪ ታሪካችን ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-07-3
#Professor

11 ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ተሰጣቸው።

አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ11 ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።

በዩኒቨርሲቲ የውስጥና ውጭ ገምጋሚዎች በጥልቀት ተመርመሮ ፣ በኮሌጆች የአካዳሚክ ኮሚሽኖች ተፈትሾ ፣ በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ታይቶና ይሁንታ አግኝቶ የቀረበለትን መረጃ ከተመለከተ በኋላ የየኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ ለ11 ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።

የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው፦

1. ዶ/ር ቁምላቸው የሺጥላ፣  
2. ዶ/ር ሽመልስ አሰፋ፣  
3. ዶ/ር መንግስቱ ለገሰ፣
4. ዶ/ር ጉታ ዘነበ፣
5. ዶ/ር ፋሲል አሰፋ፣  
6. ዶ/ር ጥልዬ ፈይሳ፣
7. ዶ/ር ብሩክ ላምቢሶ፣  
8. ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ አለሙ፣  
9. ዶ/ር ዘበነ ክፍሌ፣  
10. ዶ/ር ተረፈ ደገፋ እና
11. ዶ/ር ንጉሴ ደየሳ መሆናቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ምሁራኑ የ #ሙሉ_ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው
በመማር ማስተማር፣ በጥናትና ምርምር እንዲሁም በማኅበረሰብ ዐቀፍ እና ሙያዊ አገልግሎት የነበራቸው አበርክቶ ተገምግሞ መሆኑ ታውቋል።

@tikvahuniversity @tikvahethiopia
#Kombolcha

#ሙሉ_በሙሉ የግንባታ ወጭው በውጭ ሀገራት በሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዳያስፖራዎች የሚሸፈን መልቲ ጀነራል ሆስፒታል የመሰረት ድንጋይ የቀመጠ።

ሆስፒታሉ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ኮምቦልቻ ወረዳ የሚገነባ ሲሆን ከ300 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ይሆንበታል ተብሏል።

ፕሮጀክቱ በ1 ነጥብ 6 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ሲሆን ወጪው ሙሉ በሙሉ በውጭ ሀገራት በሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሚሸፈን ነው።

በወረዳው ለሚገነባው ሆስፒታል የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ጀማል ዪስፍ፣ የኮምቦልቻ ወረዳ አስተዳደር አቶ አልዪ ኢብራሂም እና የዲያስፖራ ተወካይ አቶ ፈረሃን አህመድ የመሰረት ድንጋዩን አስቀምጠዋል።

#ENA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አድማስ_ዲጅታል_ሎተሪ ! የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር የአድማስ  ድጅታል ሎተሪ የአንደኛ ዙር ዛሬ ነሐሴ 13 ቀን 2014 ዓ/ መውጣቱን ገልጿል። የወጡ ዕድለኛ የሚያደርጉ ቁጥሮች ፡- 👉 የ1ኛ ዕጣ የ1.5 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው ዕጣ  ቁጥር -002031699514 👉 2ኛ ዕጣ  የ800 ሺህ ብር የሚያሸልመው ዕጣ  ቁጥር -002294990063 👉 3ኛ ዕጣ የ350 ሺህ ብር የሚያሸልመው ዕጣ  ቁጥር…
#DigitalLottery

የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስጀመረው " አድማስ " የተሰኘው ድጂታል ሎተሪ የመጀመሪያው ዙር እጣ ትላንት ማውጣቱን አሳውቋል

የዲጂታል ሎተሪ ዕጣው ቀጣይነት እንዳለው የገለፀው አስተዳደሩ የሁለተኛ ዙር  ዕጣው  መስከረም 11 ቀን 2015 የሚወጣ መሆኑን ገልጿል።

የአድማስ ዲጅታል ሎተሪ በአንደኛ ዕጣው 1.5 ሚሊዮን ብር፣ በሁለተኛ 800 ሺህ ብር፣ በሶስተኛ 350 ሺህ ብር ጨምሮ ሌሎችም የገንዘብ ዕጣዎችን ያካተተ ነው።

ከብሄራዊ የሎተሪ አስተዳደር እንዳገኘነው መረጃ ዕጣው በ605 ላይ ማንኛውም ፊደል በመላክ ወይም በቴሌብር ወደ *127# በመደወል በ3 ብር ነው የሚቆረጠው።

(ከላይ በትላትናው ዕለት የወጣው የመጀመሪያ ዙር ዕጣ #ሙሉ የባለዕድለኞች ቁጥር ተያይዟል)                            

