TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#OROMIA : የኦሮሚያ ክልል አዲስ መንግስት ነገ ይመሰረታል። ነገ መስከረም 15 ቀን 2014 ዓ.ም የጨፌ ኦሮሚያ ጉባኤውን የሚያካሄድ ሲሆን አዲሱ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ይመሰረታል። በነገው ጉባኤ ነባር የጨፌው አባላት ይሸኛሉ፤ አዲሶቹ ደግሞ ይተካሉ ፤ አዲሱ የክልሉ ርእሰ መስተዳደር ጨምሮ አዲስ የካቢኔ አባላት ይሰየማሉ። @tikvahethiopia
#Oromia : ጨፌ ኦሮሚያ በአባ ገዳዎች ምርቃት ጉባኤውን ጀምሯል።

ዛሬ አዲሱ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ይመሰረታል።

ነባር የጨፌው አባላት ተሸኝተው በአዲሶቹ ይተካሉ ፤ አዲሱ የክልሉ ርእሰ መስተዳደር ጨምሮ አዲስ የካቢኔ አባላት ይሰየማሉ።

Photo Credit : ኤፍ ቢ ሲ

@tikvahethiopia
#Tigray #Afar #Amhara

UN OCHA በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ሁኔታው አሁንም መሻሻል እንዳላሳየ እና በአስከፊ ሁኔታ እንደቀጠለ ሪፖርት አድርጓል።

ጦርነቱ ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች መስፋፋቱን ተከትሎ በሁለቱ ክልሎች ሰብዓዊ ችግሩ እየተባባሰ ነው ብሏል።

ወደ ትግራይ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ ማስገቢያ መንገድ በሰመራ - አብአላ - መቐለ መስመር ብቻ በመሆኑ እርዳታ የማድረሱ እንቅስቃሴ በከባዱ የተገደበ መሆኑን ገልጾ የመንገዱ ፀጥታ የተረጋጋ ቢሆንም በቀጣይነት የሚፈጠረውን መተንበይ አይቻልም ብሏል።

ውጊው ወደ አፋር እና አማራ ክልሎች መስፋፋቱ በሲቪሎች ላይ ያስከተለው የምግብ ችግር እና መፈናቀል እየተባባሰ መሆኑን አሳውቋል።

ሙሉ ሪፖርት : reports.unocha.org/en/country/ethiopia/

@tikvahethiopia
#ኢሬቻ #መስቀል #የመንግስት_ምስረታ !

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከመስቀል፣ ከኢሬቻ በዓላት እና ከመንግስት ምስረታ ስነ-ስርዓት በፊትና በኋላ ሊከሰቱ የሚችሉ የፀጥታ ችግሮችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ፤ ችግር ቢከሰት እንኳን ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ጠንካራ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱን ይፋ አድርጓል።

ኮሚቴው በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮምሽነር ጀኔራል የሚመራ ሲሆን ፦
- ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ፣
- ከሀገር መከላከያ ሚኒስቴር፣
- ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት፣
-ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን
- ከኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከተውጣጡ አመራሮች የተዋቀረ ነው።

@tikvahethiopia
* Hawassa

የሲዳማ ክልል መዲና ሀዋሳ ከተማ በዓለም ለ42ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ34ኛ ጊዜ የሚከበረውን የቱሪዝም ቀን እያስተናገደች ትገኛለች።

በሲዳማ ክልል እየተካሄደ ባለው የቱሩዝም ቀን ላይ የፌዴራሉ እና የክልል ከፍተኛ ባለልስጣናት ፣ ባለድርሻ አካላት ተካፋይ እየሆኑ ነው ፤ ዛሬ መስከረም 15 ይጠናቀቃል።

በሌላ በኩል ፥ የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የሴንትራል ሆቴልን መሥራች እና ባለቤት ለወይዘሮ አማረች ዘለቀ ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ልማት ላበረከቱት የላቀ አስተዋጽዎ የዕውቅና ሰርተፍኬት ሰጥቷቸዋል።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba : ነገ የሚዘጉ መንገዶች !

