TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Ethiopia

በትላንትናው ዕለት 79 የሀገራችን ዜጎች ከየመን፣ ሰንዓ ወደ አገራቸው ኢትዮጵያ ተመልሰዋል።

በየመን የሚገኙ የኢትዮጵያን ዜጎችን ወደ አገራችው ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ያስታወሰው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትላንት 79 ዜጎችን ከሰንዓ በማስወጣት ወደ አገራቸው እንደሚለሱ መድረጉን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
157 ሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ መኪናዎች መቐለ ገቡ።

ትናንት ሐምሌ 27 ቀን 2013 ዓ.ም. 157 ሰብዓዊ ዕርዳታ የያዙ የጭነት መኪናዎች መቐለ የወቅታዊ መረጃ ማጣሪያ ገፅ አሳውቋል።

መኪናዎቹ የምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ አስፈላጊ መገልገያዎችን የያዙ መሆናቸው ተገልጿል።

ድጋፉ ከዓለም የምግብ ድርጅት (WFP) ፣ እንደ ዩኒሴፍ (UNICEF) እና ዩ.ኤን .ኤፍ.ፒ.ኤ (UNFPA) ካሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅቶች (UN) ፣ እንዲሁም ምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆነ ድጋፍን ለማቅረብ ከሚንቀሳቀሱ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የተገኘ ነው ተብሏል።

Photo : File

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
2 ዓለም አቀፍ የእርዳታ ቡድኖች የኢትዮጵያ መንግስት በከፊል / በሙሉ ስራቸውን እንዳቋረጠባቸው እና የስራ ፍቃዳቸውን እንደነጠቃቸው ትላንት አሳወቁ። ቡድኖቹ የDoctors Without Borders - MSF (የደች ቅርንጫፍ) እና Norwegian Refugee Council (NRC) ሲሆኑ ሐምሌ 23/2013 ዓ/ም ጀምሮ መንግስት ስራ እንዳያከናውኑ እንዳገዳቸው ገልፀዋል። ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግስት…
#Update

1ኛ MSF HOLLAND 2ኛ NORWEGIAN REFUGEE COUNCIL እና 3ኛ AL MAKTOUME FOUNDETION የተባሉ የውጭ ድርጅቶች የኢፌድሪ የሲቪክ ማህበራት ድርጅቶች ኤጀንሲ በሰጣቸው ፍቃድ በህጋዊነት በተለያዩ የሰብዓዊ ስራዎች ተሰማርተው እየሰሩ የቆዩ ድርጅቶች ሲሆኑ የድርጅቶቹን እንቅስቃሴ በተመለከተ ፍቃድ ሰጪው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ኤጀንሲ በሚያደርገው ክትትል መሰረት ድርጅቶቹ ከተቋቋሙለት አላማ ውጭ በመንቀሳቀስ፤

- አንደኛ- 1ኛ እና 2ኛ የተጠቁት ድርጂቶች የተለያዩ ሃሰተኛ መረጃዎችን በማህበራዊ ሚዲያ እና በሌሎች ዘዴዎች ሲያሰራጩ በመገኘታቸው፣

-ሁለተኛ - 3ቱም ድርጅቶች ስልጣን በተሰጠው አካል የስራ ፍቃድ ያልተሰጣቸውን የውጭ ሃር ዜጎች ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባት ከስድስት ወር በላይ ቀጥረው ሲያሰሩ በመገኘታቸው፤

- ሶስተኛ- 1ኛ የተቀመጠው ድርጅት ስልጣን በተሰጠው አካል ፍቃድ ያልተሰጣቸው የሳተላይት የሬድዬ መገናኛ መሳሪያውችን ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባ የድርጂቱ ሰራተኞች አፍራሽ ለሆኑ አላማ ሲጠቀሙበት እና ይዘው ሲንቀሳቀሱ በጸጥታ አካላት ቀጥጥር ስር በመዋላቸው

