TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AmbassadorTayeAtskeSelassie

በተመድ (UN) የኢፌዴሪ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ፥ ኢትዮጵያን ለማዳከምና አንድነቷን ለማናጋት ከየትኛውም የውስጥም ሆነ የውጭ አካል የሚሰነዘር ትንኮሳና ጫናን በአንድነት መመከት እንደሚገባ ተናገሩ።

አምባሳደሩ ይህን ያሉት በተ.መ.ድ የኢፌዴሪ ቋሚ መልዕክተኛ ፅ/ቤት አስተባባሪነት በአሜሪካ ኒውዮርክ፣ ኮኔክትከት እንዲሁም በሌሎች ስቴቶች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በተደረገ የኦንላይን ውይይት ነው።

አምባሳደሩ ፥ ምዕራባዊያን በኢትዮጵያ ላይ እያሳዩት ያለው ያልተገባ ጣልቃ ገብነት ምን ይዘት እንዳለው በተለይ ሰሞኑን የአሜሪካ ሴኔት ያወጣውን ሪዞልሽን ምንነት፣ እንዲሁም በተመድ በፀጥታው ም/ቤት ይቀርቡ የነበሩትን ጉዳዮች በዝርዝር አስረድተዋል፡፡

በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሚቀርቡትን የተሳሳቱ አመለካከቶች እና እንቅስቃሴዎችን መመከት እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

ዳያስፖራው ባለበት አካባቢ የሚገኙ ፦ ተፅእኖ ፈጣሪ የሆኑ ግለሰቦችን፣ የፓርላማ አባላትንና የሚዲያ ተቋማትን አግኝቶ ኢትዮጵያን በተመለከተ እውነታውን የማስረዳት እና ማስገንዘብ የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን በማስገንዘብ ከዚህ አንጻር የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ከዚህም በተጨማሪ አምባሳደሩ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር ሙሌት ሂደትንና መጭው 6ኛው ሀገራዊ ምርጫን በተመለከተ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ኢፕድ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#OlusegunObasanjo ትናንት በወቅታዊ የአፍሪካ የጸጥታ ሁኔታዎች ላይ የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት ስበስባ ተቀምጦ ነበር። በዚህ ስብሰባ ላይ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ በኢትዮጵያ በመደረግ ላይ ስላሉ የሰላም ጥረቶች ገለጻ አድርገዋል፡፡ በገለጻቸውም በአዲስ አበባ ከጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ፣ ከፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ እንዲሁም ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት…
#AmbassadorTayeAtskeSelassie

ትላንት በነበረው የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት ስበስባ ላይ ኢትዮጵያን በመወከል አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ንግግር አድርገው ነበር።

አምባሳደር ታዬ በህወሓት የተፈጸመው የክህደት ስራ በእጅጉ የሚያሳዝንና ኢትዮጵያ በዚህ ወንጀለኛ ቡድን ያሳለፈችውን ጊዜ ለመርሳት የአንድ ትውልድ ጊዜ የሚፈጅ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ቡድኑ ያን ሁሉ ደም መፋሰስ እንዲፈጠር ባያደርግ ኖሮ ፖለቲካዊ እጣ ፋንታውም ሆነ ሁኔታው በውይይት መፍትሄ ያገኝ እንደነበር አምባሳደሩ ገልጸዋል፡፡

“በአፍሪካዊ እገዛዎች ካለንበት ችግር መውጣት ጥሩ መፍትሄ ነው ብለን እናምናለን፤ ወደ ፖለቲካዊ መፍትሄ የሚወስደው መንገድ ግን አልጋ በአልጋ ነው ወይም ቀላል ነው ማለት አይቻልም” ብለዋል አምባሳደር ታዬ።

መንግስት አሁን ላይ የህወሓትን መስፋፋት ማስቆም እና በቡድኑ ጥቃት እየደረሰበት ያለውን ህዝብ መታደግ ላይ ትኩረት ማድረጉንም ለምክር ቤቱ መናገራቸውን አል አይን አስነብቧል።

@tikvahethiopia