መሰከረም 16/2014 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ የሚከበረው የደመራ በዓል ተጀምሮ አስከሚጠናቀቅ ከዚህ በታች የተገለፁትን መንገዶች ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ ከአ/አ ፖሊስ ማሳሰቢያ ተላፍሏል።

የሚዘጉት መንገዶች ፦

• ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አከባቢ፤
• ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያ አካባቢ፤
• ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባሻወልዴ ችሎት ወይም ፓርላማ መብራት፤
• ከፒያሣ አካባቢ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቸርችር ጎዳና ቴዎድሮስ አደባባይ፤
• ከተክለ ሀይማኖት በሜትሮሎጂ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት አካባቢ፤
• ከተክለ ሀይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ የኋላ በር አካባቢ፤
• ከሲኒማ ራስ በጎላ ሚካኤል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኢምግሬሽን የኋላ በር መግቢያ፤
• ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ፤
• ከባሻ ወልዴ ችሎት በኦርማ ጋራዥ ወደፉል ውኋ መስኪድ የሚወስደው መንገድ ንግድ ማተሚያ ቤት ፤
• ከጎፋ በቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ወደ ለገሐር አዲሱ መንገድ የመወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛው ላይ
• ከጦር ኃይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ሜክሲኮ አደባባይ
• ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ ናቸው።

ስንት ሰዓት ነው የሚዘጋው ?

ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ሁሉ ዝግ ነው።

*** ሌላው ፦
ደመራው የሚደመርበት መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ስታዲዬም እንዲሁም ከሃራምቤ ሆቴል ወደ ሴንጅ ዮሴፍ የሚያቋርጠው መስቀለኛ መንገዱ ለበዓሉ በሚደረገው ዝግጅት ምክንያት ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ዝግ የሚደረግ ይሆናል፡፡

በተጨማሪም ከሳሪስ እና ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ከባድ ተሸከርካሪዎች መንገዱ አጎና ሲኒማ ጋር የሚዘጋ ይሆናል፡፡

#ሼር ያድርጉት !

@tikvahethiopia
* ኒውዮርክ

የኢትዮጵያ ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ መከሩ።

በኒውዮርክ የተመድ ስብሰባ እየተካፈሉ የሚገኙት አቶ ደመቀ፥ ከሀገራት ባለስልጣናት እና ከተቋማት አመራሮች ጋር የሚያደርጉት የጎንዮሽ ምክክር የቀጠለ ሲሆን ትላንት ከአንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር መክረዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ይፋ ባደረገው መረጃ ዋና ፀሐፊው እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ውስጣዊ ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።

ዋና ፀሐፊው ወደ ሰላም የሚወስዱ እርምጃዎች እንዲኖሩ በድጋሚ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን የሰብአዊ ተደራሽነትን ይበልጥ ማመቻቸት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተመለከተ ዋና ፀሐፊው ውይይቱን እንደገና ማስጀመርን አስፈላጊ እንደሆነ አስገንዝበው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለአፍሪካ ህብረት የማሸማገል ጥረቶች ድጋፉን እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል።

@tikvahethiopia
#ደሴ

የኢትዮጵያ 🇪🇹 ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ደሴ ገቡ።

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ደሴ የገቡት ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በደሴ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ወገኖችን ለመጎብኘት ነው።

የደሴ ከንቲባ አቶ አበበ ገ/መስቀል ፥ ሽብርተኛ ድርጅት ተብሎ የተፈረጀው ህወሓት በአማራ ክልል በከፈተው ጦርነት ተፈናቅለው ደሴ የሚገኙ 300 ሺህ ዜጎች እንዳሉ አሳውቀዋል።

የፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጉብኝትም ተፈናቃዮች ያሉበትን ወቅታዊ ሁኔታ በትክክል ለመረዳት እንደሆነ ገልፀዋል።

ከጉብኝታቸው በኋላም ለተፈናቃዮች ድጋፍ ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከንቲባው አስታውቀዋል።

Photo Credit : ENA

@tikvahethiopia
#Tigray : ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ (አይሲአርሲ) በትግራይ ክልል በሆስፒታሎች እና ሌሎች የጤና ተቋማት ውስጥ ለሚገኙ 15,000 የጤና ሰራተኞች እና ሕሙማን ለ2 ወራት የሚሆን የመሠረታዊ የምግብ አቅርቦቶችን ማሰራጨት መጀመሩን ዛሬ አስታውቋል።