- አራተኛ- 3ኛ የተጠቀሰው ድርጅት የትምህርት ሚንስቴር የኮቪድ-19 ፕሮቶኮልን ባለማክበር ፣ የበጀት አጠቃቀም ግልጽነት የጎደለውና በትምህርት ቤቱ ስም የሚመጣን በጀት ከአላማው ውጭ እየተጠቀመ በመሆኑ እንዲሁም በሰራተኞች አስተዳደር ችግር የታየበት በመሆኑ ምክንያት፤

ድርጅቶቹ ከተቋቋሙት አላማ ውጭና የሃገርን ጥቅም በሚጻረር መልኩ ሲንቀሳቀሱ በመገኘታቸው እንዲታረሙ በተደጋጋሚ ከድርጅቶቹ ሃላፊዎች ጋር ውይይት ቢደረግም ሊያስተካክሉ ስላልቻሉ አጠቃላይ ምርመራ ተደርጎ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ አጠቃላይ የድርጅቶቹ እንቅስቃሴ ለ3 ወራት #ታግዷል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tokyo2020 በ1,500 ሜትር ለፍፃሜ ለማለፍ በተካሄደው ውድድር በመጀመሪያው ምድብ የተወዳደረችው ፍሬወይኒ ሀይሉ 3:57.54 በሆነ ሰዓት 2ኛ ደረጃን በመያዝ ለ ፍፃሜው አልፋለች። @tikvahethsport
#ምድብ2

በ1500 ሜትር ለፍፃሜ ለማለፍ በተካሄደ በ2ኛው ምድብ ውድድር ኢትዮጵያን ወክላ የተወዳደረችው #ለምለም_ሀይሉ ዘጠነኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች።

ለምለም ወደ ቀጣዪ ዙር ማለፍ ሳትችል ቀርታለች።

በዚህ ምድብ በተደረገው ውድድር ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ኔዘርላንድን ወክላ የተሳተፈችው #ሲፋን_ሀሰን ቀዳሚውን ደረጃ በመያዝ ለፍፃሜው አልፋለች።

የ1500 ሜትር ፍፃሜ ውድድር የፊታችን አርብ ከቀኑ 9:50 ጀምሮ ይደረጋል።

@tikvahethsport
አንዲት የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከባሮ ድልድይ ዘላ ህይወቷ አለፈ።

ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ የተቋሙ ተማሪ የነበረች ወጣት ባልታወቀ ምክንያት ከባሮ ድልድይ በመዝለል ህይወቷ ማለፉን ገልጿል።

የሎጆስቲክስ ትምህርት ክፍል ሶስተኛ ዓመት ተማሪ የነበረችው ተማሪ ቀመሪያ ኃይሉ ሐምሌ 24/2013 ዓ.ም ከቀኑ 12:00 ሰዓት አካባቢ ከባሮ ድልድይ ወደ ወንዙ በመዝለል ህይወቷ ማለፉ ነው የተገለፀው።

የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ፣ የክልሉ ፖሊስ፣ የአቦል ወረዳ አመራሮችና ነዋሪዎች ያደረጉትን ፍለጋ ተከትሎ የሟቿ አስክሬን በአቦል ወረዳ "ፒኝኬው ቀበሌ" መገኘቱን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

More: @tikvahuniversity
#Tokyo 🇪🇹

በ 3 ሺህ ሜትር መሰናክል በተካሄደ የ ፍፃሜ ውድድር ዩጋንዳዊቷ ቼሙታይ የ ወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ሆናለች ።

ኢትዮጵያዊቷ መቅደስ አበበ ውድድሯን በ አራተኛነት እንዲሁም ዘርፌ ወንድማገኝ በ ስምንተኛነት ውድድራቸውን አጠናቀዋል ።

አትሌት ዘርፌ ወንድማገኝ የገባችበት 9:16.41 ሰዓት የ ግሏ ምርጥ ሰዓት ሆኖ ተመዝግቧል ።

ሁለቱም በ ርቀቱ የተሳተፉት አትሌቶቻችን መቅደስ አበበ እና ዘርፌ ወንድማገኝ የመጀመሪያ የ ኦሎምፒክ ተሳትፏቸው ነበር ።

@tikvahethsport
ኤርትራውያን ስደተኞችን ሰላም ወዳለበት የማዘዋወር ስራ...

የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን (UNHCR) ስደተኞቹን የተሻለ ሰላም ወዳለባቸው አካባቢዎች ለማዘዋወር የአደጋ ግዜ እቅድ ማዘጋጀቱን አሳውቋል።

ድርጅቱ ይህን ያሳወቀው ለቢቢሲ በሰጠው ቃል ነው።

በማይጸብሪ በሚገኙት ማይ አይኒ እና አዲ ሃሩሽ መጠለያ ጣቢያዎች ያሉ ስደተኞችን በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን፣ ዳባት ከተማ እየተገነባ ወደሚገኘው አዲስ ጣቢያ እንደሚዘዋወሩ ተገልጿል።

በ91 ሄክታር መሬት ላይ የሚገነባው የመጠለያ ካምፕ 25 ሺ ስደተኞችን ለማስተናገድ አቅም አለው።

የስደተኞችን ደህንነት በተመለከተ የተጠየቁት የUNHCR የኢትዮጵያ ቃል አቀባይ ነቨን ከርቨንኮቪክ ስደተኞቹ "የሰብዓዊ እርዳታ ተቋርጦባቸው በማያቋርጥ ፍርሃት ውስጥ እየኖሩ ይገኛሉ" ብለዋል።

ከማይ አይኒ ካምፕ ለUNHCR በቅርቡ በደረሰ ሪፖርት ቢያንስ 1 ስደተኛ በካምፑ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች መገደሉን ያመለከተ ሲሆን ሐምሌ 14 ሌላ ስደተኛ መገደሉን የሚያመላክት ሌላ ሪፖርት ለUNHCR ደርሶ እንደነበር አሳውቀዋል።

የድርጅቱ ሠራተኞች ላለፉት 3 ሳምንታት ከስደተኞች መጠለያ ካምፖች ጋር ያላቸው ግንኙነት ሙሉ በሙሉ መቋረጡን አስረድተዋል።

"ወጥመድ ውስጥ የገቡ ስደተኞች አስቸኳይ የሕይወት አድን እርዳታ ያስፈልጋቸዋል" በማለት ስለ ስደተኞቹ ገልጸዋል።

ወደ 24,000 የሚሆኑ ኤርትራዊያን ስደተኞች ማስፈራራትና እንግልት እየገጠማቸው እንደሆነም ገልጸዋል።

More : telegra.ph/BBC-08-04

Source : BBC

@tikvahethiopia
#ItsMyDam🇪🇹

ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ለማድረግ የሚያገለግል የሞባይል መተግበሪያ ይፋ ተደረገ።

ይፋ የተደረገው መተግበሪያ" Its My Dam" የተሠኘ ስያሜ ያለው ሲሆን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል ነው ይፋ የተደረገው።

የገቢ ማሰባሰቢያ መተግበሪያውን ወደ ሥራ ለማስገባት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚደንት አቶ አቤ ሳኖ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

መተግበሪያዉ ከ1 ዶላር ጀምሮ እስከ 10 ሺህ ዶላር ድረስ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል ነው።

Photo Credit : EEP

@tikvahethiopia
#USA : አሜሪካ 1,210,550 ዶዝ የጆንሰን እና ጆንሰን ኮቪድ-19 ክትባት ለኢትዮጵያ ለግሳለች።

በአዲስ አበባ ከሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በተገኘው መረጃ ልገሳው ከዚህ ቀደም ከተለገሱት 453,600 ክትባቶች ተጨማሪ ነው።

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ ፥ “ልገሳው የኢትዮጵያ ህዝቦች የኮቪድ -19ን ወረርሽኝ ለመከላከል የሚያደርጉትን ትግል ያግዛል" ብለዋል።

በተጨማሪም፤ "የኮቪድ -19 ክትባቶችን ለኢትዮጵያ በማድረስ የህይወት አድን ስራ ላይ በመሳተፋችን ክብር ይሰማናል" ያሉ ሲሆን የኢትዮጵያ የቅርብ የጤና አጋር እንደመሆናችን ሕይወትን ለማዳን እና ወረርሽኙን ለማጥፋት ቁርጠኛ ነን” ሲሉ ተናግረዋል።