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ETHIOPIA

ከውጭ የሚገቡ ሆነ ሀገር ውስጥ የሚመረቱ #የኤሌክትሪክ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች፣ የቤት አውቶሞቢሎችና የእቃ መጫኛ ተሽከርካሪዎች ላይ ዝቅተኛ የጉምሩክ ታሪፍ የሚጣልባቸው ሲሆን ከተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ከኤክሳይዝ ታክስና ከሱር ታክስ #ነፃ መደረጋቸውን ገንዘብ ሚኒስቴር አሳውቋል።

የታክስ ማሻሻያው በርካታ ዓላማዎች ያሉት ሲሆን ከዓላማው አንዱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እንዲቀርቡ ለማስቻል ነው።

በታክስ ማሻሻያው መሰረት (የቤት አውቶሞቢሎች) ፦

1ኛ. ሙሉ በሙሉ ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ አውቶሞቢሎች ከጉምሩክ ቀረጥ፣ ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ #ሙሉ_በሙሉ_ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡

2ኛ. በከፊል ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ የኤሌክትሪክ የቤት አውቶ ሞቢሎችን 5 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ #ሙሉ_በሙሉ_ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡

3ኛ. ሙሉ ለሙሉ ተገጣጥመው ያለቀላቸው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢሎች ወደ ሀገር ሲገቡ 15 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ #ሙሉ_በሙሉ_ነጻ እንዲሆኑ ተወስኗል፡፡

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት በአዲስ አበባ ከ4 ወራት በላይ ተቋርጦ የነበረዉ የመታወቂያ #እድሳት አገልግሎት በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል። @tikvahethiopia
#መታወቂያ

የአዲስ አበባ የወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ፤ የተፈቀዱ አዲስ የነዋሪነት ምዝገባ እና የመታወቂያ አገልግሎቶችን አሳውቋል።

በከተማ አስተዳደሩ ተቋርጦ የነበረዉ የመታወቂያ እድሳት አገልግሎት ከህዳር 1/2015ዓ.ም ጀምሮ የተፈቀደ መሆኑ ያስታወሰው ኤጀንሲው አሁን ደግሞ ፦

👉 በቤተሰብ ማህደር ተመዝግበው 18 ዓመት የሞላቸው ነዋሪዎች፤

👉 ለህክምና ክትትል የሚፈልጉ እና ህጋዊ የህክምና ማስረጃ የሚያቀርቡ ዜጎች፤

👉 በከተማዉ ፍ/ቤት መብት ለማስከበር የሚያበቃቸዉ የመብት ጉዳይ ኖሯቸዉ #የነዋሪነት_መታወቂያ ለሚያስፈልጋቸዉ ነዋሪዎች አሰራርን በመከተል አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታዎች ሲያሟሉ አገልግሎት እንዲያገኙ መፈቀደኑን ገልጿል።

ይህ የተፈቀደው ከትላንት ዓርብ ህዳር 23/2015 ዓ.ም ጀምሮ ሲሆን ተገልጋዮች ሊኖር የሚችለውን ጫና ከግምት በማስገባት በተረጋጋ ሁኔታ ቀርባድ አገልግሎት እንዲያገኙ መልዕክት አስተላልፏል።

በሌላ በኩል ፤ የአዲስ አበባ ከተማ የወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ዛሬ ቅዳሜ ህዳር 24 #ሙሉ_ቀን በሁሉም የወረዳ ፅ/ቤቶች አገልግሎት እንደሚሰጥ የገለፀ ሲሆን ነገ እሁድ ህዳር 25 አገልግሎት ዝግ መሆኑን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA ከውጭ የሚገቡ ሆነ ሀገር ውስጥ የሚመረቱ #የኤሌክትሪክ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች፣ የቤት አውቶሞቢሎችና የእቃ መጫኛ ተሽከርካሪዎች ላይ ዝቅተኛ የጉምሩክ ታሪፍ የሚጣልባቸው ሲሆን ከተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ከኤክሳይዝ ታክስና ከሱር ታክስ #ነፃ መደረጋቸውን ገንዘብ ሚኒስቴር አሳውቋል። የታክስ ማሻሻያው በርካታ ዓላማዎች ያሉት ሲሆን ከዓላማው አንዱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በተመጣጣኝ…
ቁጥሮች ...