አይሲአርሲ ፥ "ሕሙማን የሕክምና አገልግሎት ማግኘት እንዲቀጥሉ የሕክምና ሠራተኞችን መደገፍ አስፈላጊ ነው" ብሏል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Oromia : ጨፌ ኦሮሚያ በአባ ገዳዎች ምርቃት ጉባኤውን ጀምሯል። ዛሬ አዲሱ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ይመሰረታል። ነባር የጨፌው አባላት ተሸኝተው በአዲሶቹ ይተካሉ ፤ አዲሱ የክልሉ ርእሰ መስተዳደር ጨምሮ አዲስ የካቢኔ አባላት ይሰየማሉ። Photo Credit : ኤፍ ቢ ሲ @tikvahethiopia
#Update

አቶ ሽመልስ አብዲሳ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ።

የጨፌ ኦሮሚያ ምክር ቤት አቶ ሽመልስ አብዲሳን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አድርጎ ሾሟል።

አቶ ሽመልስ የክልል ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ዛሬ ስራ በጀመረው በአዲሱ የጨፌ አባላት ነው፡፡

ፕሬዚዳንቱ በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል፡፡

Credit : ENA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update አቶ ሽመልስ አብዲሳ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ። የጨፌ ኦሮሚያ ምክር ቤት አቶ ሽመልስ አብዲሳን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አድርጎ ሾሟል። አቶ ሽመልስ የክልል ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ዛሬ ስራ በጀመረው በአዲሱ የጨፌ አባላት ነው፡፡ ፕሬዚዳንቱ በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል፡፡ Credit : ENA @tikvahethiopia
#Oromia

ጨፌ ኦሮሚያ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ያቀረቧቸውን ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የክልል ካቢኔ አባላት ሹመት አጽድቋል፡፡

በዚህም :-

1.አቶ አወሉ አብዲ - የክልሉ ምክትል ፕሬዘዳንት
2. አቶ ፍቃዱ ተሰማ - በጨፌ የመንግስት ተጠሪ
3. ዶክተር ግርማ አመንቴ - በምክትል ፕሬዘዳንት ማዕረግ የክልሉ መንግስት የልማት ድርጅቶች ክላስተር አስተባባሪ
4. ወይዘሮ መስከረም ደበበ - በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ
5. አቶ አዲሱ አረጋ - በምክትል ፕሬዘዳንት ማዕረግ የከተማ ክላስተር አስተባባሪ
6. አቶ አብዱራህማን አብደላ - በምክትል ፕሬዘዳንት ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪ
7. አቶ አብዱልሃኪም ሙሉ - በምክትል ፕሬዘዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ
8. አቶ አበራ ወርቁ - የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ሃላፊ
9. ወይዘሮ አዱኛ አህመድ - የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዋና አቃቢ
10. አቶ ሻፊ ሁሴን - የኦሮሚያ አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ
11. ኢንጂነር ሚሊዮን በቀለ - የኦሮሚያ ውሃ መስኖና ኢነርጂ ቢሮ ሃላፊ
12. አቶ ቶለሳ ገደፋ - የኦሮሚያ የገንዘብና ኢኮኖሚያዊ ልማት ቢሮ ሃላፊ
13. አቶ አበራ ቡኖ - የክልሉ ሚሊሺያ ቢሮ ሃላፊ
14. ወይዘሮ ሳሚያ አብደላ - የስፖርት ኮሚሽን
15. ጉዮ ገልገሎ - የቤቶችና ከተማ ልማት ቢሮ ሃላፊ
16. አቶ አህመድ ኢድሪስ - የስራ ዕድል ፈጠራ ቢሮ ሃላፊ
17. ወይዘሮ ሀዋ - አህመድ የንግድ ቢሮ ሃላፊ
18. ዶክተር መንግስቱ በቀለ - የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ሃላፊ
19. ወይዘሮ ሰዓዳ ዑስማን - የኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝምቢሮ ሃላፊ .
20. አቶ ጉታ ላቾሬ - የመሬት ቢሮ ሃላፊ .
21. ወይዘሮ መሰረት አሰፋ - የህብረት ስራ ማስፋፊያ ኤጄንሲ ሃላፊ
22. ዶክተር ተሾመ አዱኛ - የኢንቬስመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ
23. ኢንጂነር ሄለን ታምሩ - የኦሮሚያ መንገዶችና ሎጄስቲክ ቢሮ ሃላፊ
24. ዶክተር ቶላ በሪሶ - የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ
25. ዶክተር ኢንጂነር መሳይ ዳንኤል - የኦሮሚያ መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ ሃላፊ
26. ወይዘሮ ጀሚላ ሲንቢሩ - የኦሮሚያ ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ
27. አቶ አራርሶ ቢቂላ (የኦሮሞ ነፃነት ግንባር የስራ አስፈፃሚ አባል) - የኦሮሚያ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ
28. አቶ ሃይሉ አዱኛ - የኦሮሚያ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ
29. አቶ ሁሴን ፈይሶ - የፐብልክ ሰርቪስ ቢሮ ሃላፊ
30. ዶክተር አብዱልአዚዝ ዳውድ - የኦሮሚያ ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር
31. አቶ ጌቱ ወዬሳ - የፕሬዝዳንት ቢሮ ሃላፊ .
32. ወይዘሮ ኮኮቤ ዲዳ - የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች ቢሮ ሃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