ከክትባቱ ጋር በተያያዘ የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በትዊተር ገፃቸው የአሜሪካን ድጋፍ እንደሚያደንቁ ገልፀው ፤ ኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመዋጋት እና የኮቪድ-19 ክትባትን ተደራሽ ለማድረግ የምታደርገውን ጥረት ትቀጥላለች ብለዋል።

ዶ/ር ሊያ COVAX፣ UNICEF ፣ CDC Africaን ድጋፉን ስለመቻቹና ስለደገፉ አመስግነዋል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት 5,916 የኮቪድ-19 ላብራቶሪ ምርመራ ያከናወነች ሲሆን 511 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተግኝተዋል፤ ስምንት ሰው ህይወቱ ያለፈ ሲሆን 123 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።

@tikvahethiopia
ባለፉት ቀናት በሱዳን ጉብኝት ያደረጉት የUSAID ኃላፊ ሳማንታ ፖውር ኢትዮጵያ ይገኛሉ።

ፖወር ወደኢትዮጵያ መግባታቸው በይፋ በሚዲያ ሳይታወቅ እና እሳቸው ሆነ ተቋማቸው ሳያሳውቁ ነው ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ሆነው መግለጫ የሰጡት።

ለመሆኑ በመግለጫቸው ምን አሉ ?

- ከሰላም ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል እና ከዶ/ር ሊያ ታደሰ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

- በትግራይ ክልል ካለው ግጭት ጋር በተያያዘ የሰላም አማራጮች መታየት እንዳለባቸው ፣ ግጭት መቆም እንዳለበት ፣ ሁሉም ተፋላሚ ኃይሎች ወደ ድርድር መምጣት እንዳለባቸው ከሰላም ሚኒስትር ጋር መነጋገራቸውን ገልፀዋል።

- የትግራይ ያለው የውጥ ግጭት ሊፈታ የሚችለው በሰላማዊ አማራጭ ብቻ መሆን እንዳለበት መነጋገራቸውን አሳውቀዋል።

- የአሜሪካ መንግስት ይሁን ሌሎች አካላት የሚሰጡት መገልጿቸው ሃሳቦች መፍትሄ ከማፈላለግ ሃሳብ ጋር የተያያዙ ናቸው ብለዋል።

- ለውጣዊ ግጭት ወታደራዊ አማራጭ መፍትሄ እንደማይሆን፣ ሁሉም አካላት ግጭቱን አስቸኳይ አቁመው ውይይት መጀመር እንዳለባቸው ተናግረዋል።

- ግጭቱ እየሰፋ መሄዱን ተናግረው ሰላማዊ መፍትሄ ካልተበጀለት ይበልጥ እየተስፋፋ በርካታ ሰዎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ ተናግረዋል።

- በአፋር እና አማራ ክልል ህወሃት በፈፀመው ጥቃት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀላቸው አንስተዋል።

- ዓለም አቀፍ ህጎች መከበር እንዳለባቸው፣ ንፁሃን ለአላስፈላጊ ጉዳት መዳረግ እንደሌለባቸው ፣ የሰብዓዊ ድጋፍ ሰራተኞች ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ተናግረዋል።

- ከሰሞኑ የአሜሪካ መንግስት ይፋ ካደረገው 149 ሚሊዮን ዶላር የሰብዓዊ ድጋፍ በተጨማሪ በዛሬው ዕለት 45 ሚሊዮን ተጨማሪ በጀት ለኮቪድ ወረርሽኝ ለመከላከል ለሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል ለኢትዮጵያ ይፋ አድርገዋል።

#VOA

@tikvahethiopia
ሳማንታ ፖወር በኢትዮጵያ ማንን አገኙ ?