(ኢትዮጵያ - የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች)

[ ሪፖርተር ጋዜጣ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ በርኦ ሐሰንን ቃለ መጠይቅ አድርጎ ካወጣው ዘገባ የተወሰደ ]

• መስከረም ወር ላይ የገንዘብ ሚኒስቴር ካደረገው በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች የታክስ ማሻሻያ በኋላ ከ7,000 በላይ ተሽከርካዎች አገር ውስጥ ገብተዋል።

• ከብሔራዊ ባንክ ጋር የኤሌክትሪክ አውቶብሶች እንዲጉ መግባባት ላይ ተደርሶ እንቅስቃሴዎች የተጀመረ ሲሆን በቅርቡ 1,300 የኤሌክትሪክ አውቶቡሶች ወደ አገር ቤት ይገባሉ።

• የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የአሥር ዓመት ዕቅድ 48,000 የብዙኃን ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ የኤሌክትሪክ አውቶብሶች ፤ በተጨማሪም 148,000 የኤሌክትሪክ #አውቶሞቢሎችን አገር ውስጥ እንዲገቡ ማድረግ ነው።

#ማስታወሻ

በመስከረም ወር ይፋ የሆነው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነፃ ማስገቢያ ማሻሻያ ፦

1ኛ. ሙሉ በሙሉ ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ አውቶሞቢሎች ከጉምሩክ ቀረጥ፣ ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ #ሙሉ_በሙሉ_ነጻ ናቸው።

2ኛ. በከፊል ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ የኤሌክትሪክ የቤት አውቶሞቢሎችን 5 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ #ሙሉ_በሙሉ_ነጻ ናቸው።

3ኛ. ሙሉ ለሙሉ ተገጣጥመው ያለቀላቸው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢሎች ወደ ሀገር ሲገቡ 15 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ #ሙሉ_በሙሉ_ነጻ ናቸው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሰልፉ ተራዝሟል " ቅዱስ ሲኖዶስ ምንም እንኳን የአቋም ለውጥ ባያደርግም ትላንት በነበረው ውይይት መንግስት የቤተክርስቲያኗን ጥሪ በመቀበል የቤተክርስቲያኗን ችግር ለመፍታት #በመስማማቱ ነገ ሊደረግ የታሰበው ሰላማዊ ሰልፍ መራዘሙን አሳውቋል። @tikvahethiopia
#Update


ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩን ጨምሮ አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ያካተተ ልኡክ በትናትናው እለት ከመንግሥት ጋር ባደረጉት ውይይት መንግሥት የቤተ ክርስቲያኒቱን አቋም #ሙሉ_በሙሉ የተቀበለ ቢሆንም ይህንን ለማስፈጸም የሚያስችል የአፈጻጸም የድርጊት ጊዜ የሚያስፈልግ በመሆኑ እሁድ የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ/ም እንዲካሔድ የተወሰነው ሀገር ዓቀፍ እና ዓለም አቀፍ የአደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ ለተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም መወሰኑን ቅዱስ ሲኖዶስ አሳውቋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

Credit : EOTC TV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሰበር_ዜና የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ  የሦስቱን አባቶችና የ20ቹን መነኮሳት ውግዘት ከዛሬ 21/07/2015 ዓ/ም ጀምሮ ማንሳቱን በሰጠው መግለጫ አሳውቋል። ውግዘቱ የተነሳላቸው ቤተ ክርስቲያን በሰጠቻቸው ማዕረግ እንዲጠሩም ገልጿል። በዚህ መሠረት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ ተብለው እንደሚጠሩና ወደ ነበረ የአባትነት ኃላፊነታቸው የሚመለሱ ሲሆን…
ቅዱስ ሲኖዶስ ምን ውሳኔ አስተላለፈ ?

ካሁን ቀደም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበትና በመቀጠል አቶ ሽመልስ አብዲሳ የኦሮምያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት በተገኙበት በተደረገው ውይይት በተደረሰው 10ሩ የስምምነት ነጥቦች መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ በስፋት ከተወያየ በኋላ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል።

ከውሳኔዎቹ መካከል ፦

- የካቲት 8 ቀን 2015 ዓ.ም. የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ መሪነት ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ በመምጣት እስካሁን ድረስ በበዓታቸው ጸንተው የቆዩት 3ቱም የቀድሞ ሊቃነ ጳጳሳት ማለትም ፦
👉 ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣
👉 ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ
👉 ብፁዕ አቡነ ዜናማርቆስ ላይ አስቀድሞ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም. በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተላለፈው ውግዘት ከዛሬ መጋቢት 21 ቀን 2015ዓ.ም. ጀምሮ #ተነስቷል፡፡

- ውግዘቱ የተነሣላቸው 3ቱም ሊቃነ ጳጳሳት ከዛሬ መጋቢት 21 ቀነ 2015ዓ.ም. ጀምሮ በቀድሞ የሊቀ ጳጳስነት ማዕረጋቸውና ስማቸው ማለትም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ሊቀጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ሊቀጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ዜናማርቆስ ሊቀጳጳስ ተብለው እንዲጠሩና አስቀድሞ ተመድበው ይሰሩበት በነበረው የሥራ ኃላፊነታቸው ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

- ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት በተደረገው ውይይት በተደረሰው ስምምነት መሠረት ጥሪውን ተቀብለው ለስምምነቱ ተገዥ በመሆን በጽሑፍ ጥያቄያቸውን ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ያቀረቡት 20ዎቹ የቀድሞ መነኮሳት ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም. በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ የተላለፈው ውግዘት ከዛሬ መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ #ተነስቷል፡፡ ቀሪዎቹ 5ቱ ባለው ጊዜ ተጠቅመው ወደቤተ ክርስቲያናቸው እንዲመለሱ ቅዱስ ሲኖዶስ በድጋሚ ያሳሰበ ሲሆን ውግዘቱን በሚመለከት በቋሚ ሲኖዶስ በኩል ታይቶ እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

- ውግዘቱ የተነሣላቸው 20ዎቹም የቀድሞ መነኮሳት አስቀድሞ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ከዲቁና እስከ ቁምስና ባለው ማዕረገ ክህነታቸው እንዲያገለግሉ እና በምንኩስና ስማቸውም እንዲጠሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

- ሃያዎቹ (20ዎቹ) የቀድሞ መነኮሳት የሥራ ምደባን በተመለከተ በተደረሰው ስምምነት መሠረት በቀድሞው የሥራ መደብ ደረጃቸው እንዲመደቡ ቅዱስ ሲኖዶስ በመወሰን ዝርዝር ጉዳዩ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ በኩል እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ አዟል።

- ምንም እንኳን አስቀድሞ ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጋር በተደረገው ውይይትና ስምምነት መሠረት የታሰሩት ግለሰቦች በሙሉ እንደሚፈቱ ቃል የተገባ ቢሆንም እስካሁን ድረስ በርካታ ሰዎች በእስር ላይ የሚገኙ ስለሆነ መንግስት አስቀድሞ በገባው ቃል መሠረት ሁሉንም እስረኞች እንዲፈታ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥብቅ አሳስቧል።

- በተከሰተው ችግር ከሀገረ ስብከት እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ባሉት የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር ላይ በኃላፊነት ተመድበው ሲሰሩ ቆይተው በችግሩ ምክንያት ተፈናቅለው የቆዩት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሀገረ ስብከትና የወረዳ ቤተ ክህነት ሠራተኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት በምድብ ሥራቸው ላይ እንዲቀጥሉ ከፌዴራል ጀምሮ በየደረጃው ያሉ የመንግስት አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፡፡

(#ሙሉ ውሳኔው እንዲሁም መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#Woldia

በወልድያ ከተማ የሰዓት እላፊ ታወጀ  ፤ ጥብቅ የሆኑ ክልከላዎችም ተጥለዋል።

ወልድያ ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ኮማንድ ፖስት ላልተወሰነ ጊዜ የሚቆይ የሰዓት እላፊ ገደብ እና ክልከላ ማስቀመጡ ተገልጿል።

ክልከላዎቹ ፦

- ጭፈራ ቤቶች፥ ካፍቴሪያዎች፣ ሬስቶራንቶች እና የመሳሰሉት ማንኛውም መጠጥ ቤቶች ከምሽቱ 2:00 ሰዓት በኋላ አገልግሎት መስጠት አይችሉም።

- ለባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 1:00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12:00  ሰዓት ባለው ጊዜ መንቀሳቀስ የተከለከለ ሲሆን ፤ ከተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ለጸጥታ ሥራ ከተመደቡ ተሽከርካሪዎች ውጭ በዚህ ምደባ ስምሪት ያልታቀፉ የመንግሥት ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 2:00 እስከ ጧቱ 12:00  ብቻ እንዲሆን ተወስኗል።

- የሰው እንቅስቃሴ ለጸጥታ ሥራ ከተመደበው ሰው ውጭ ከምሽቱ 3:00 እስከ ጧቱ 12:00 ሰዓት ባለው ጊዜ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

- በማንኛውም ቦታና ጊዜ ለጸጥታ ሥራ ስምሪት ከተመደበ አካል ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ ተከልክሏል።

- አድማ መቀስቀስ፣ ማድረግና ማስተባበር እንዲሁም መደበኛ ሥራን ማስተጓጎል በጥብቅ ተከልክሏል።

- የመንግሥትን የታጠቀ ኀይል ያስከዳ፣ በተለያየ መንገድ አማሎ የጦር መሳሪያ የገዛ፣ የለወጠ፣ ባልተገባ መንገድ መታወቂያ የሰጠ፣ መንገድ የመራ ማንኛውም አካል በሕግ ተጠያቂ ይሆናል ተብሏል።