ሹመቱ የተሰጠው ተሿሚዎቹ ባላቸው የትምህርት ዝግጅት ፣ በአመራር ሰጪነት ፣ በፖለቲካ ቁርጠኝነትና ብቃት መሆኑ ተገልጿል።

Credit : ENA

@tikvahethiopia
#Somalia : ዛሬ በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሹ በፕሬዚዳንቱ መኖሪያ አቅራቢያ በሚገኝ መስቀለኛ መንገድ ላይ በአንድ የአጥፍቶ ጠፊ የመኪና ፍንዳታ 8 ሰዎች መገደላቸውን እና የተጎዱ ሰዎች ስለመኖራቸው AFP ዘግቧል።

የተጎጂዎች ቁጥር ከዚህም ከፍ ሊል እንደሚችል ተነግሯል።

የሱማሊያ ፖሊስ ከጥቃቱ ጀርባ አል-ሸባብ እንዳለ ገልጿል።

የመንግስት ቃል አቀባይ የሆኑት መሐመድ ኢብራሂም ሞዓሊሙ በበኩላቸው ከተገደሉት መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር መሐመድ ሁሴን ሮቤል ጽሕፈት ቤት የሴቶችና የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች አማካሪ ሂባቅ አቡካር ይገኙበታል ብለዋል።

@tikvahethiopia
#Amhara : "275 ሺህ ሄክታር መሬት አልታረሰም ፥ በዘር የተሸፈነ አንድ ሚሊዮን ሄክታር በእንክብካቤ እጦት ተበላሽቶ ቀርቷል" - ግብርና ሚኒስቴር

ግብርና ሚኒስቴር ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው ህወሓት በአማራ ክልል በፈፀመው ወረራ 275 ሺህ ሄክታር መሬት ሳይታረስ መቅረቱን እና በዘር የተሸፈነ አንድ ሚሊዮን ሄክታር በእንክብካቤ እጦት ተበላሽቶ እንደቀረ አስታወቀ።

የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሳኒ ረዲ ለኢፕድ በሰጡት ቃል ፤ በሰሜን ወሎ፣ ዋግህምራ፣ ሰሜን ጎንደር ብቻ ሁለት መቶ 75 ሺህ ሄክታር መሬት ሳይታረስ መቅረቱን አመልክተዋል።

በእነዚህ አካባቢዎች አንድ (1) ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር የተሸፈነ እንክብካቤ ሳይደረግለት በእንስሳት እንዲበላ በመደረጉ የተዘራው ሰብል መበላሸቱን ገልፀዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው ህወሓት በግብርናው ዘርፍ ያደረሰው የጉዳት መጠን ጠቅለል ያለ ጥናት እየተጠና ነው ብለዋል።

"ሰላም በሆኑ ሌሎችም የሀገሪቱ አካባቢዎች ሚሊሻው እና ልዩ ሃይሎች በመዝመታቸው፣ ወላጆቻቸውን በግብርና እርሻ ያግዙ የነበሩ ወጣቶች ህወሓትን ለመመከት ግንባር ላይ በመሰለፋቸው ምክንያት የሚታጣው ምርት በባለሙያዎች እየተጠና ነው" ሲሉም አቶ ሳኒ ረዲ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ሀገር መከላከያ ሰራዊት ትላንት ካማሽ ገብቷል።

የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ካማሽ ከተማ ሙሉ ለሙሉ መግባቱን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ም/ኮሚሽነር ኢንስፔክተር ምስጋናው እንጂፈታ አሳውቀዋል።

የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ካማሽ መግባቱን ተከትሎ በአካባቢው ይሰማ የነበረው የተኩስ ልውውጥ መቆሙንና በአካባቢው የነበረውን ታጣቂ ኃይልም ማፈግፈጉን ገልፀዋል።

