#ደሴ

የኢትዮጵያ 🇪🇹 ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ደሴ ገቡ።

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ደሴ የገቡት ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በደሴ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ወገኖችን ለመጎብኘት ነው።

የደሴ ከንቲባ አቶ አበበ ገ/መስቀል ፥ ሽብርተኛ ድርጅት ተብሎ የተፈረጀው ህወሓት በአማራ ክልል በከፈተው ጦርነት ተፈናቅለው ደሴ የሚገኙ 300 ሺህ ዜጎች እንዳሉ አሳውቀዋል።

የፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጉብኝትም ተፈናቃዮች ያሉበትን ወቅታዊ ሁኔታ በትክክል ለመረዳት እንደሆነ ገልፀዋል።

ከጉብኝታቸው በኋላም ለተፈናቃዮች ድጋፍ ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከንቲባው አስታውቀዋል።

Photo Credit : ENA

@tikvahethiopia