- የመንግሥት የጸጥታ ኀይል ሕግና ስርዓትን ለማስከበር በሚያከናውናቸው ተግባሮች ዙሪያ ማንኛውም ሰው የመተባበር ግዴታ ተጥሎበታል ፤ የማይተባበር በሕግ ይጠየቃል ተብሏል።

የኮማንድ ፖስቱ በአብዛኛውን በሌሎች ከተማዎች የተጣሉ ክልከላዎችን አይነት ይዘት ያለው ክልከላ ነው የጣለው። (#ሙሉ ዝርዝሩ ከላይ ተያይዟል)

ኮማንድ ፖስቱ ይህ ውሳኔ የተላለፈባቸው ምክንያቶች ፦ በከተማው የተጀመሩ ልማቶችን " አመጹን መቀላቀል ሲገባህ ልማትን እያስቀጠለክ " በሚል ዛቻ ልማትን የማደናቀፍ ፤ በሙስና፥ በሌብነት፥ እና በተለያዩ ብልሹ ወንጀሎች ስጋት ያለባቸው አካላት የዕለት ጉርስ ፈላጊዎችን በገዘብ በመግዛት ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠርና ለማባባስ የሚያደርጉት ሙከራ በመረጃ ደረጃ የተገኘ በመሆኑ ነው ብሏል።

ከዚህ ባለፈ የትንሳኤ እና የረመዳን ሃይማኖታዊ ሁነቶችን በሰላም ለማጠናቀቅ ለዕኩይ ዓላማ የተሰማሩ ሰርጎ ገቦችን ለመቆጣጠር ነው ሲል አሳውቋል።

(የወልድያ ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ኮማንድ ፖስት ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
የብልፅግና ፓርቲ የወረዳ አመራር ተገደሉ።

ከትላንት በስቲያ ከአዳማ ወደ አዋሽ በሚወስደው መንገድ ላይ በተከፈተ ተኩስ በአፋር ክልል በገቢ ረሱ የሓንሩካ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኡመር ለማ መገደላቸውን የአፋር ክልል የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት አሳውቋል።

ጥቃቱን " አሸባሪዎች " ናቸው የፈፀሙት ያለው የአፋር ብልፅግና " በፈፀሙት ድንገተኛ ጥቃት የአቶ ኡመር ለማን ህይወት ቀጥፈዋል ብሏል።

ፅ/ቤቱ ባሰራጨው መረጃ ጥቃት አድራሾቹ ላይ የተወሰደ እርምጃ ይኖር እንደሆነ እና ጥቃቱ በተፈፀመበት ወቅት በሌሎች ላይ ጉዳት ደርሶ እንደሆነ በዝርዝር ያሳወቀው ነገር የለም።

ከዚህ ቀደም በዚሁ ቀጠና እጅግ የለየለት የወንጀል ተግባር በታጠቁ አካላት እንደሚፈፀም ሲገለፅ እንደነበር ይታወሳል።

በዚሁ መስመር ታጣቂዎች እንደሚንቀሳቀሱና እንደ ከተማዎች ውስጥ በመግባት ጭምር ሰላማዊ ሰዎችን መግደል፣ በየመንገዱ ሰላማዊ ሰዎችን እያገቱ ከፍተኛ ገንዘብ የመጠየቅ ፤ በአጠቃላይ በቀጠናው ወጥቶ ለመግባት ከፍተኛ ስጋት የመፍጠር እንቅስቃሴ እንደሚያደርጉ የአካባቢው የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በተደጋጋሚ መግለፃቸው ይታወሳል።

መንግሥት ይህንን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የሆነና ዜጎች ቀንም ማታም ያለስጋት ሲንቀሳቀሱበት የነበረውን ቀጠና ይህን ያህል ጊዜ #ሙሉ_በሙሉ ከታጣቂዎች እንቅስቃሴና የወንጀል ተግባር ነፃ ማድረግ ለምን እንዳልቻለ የብዙሀኑ ጥያቄ ነው።

እስከ ዛሬ ድረስ በንፁሃን ላይ ሲፈፀሙት ለነበሩት ጥቃቶች ፣ ዝርፊያዎች ወንጀለኞቹ መቼ ነው ወደ ፍርድ አደባባይ የሚቀርቡት ? መቼስ ነው ፍትህ የሚሰጠው ? የሚለውም ጉዳይ መልስ ይፈልጋል።

@tikvahethiopia