የUSAID ኃላፊ ሳምንታ ፓወር ሱዳን እንደነበሩ ቢታወቅም በይፋ በሚዲያ ሳይገለፅ ፣ በመንግስትም የተባለ ነገር ሳይኖር እንዲሁም እሳቸው ሆነ ተቋማቸው USAID ያሉት ነገር ሳይሆር ዛሬ አዲስ አበባ ሆነው መግለጫ ሰጥተዋል።

ትላንት ነው ኢትዮጵያ የገቡት።

ፓወር በኢትዮጵያ ቆያታቸው ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ተገናኝተዋል።

እሳቸው እንዳሳወቁት ከጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ እና ከሰላም ሚኒስትር ሙፈርያት ካሚል ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።

ሳማንታ ፓወር ዛሬ ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ለማግኘት እና ለመወያየት ጥረት ቢያደርጉም አልተሳካላቸውም፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከከተማ ውጭ እንደሆኑ እንደተነገራቸው ገልፀዋል።

ሳማንት አሁን ላይ ቆይታቸውን ያጠናቀቁ ይመስላል አብረዋቸው ያሉ ባልደረቦቻቸው እንደገለፁት ዛሬ ለሊት ወደአሜሪካ ይበራሉ።

ሳማንታ ፓወር የተለያዩ አሉባልታዎች ሊወሩ እንደሚችል ያነሱ ሲሆን የተሳሳቱ መረጃዎች በሚሰራጭበት ጊዜ መወያያት ብቸኛው መፍትሄ ነው ብለዋል።

ሳማንታ ፓወር ከአሜሪካ በተነሱበት ወቅት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይን ጨምሮ ከሌሎችም ባለስልጣናት ጋር እንደሚነጋገሩ አስበው ነበር የመጡት።

የጉብኝታቸው ዋነኛ አላማ በትግራይ ክልል ረሃብን ለመከላከል የሰብዓዊ እርዳታ ተደራሽነት ከፍ እንዲል ለማድረግ በመንግስት ላይ ጫና ለማሳደር ነበር።

የመረጃ ባለቤት ፦ ጋዜጠኛ ኬኒዲ አባተ

@tikvahethiopia
ማርቲን ግሪፊትድ በትግራይ ቆይታቸው ምን ታዘቡ ?

(በቢቢሲ)

አዲሱ የተባበሩት መንግሥታት የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ አስተባባሪ ማርቲን ግሪፊትስ በትግራይ ክልል ለሁለት ቀናት ጉብኝት አድርገዋል። ግሪፊትስ በትግራይ ስለተማለከቱት ሁኔታ ቢሯቸው መግለጫ አውጥቷል።

ግሪፊትስ በትግራይ ቆይታቸው ፦

- በትግራይ ክልል የተመለከቱት የጥፋት መጠን ልባቸውን እንደሰበረው ገልፀዋል። አስከፊ የሰብዓዊ ሁኔታ መመልከታቸውን ተናግረዋል።

- በጦርነቱ ህይወታቸው ከተመሰቃቀለ ዜጎች ጋር መወያየታቸው ገልፀዋል።

- በጦርነቱ ምክንያት የነበራቸውን ሁሉ ያጡ ሰዎች ማግኘታቸውን፣ መኖሪያቸውንና የእርሻ መሬታቸውን እንዲሁም መንደሮቻቸውንና ከተማቸውን ጥለው የተሰደዱ፣ በሃውዜን ቤታቸው ተቃጥሎ ሰብላቸው የተዘረፈ ቤተሰብ ማግኘታቸውን፣ እስካሁን ድረስ መጠለያም ሆነ ምግብ የሌላቸው ቤተሰቦችን ማግኘታቸው ገልፀዋል፤ "ይህን ማየትም ሆነ የጥፋቱን መጠን መመልከት ልብ ይሰብራል" ብለዋል።

- በትግራይ ጉብኝታቸው ወቅት አሰቃቂ ጥቃት የደረሰባቸውን ግለሰቦችን አነጋግረዋል ፤ የዜጎች መሰረታዊ ልማት የሆኑ እንደ ትምህርት ቤት፣ ሆስፒታልና ውሃ አገልግሎቶች ስልታዊ በሆነ መንገድ እንዴት እንደወደሙም በአይናቸው መመልከታቸውን ገልፀዋል።

