TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፈጣሪ ማስተዋል ይስጠን!

ዛሬ አንዳንዶች ባሉበት ሆነው ተዋልደው ተከባብረው የሚኖሩ #ብሄሮችን ለማጋጨት ይሞክራሉ፤ ሰዎችን ለጥል ያነሳሳሉ፤ እርስ በእርስ እንዲገዳደሉ ይቀሰቅሳሉ፤ በፍቅር የሚኖረውን ህዝብ ይከፋፍላሉ፤ ወጣቱ ሰብዓዊነቱን እንዲረሳና ብሄሩን እንዲያስቀድም በሙሉ አቅማቸውን ቀን ማታ ይቀሰቅሳሉ፤ ህግን ስርዓትን አክብሮ የሚኖረውን ወጣት ተነሳ ግደል፣ አጥፋ እያሉ ይመክራሉ፤ ብሄር መስደብ፣ ማንቋሸሽ ባህል እንዲሆን ይሰራሉ፤ ወጣቱን ሳያውቀው ከፈጣሪው ጋር ያጋጫሉ፤ የተወሰነ ሰው ባጠፋው ወንጀል ሚሊዮኖች መሰደብ፣ መገለል እንዳለባቸው ምንም ሳይፈሩ ይናገራሉ።

እንዲህ የሚያደርጉ ሰዎች ብዙዎቹ ከራሳቸው ጋር የተጣሉ፣ ሰውነታቸውን የረሱ፣ ፈጣሪን የካዱ፣ እውቀት የራቃቸው፣ ማስተዋል ያልፈጠረባቸው ናቸው።

ዛሬ በብሄሮች መካከል እሳት ለመለኮስ የሚጥሩ ሰዎች የለኮሱት እሳት እራሳቸውን እንደሚያነድ፤ እራሳቸውን እንደሚፈጅ ፍፁም አላስተዋሉም።

የዛሬዎቹ የጥላቻ ነጋዴዎች #ነገን አሻግረው አላዩም። ይህ ህዝብ በጣም የተዋሀደ፣ እርስ በእርሱ የተዋለደ ህዝብ ነው። ዛሬ ብሄር ለይተው በለው የሚሉት ተራ ግለሰቦች ነገ የራሳቸው ወንድም እና እህቶች ካሉበት አካባቢ ወጥተው እንደሚማሩ ረስተውታል፤ ከአንዱ ከተማ ወደ ሌላው ከተማ ሄደው የሚማሩትን #ምስኪን ልጆችን ረስተዋቸዋል።

የብሄር ተቆርቋሪዎች መስለው የራሳቸውን ወንድም እና እህቶች የሚያጋድሉት ሰይጣኖች ናቸው። ወንድም እና እህቶቻቸው በሄዱበት ቦታ ሁሉ በቋንቋቸውና በባህላቸው እንዲሸማቀቁ ሊያደርጓቸው ያሰቡ እነሱ እውነትም የዚህች ሀገር ጠላቶች ናቸው።

እናተ የጥላቻ ነጋዴዎች...

◾️ነገ ምስኪን እህት ወንድሞቻችሁ የት ተመድበው እንደሚማሩ አታውቁምና ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርና አንድነትን አስተምሩ።

◾️ነገ ምንም የማያውቀው ሰራተኛ የዕለት ጉርሱን ፍለገ የትኛው ከተማ እንደሚሄድ አታውቁም ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርና አንድነትን አስተምሩ።

ሁሉም ሰላምን የሚወድ፤ ሀገሩን የሚወድ ሰው በብሄር ማካከል ጥላቻ እንዲኖር የሚሰሩትን ያግልላቸው። የማዕበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የጥላቻ ገፆች እና ግለሰቦችን #Block አድርጓቸው።

ለወጣቱ ፍቅርን እናውርሰው። ፍቅር እንደሚያሸንፍ ደጋግመን እንገረው። #ሰውነት ከሀገር፣ ከብሄር፣ ከዘር እንደሚበልጥ እንገረው።

ፈጣሪ ማስተዋልን ይስጠን!
ፀጋአብ ወልዴ-ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፈጣሪ ማስተዋል ይስጠን!

ዛሬ አንዳንዶች ባሉበት ሆነው ተዋልደው ተከባብረው የሚኖሩ #ብሄሮችን ለማጋጨት ይሞክራሉ፤ ሰዎችን ለጥል ያነሳሳሉ፤ እርስ በእርስ እንዲገዳደሉ ይቀሰቅሳሉ፤ በፍቅር የሚኖረውን ህዝብ ይከፋፍላሉ፤ ወጣቱ ሰብዓዊነቱን እንዲረሳና ብሄሩን እንዲያስቀድም በሙሉ አቅማቸውን ቀን ማታ ይቀሰቅሳሉ፤ ህግን ስርዓትን አክብሮ የሚኖረውን ወጣት ተነሳ ግደል፣ አጥፋ እያሉ ይመክራሉ፤ ብሄር መስደብ፣ ማንቋሸሽ ባህል እንዲሆን ይሰራሉ፤ ወጣቱን ሳያውቀው ከፈጣሪው ጋር ያጋጫሉ፤ የተወሰነ ሰው ባጠፋው ወንጀል ሚሊዮኖች መሰደብ፣ መገለል እንዳለባቸው ምንም ሳይፈሩ ይናገራሉ።

እንዲህ የሚያደርጉ ሰዎች ብዙዎቹ ከራሳቸው ጋር የተጣሉ፣ ሰውነታቸውን የረሱ፣ ፈጣሪን የካዱ፣ እውቀት የራቃቸው፣ ማስተዋል ያልፈጠረባቸው ናቸው።

