TIKVAH-ETHIOPIA
#OlusegunObasanjo ትናንት በወቅታዊ የአፍሪካ የጸጥታ ሁኔታዎች ላይ የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት ስበስባ ተቀምጦ ነበር። በዚህ ስብሰባ ላይ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ በኢትዮጵያ በመደረግ ላይ ስላሉ የሰላም ጥረቶች ገለጻ አድርገዋል፡፡ በገለጻቸውም በአዲስ አበባ ከጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ፣ ከፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ እንዲሁም ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት…
#AmbassadorTayeAtskeSelassie

ትላንት በነበረው የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት ስበስባ ላይ ኢትዮጵያን በመወከል አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ንግግር አድርገው ነበር።

አምባሳደር ታዬ በህወሓት የተፈጸመው የክህደት ስራ በእጅጉ የሚያሳዝንና ኢትዮጵያ በዚህ ወንጀለኛ ቡድን ያሳለፈችውን ጊዜ ለመርሳት የአንድ ትውልድ ጊዜ የሚፈጅ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ቡድኑ ያን ሁሉ ደም መፋሰስ እንዲፈጠር ባያደርግ ኖሮ ፖለቲካዊ እጣ ፋንታውም ሆነ ሁኔታው በውይይት መፍትሄ ያገኝ እንደነበር አምባሳደሩ ገልጸዋል፡፡

“በአፍሪካዊ እገዛዎች ካለንበት ችግር መውጣት ጥሩ መፍትሄ ነው ብለን እናምናለን፤ ወደ ፖለቲካዊ መፍትሄ የሚወስደው መንገድ ግን አልጋ በአልጋ ነው ወይም ቀላል ነው ማለት አይቻልም” ብለዋል አምባሳደር ታዬ።

መንግስት አሁን ላይ የህወሓትን መስፋፋት ማስቆም እና በቡድኑ ጥቃት እየደረሰበት ያለውን ህዝብ መታደግ ላይ ትኩረት ማድረጉንም ለምክር ቤቱ መናገራቸውን አል አይን አስነብቧል።

@tikvahethiopia