- በመቐለ እና ፍሬወይኒ ውስጥ ለሳምንታት ያህል የተደፈሩትን ጨምሮ አሰቃቂ የሚባሉ ወሲባዊ ጥቃቶች የተፈፀመባቸውን ሴቶችን ማናገራቸው ገልፀዋል። እነዚህ ሴቶች ሁለንተናዊና ሁሉን አቀፍ አገልግሎቶች ቢሹም "አብዛኛው የጤና ማዕከላት አገልግሎት እየሰጡ አይደለም ብለዋል።

- የመገናኛ ተደራሽነት፣ ነዳጅና እና የባንክን የመሳሰሉ መሰረታዊ አገልግሎቶች መቋረጥ አስከፊውን ሁኔታ እያባባሰው መሆኑን ተናግረዋል።

https://telegra.ph/BBC-08-05

@tikvahethiopia
ግሪፍቲስ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ማንን አገኙ ?

የተባበሩት መንግሥታት የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ አስተባባሪ ማርቲን ግሪፊትስ በኢትዮጵያ የስድስት ቀናት ጉብኝት አድርገው ነበር።

በዚህ ጉብኝታቸው ፦

- ከፌደራል መንግሥቱ
- ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንት
- ከአፍሪካ ሕብረት
- ከሰብአዊ እና ዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ጋር ገንቢ ስብሰባዎች አካሂደዋል።

ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንዲሁም የሰላም ሚኒስትሯን ጨምሮ ከሌሎች ቁልፍ የመንግሥት በለሥልጣናት ጋር ስብሰባ አድርገዋል።

በስብሰባው ሰብአዊ እርዳታ ሁኔታና የረድዔት ድርጅቶች ለኢትዮጵያውያን እርዳታ በሚያቀርቡበት ወቅት የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች ላይ ለመወያየት ዕድል አግኝተው ነበር ተብሏል።

ግሪፊትስ ከኢትዮጵያ ጉብኝታቸው በኃላ በትዊተር ገፃቸው፦

- ከዶክተር አብይ ጋር ገንቢ ውይይት ማድረጋቸውን ገልፀዋል።

- ወደ ትግራይ ተጉዘው ድጋፍ የሚፈልጉ ዜጎችን አነጋግረዋል።

- እየሰፋ የመጣው ግጭት መቆም እንዳለበት ፣ የሰብዓዊ ድጋፍ ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች እንዲደርስ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ አንስተዋል።

- የእርዳታና የሰብአዊ እርዳታ ሰራተኞች ለተቸገሩ ሰዎች የሚደርሱበትን ሁኔታ ለማሻሻል ከመንግስት ጋር መሥራት አለብን ብለዋል።

- በቀን መቶ የጭነት መኪናዎችን ለማስገባት ጠንክረን እየሠራን ነው ይህ እንደሚሆን የኢትዮጵያ መንግስት አረጋግጦልናል ብለዋል።

- እርዳታ ለሚፈልጉ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ መድረስ እና የእርዳታ ሰራተኞች ጥበቃ እንዲደረግላቸው በግል መሥራቴን እቀጥላለሁ ብለዋል።

- በሰብአዊ ፍላጎት ውስጥ ላሉ ኢትዮጵያዊ ዜጎች ሁሉ እርዳታ እንዲደርሳቸው -በትግራይ ፣ በአማራ ፣ በአፋር፣ በማንኛውም ክልል- ቅድሚያ የምሰጠው ጉዳይ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

@tikvahethiopia
#Tokyo2020 🇪🇹 #Ethiopia

ድል ለሀገራችን ኢትዮጵያ !

ዛሬ በቶኪዮ ኦሎምፒክ የሀገራችን አትሌቶች ውድድራቸውን ይካሂዳሉ ።

ቀን 8:00 ላይ የ ወንዶች 1,500 ሜትር #ግማሽ_ፍፃሜ ውድድር የሚካሄድ ሲሆን ታደሰ ለሚ እና ሳሙኤል አባተ በ ርቀቱ የሚሳተፉ አትሌቶቻችን ናቸው።

ድል ለሀገራችን !

ፎቶ :- ከግራ ወደ ቀኝ ታደሰ ለሚ እና ሳሙኤል አባተ

@tikvahethsport