TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሳዛኝ ዜና‼️

በኢሉአባቦር ዞን #መቱ ከተማ በደረሰ የግንብ አጥር #መደርመስ አደጋ የአንድ ቤተሰብ አባል የሆኑ ሰባት ሰዎች ህይወት አለፈ። የመቱ ከተማ ፖሊስ ጽህፈት ቤት የወንጀል ምርመራና ፍትህ አሰጣጥ ሥራ ሂደት መሪ ኮማንደር ተሾመ ታደሰ ለኢዜአ እንደገለጹት አደጋው ትላንት ከሌሊቱ 8፡00 ሰዓት ላይ የደረሰው በከተማው ቀበሌ 01 ውስጥ ነው፡፡

የሰዎቹ ሕይወት ሊያልፍ የቻለው በከፍታ ተሰርቶ የነበረው አንድ የንግድ ድርጅት የግንብ አጥር በጎረቤት መኖሪያ ቤት ላይ ድንገት በመደርመሱ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡

በአደጋው በእንቅልፍ ላይ የነበሩ እናትና ስድስት ልጆቻቸው ሕይወት ወዲያውኑ ማለፉን ኮማንደር ተሾመ ተናግረዋል፡፡

ሕይወታቸውን ካጡ የቤተሰቡ አባላት አምስቱ ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊ ህጻናት ናቸው፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዛሬ የህዳር 10/2012 ዓ/ም በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባልት እና ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተሰባሰበ መረጃ👇
https://telegra.ph/ETH-11-20-4

(TIKVAH-ETHIOPIA)

#ድሬዳዋ #ሀረማያ #ወልዲያ #መቱ #ASTU
#መደወላቡ #ባህርዳር #ደባርቅ #ደብረታቦር

@tsegabwolde @tikvahethiopia