ኢስፔክተር ምስጋናው እንጅፈታ ለ#ቪኦኤ በሰጡት ቃል ፥ በካማሺ ዞን የሚንቀሳቀሱ እራሳቸው የቤንሻንጉል ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ቤህነን) የሚባሉ ታጣቂዎች የዞኑን በርካታ ቦታዎች ተቆጣጥረው መቆየታቸውን አስረድተዋል።

"የቤህነን ታጣቂ ከኦነግ ሸኔ ጋር ቅንጅት አላቸው፣ ከእነሱ ጋር እየተጋገዙ ነው ይህን የሚያደርጉት፣ በዞኑ 5 ወረዳ ነው ያለው ከዞን እና የወረዳ ማዕከሎች ውጪ አንድም ቀበሌ በመንግስት እጅ ላይ የለም" ሲሉ አክለዋል።

ከመንግስት እጅ በወጡ ቦታዎች በፖለቲካው እንቅስቃሴ የለም፣ ሙሉ በሙሉ ግንኙነቶችም ተቋርጠዋል በዚህ ምክንያት በዞኑ ሰብዓዊ ቀውስ ተፈጥሯል ሲሉ ገልፀዋል።

ኢንስፔክተር ምስጋናው ፥ ባለው የፀጥታ ኃይል ውስንነት የተነሳ ችግር አለባቸው ተብሎ በጥናት የተለዩ ቦታዎች በመግባት ህግ ማስከበር እንዳልተቻለ አመልክተው ፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ ህብረተሰቡ በተጎሳቆለ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለው ብለዋል።

ከመንግስት ቁጥጥር ውጭ በሆኑ ቦታዎች ያልተዘረፈ ከብት የለም፤ ያልተዘረፈ ንብረት የለም፣ የከፋ ሰብዓዊ ቀውስ ነው ያለው ፤ ህብረተሰቡ በረሃብ እየተጎዳ ነው፣ መድሃኒት የለም ተዘርፏል፣ ጤና ኬላዎች ግብአት አይገባላቸውም ግንኙነት የለም ተቋርጧል በዚህም ህብረተሰቡ ከፍተኛ ስቃይ ላይ መሆኑን አመልክተዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/Benishangul-Gumuz-09-25

@tikvahethiopia
#AddisAbaba - ማስታወሻ !

ዛሬ በመስቀል አደባባይ የሚከበረው የደመራ በዓል ተጀምሮ አስከሚጠናቀቅ ከዚህ በታች የተገለፁትን መንገዶች ዝግ ይሆናሉ።

የሚዘጉት መንገዶች ፦

• ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አከባቢ፤
• ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያ አካባቢ፤
• ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባሻወልዴ ችሎት ወይም ፓርላማ መብራት፤
• ከፒያሣ አካባቢ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቸርችር ጎዳና ቴዎድሮስ አደባባይ፤
• ከተክለ ሀይማኖት በሜትሮሎጂ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት አካባቢ፤
• ከተክለ ሀይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ የኋላ በር አካባቢ፤
• ከሲኒማ ራስ በጎላ ሚካኤል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኢምግሬሽን የኋላ በር መግቢያ፤
• ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ፤
• ከባሻ ወልዴ ችሎት በኦርማ ጋራዥ ወደፉል ውኋ መስኪድ የሚወስደው መንገድ ንግድ ማተሚያ ቤት ፤
• ከጎፋ በቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ወደ ለገሐር አዲሱ መንገድ የመወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛው ላይ
• ከጦር ኃይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ሜክሲኮ አደባባይ
• ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ ናቸው።

ስንት ሰዓት ነው የሚዘጋው ?

ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ሁሉ ዝግ ነው።

*** ሌላው ፦
ደመራው የሚደመርበት መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ስታዲዬም እንዲሁም ከሃራምቤ ሆቴል ወደ ሴንጅ ዮሴፍ የሚያቋርጠው መስቀለኛ መንገዱ ለበዓሉ በሚደረገው ዝግጅት ምክንያት ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ዝግ የሚደረግ ይሆናል፡፡

በተጨማሪም ከሳሪስ እና ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ከባድ ተሸከርካሪዎች መንገዱ አጎና ሲኒማ ጋር የሚዘጋ ይሆናል፡፡

#ሼር ያድርጉት !

@tikvahethiopia