ዛሬ በብሄሮች መካከል እሳት ለመለኮስ የሚጥሩ ሰዎች የለኮሱት እሳት እራሳቸውን እንደሚያነድ፤ እራሳቸውን እንደሚፈጅ ፍፁም አላስተዋሉም።

የዛሬዎቹ የጥላቻ ነጋዴዎች #ነገን አሻግረው አላዩም። ይህ ህዝብ በጣም የተዋሀደ፣ እርስ በእርሱ የተዋለደ ህዝብ ነው። ዛሬ ብሄር ለይተው በለው የሚሉት ተራ ግለሰቦች ነገ የራሳቸው ወንድም እና እህቶች ካሉበት አካባቢ ወጥተው እንደሚማሩ ረስተውታል፤ ከአንዱ ከተማ ወደ ሌላው ከተማ ሄደው የሚማሩትን #ምስኪን ልጆችን ረስተዋቸዋል።

የብሄር ተቆርቋሪዎች መስለው የራሳቸውን ወንድም እና እህቶች የሚያጋድሉት ሰይጣኖች ናቸው። ወንድም እና እህቶቻቸው በሄዱበት ቦታ ሁሉ በቋንቋቸውና በባህላቸው እንዲሸማቀቁ ሊያደርጓቸው ያሰቡ እነሱ እውነትም የዚህች ሀገር ጠላቶች ናቸው።

እናተ የጥላቻ ነጋዴዎች...

◾️ነገ ምስኪን እህት ወንድሞቻችሁ የት ተመድበው እንደሚማሩ አታውቁምና ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርና አንድነትን አስተምሩ።

◾️ነገ ምንም የማያውቀው ሰራተኛ የዕለት ጉርሱን ፍለገ የትኛው ከተማ እንደሚሄድ አታውቁም ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርና አንድነትን አስተምሩ።

ሁሉም ሰላምን የሚወድ፤ ሀገሩን የሚወድ ሰው በብሄር ማካከል ጥላቻ እንዲኖር የሚሰሩትን ያግልላቸው። የማዕበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የጥላቻ ገፆች እና ግለሰቦችን #Block አድርጓቸው።

ለወጣቱ ፍቅርን እናውርሰው። ፍቅር እንደሚያሸንፍ ደጋግመን እንገረው። #ሰውነት ከሀገር፣ ከብሄር፣ ከዘር እንደሚበልጥ እንገረው።

ፈጣሪ ማስተዋልን ይስጠን!
ፀጋአብ ወልዴ-ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለሁሉም የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት በሙሉ፦

▪️ጥር 1 እስከ ጥር 21-TIKVAH-ETH▪️

የሰላም፣ የፍቅር እና አንድነት ሳምንታትን በመላው ሀገሪቱ አውጀን የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን እያደረግን እንገኛለን። በፌስቡክ ላይ ተፅእኖ እንዲፈጠር እያደረጋችሁት ላለው ትልቅ ስራ ምስጋና ይገባችኃል።

#ነገ_ሰኞ ሁሉም የቤተሰባችን አባል ተከታዮቹን ስራዎች እንዲሰራ በታላቅ ትህትና እንለምናለን፦

•ሰራተኞች ወደስራ ከመግባታችሁ በፊት አንዳች መልካም ስራ እንድትሰሩ፦ በጎዳና ላይ ካሉ አቅም ከሌላቸ ወገኖች አንዱን እንኳን ቁርስ ብታበሉ። አልያም እናተ ለአእምሯቹ ደስታን የሚሰጣችሁን መልካም ስራ ብትሰሩ። ስራ ቦታ በሚኖራችሁ የእረፍት ጊዜ በሀገራችን ሰላም ማስጠበቅ ዙሪያ ከጓደኞቻችሁ ጋር ውይይት ብታደርጉ።

•የታክሲ ሹፌሮች በስራ እንቅስቃሴያችሁ ሰላም እና አንድነትን የሚያጎለብቱ ሙዚቃዎችን ለተሳፋሪዎች በመክፈት ተፅእኖ እድትፈጥሩ። ተሰብስባችሁ ምሳ በምትመግቡበት ወቅት ስለሰላም እና አንድነት እንድትመክሩ።

•ተማሪዎች በእረፍት ጊዚያችሁ ስለሰላም እንድትነጋገሩ። በቀጣይ ሳምንታት በተለያዩ መልካም ስራዎች ላይ ስለመሳተፍ ብትመክሩ። (በቡድን ሆናችሁ ደም ልገሳ፣ ህሙማንን መጠየቅ፣ የተቸገሩትን መርዳት...)

🔹ሁላችንም በፌስቡክ ብሄር ተኮር የጥላቻ መልዕክቶችን እና ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችን የሚያስተላልፉ ገለሰቦችን #Block ማድረጋችንን አጠናክረን እንቀጥላልን!!

🙏መልዕክቱ ተፈፃሚ እንደሚሆን ባለሙሉ ተስፋ ነን!! በቤተሰባችን አፍረን አናውቅም!!🙏
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#StopHateSpeech #ኢትዮጵያን_እናድን!

በማህበራዊ ሚዲያ በየቀኑ የሚታየው #የጥላቻ_ንግግር ሀገራችንን ወደለየለት ቀውስ ውስጥ እና ወደማንወጣው #አስከፊ ችግር ውስጥ ይከታታልና ሁላችንም የጥላቻ ንግግሮችን በመቃወም፤ ተሳዳቢዎችን ከተቻለ ለማረም ካልሆነም #Block በማድረግ ይህች ሀገራ እየሄደችበት ካለው የቁልቁለት ጉዞ በፍጥነት ልናስቆማት ይገባል።

#የፀረ_ጥላቻ_ህጉ_ይፍጠንልን!!
#የፌደራል_ጠቅላይ_አቃቤ_ህግ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia