TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Mekelle የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ እና የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ አስተባባሪ የሆኑት ማርቲን ግሪፊትስ እና በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ ዛሬ የትግራይ ክልል መዲና መቐለ መግባታቸውን ሮይተርስ ከአንድ የሰብዓዊ ድጋፍ አድራጊ ምንጭ እና ጉዳዩን ከሚያውቅ አንድ ሰው መስማቱን ዘግቧል። በኢትዮጵያ የሚገኘው የUN…
#Olusegun_Obasanjo

ለሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት መፍትሄ አፈላላጊው ሰው - ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ !

በአፍሪካ ህብረት (AU) የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው ከተሾሙ በኃላ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት እንዲፈታና ሰላም እንዲወርድ የተለያዩ ስራዎችን እየሰሩ ይገኛሉ።

ኦባሳንጆ በተለያዩ ጊዜያት ከተለያዩ አካላት ጋር ውይይት ሲያደርጉ ነበር፤ ከኢትዮጵያ ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እንዲሁም ከሌሎች ኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ተወያይተዋል።

ኦባሳንጆ በሰሜን ጦርነት ጉዳይ ከአሜሪካ እና አውሮፓ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎችም ጋር ውይይት ሲያደርጉ ቆይተዋል።

የአፍሪካ ህብረት የሰሜን ኢትዮጵያን ግጭት እንዲፈታ በግጭቱ እየተሳተፉ ካሉ ኃይሎች ጋር እየተወያየ አንደሆነ መግለፁ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ መንግስት በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛው ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ፣ ይዘውት የሚመጡትን የመፍትሔ ሐሳብ እየጠበቀ ነው።

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Olusegun-Obasanjo-11-08
Audio
#Olusegun_Obasanjo

ከቀናት በፊት ትግራይ ክልል ፤ መቐለ የነበሩት እና ከዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር ምክክር ያደረጉት በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት መቋጫ እንዲያገኝ እንዲሁም ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ እየተደረገ ያለውን ጥረት በተመለከተ ከBBC Focus on Africa ጋር ያደረጉት ቃለምልልስ ከላይ በድምፅ ተያይዟል።

(3.3 MB)

@tikvahethiopia