TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ለጥንቃቄ

" በምዕራብ ኦሞ ዞን ባለፉት ሦስት ወራት 9,000 #ህፃናት በኩፍኝ ተጠቅተዋል። 11 ሞት ተመዝግቧል " - የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ፦
° 65 በመቶ የሚሆን #ገዳይ የወባ ዝርያ እንዳለ፣
° በአንድ ዓመት ውስጥ 101 ሰዎች በወባ እንደሞቱ፣
° ማኅበረሰቡ ወደ ሕክምና ተቋማት እንዲሄድና አጎበር የመጠቀም ልምዱን እንዲያዳብር የክልሉ ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ዳይሬክተር አቶ ተስፋፅዮን ተረፈ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ኩፍኝ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ?

* ምዕራብ ኦሞ ዞን ባለፉት 3 ወራት 9,000 #ህፃናት በኩፍኝ ተጠቅተዋል። 11 ሞት ተመዝግቧል። በክልሉ በአንድ ዓመት ውስጥ 12,700 የኩፍኝ ኬዞች ተገኝተዋል። 

* ከሌሎች ቦታዎች በተለዬ መልኩ በምዕራብ ኦሞ ዞን አሁንም ከፍተኛ ሥራ የሚጠይቅ የኩፍኝ ወረርሽኝ ስርጭት አለ። በመቀጠልም በቤንቺ ሸኮና ከፋ ዞኖች በተወሰኑ ወረዳዎች ይስተዋላል።

* አርሶ አደሮች በሚኖሩባቸው ( #በተለይም ምዕራብ ኦሞ)፣ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች የክትባት አሰጣጡን አፌክት ያደርገዋል።

* #አርሶ_አደሮች ባሉባቸው አካባቢዎች ላይ ችግሩ እንዲቀረፍ ለማድረግ የጤና ባለሙያዎች በአካባቢው ተንቀሳቀሰው ሕክምና እንዲሰጡ እየተደረገ ነው።
 
* የኩፍኝ ኬዞች ያሉባቸው አራት ዞኖች ናቸው። ቤንቺ ሸኮ ዞን ላይ ወደ 3,000፣ ከፋ ዞን ከ1,000 በላይ ኬዞች ነበሩ ፤ አሁን መቆጣጠር ተችሏል።

* ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ የኩፍኝ ክትባት ዘመቻ ለማድረግ ጤና ሚኒስቴር ፈቅዷል። ከአምስት ዓመት በታች ለሚሆኑ ሕፃናት ክትባት ይደረጋል።
 
ወባ በምን ደረጃ ይገኛል?

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃልፊ አቶ ኢብራሄም ተማሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፦

- ለሁለት ዓመታት #የወባ_ወረርሽኝ በክልሉ ተከስቶ ቆይቷል። የኩፍኝ ወረርሽኝም በተለይ በምዕራብ ኦሞ ዞን ልዩ ትኩረት ይሻል። ከእስከዛሬው ጋር ሲነጻጸር ግን ኬዞቹ እየቀነሱ ነው። ግን አሁንም ሥራ ይጠይቃል።

- የወባ ወረርሽኝ ቆዬ ስንል በርካታ ሥራዎችን ሰርተናል ከወባ ጋር ተያይዞ ወደ 1.2 ሚሊዮን የአጎበር ስርጭት ተካሂዷል። ከ6,000 ኪ.ግ በላይ እርጭት ተካሂዷል።

- አሁንም ውሃ ያቆሩ ቦታዎች ላይ እርጭት እያካሄድን ነው ፤ በጣም በተለየ መንገድ ምዕራብ ኦሞ ላይ ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ያለው ግብዓት አሰራጭተን የመከላከሉን ሥራ እየሰራን ነው።

አቶ ተስፋፅዮ በበኩላቸው ስለ ወባ ምን አሉ ?

* የተወሰኑ ወረዳዎችን ላያካትት ይችል ይሆናል እንጂ ሁሉም  ዞኖች በጣም ከፍተኛ የወባ ጫና ያለባቸው ናቸው።

* በአመት ውስጥ #በ6_ዞኖች በወባ ወደ 101 ሞት ተመዝግቧል። አሁን ግን ማኅበረሰቡ  በአቅራቢያቸው ህክምና እያገኙ ስለሆነ የህመም (የኬዝ)፣ የሞት መጠኑ በዛው ልክ ቀንሷል።

* ላለፉት ሁለት ዓመት ለዚህ መንስኤ የሆኑ ጥናቶች ለማድረግ ሞክረናል፣ የምላሽ ሥራው ተሰርቷል።

* እስካሁን ባለው በአጠቃላይ ወደ 400,054 ሰዎች በአንድ ዓመት የወባ አይነቶች ተለይተው ህክምና ያገኙ ናቸው።

* በተሰሩ ሥራዎች በተለይ ከአራት ወራት በፊት እስከ 15,000 ሰዎች በወባ ይጠቁ ነበር። አሁን ባለንበት በሳምንት በወባ የመጠቃቱ ሁኔታ ከ7,000 እስከ 6,000 ሰዎች ዝቅ ለማድረግ ተችላል።

* በመከላከል ላይ ያለ ክፍተት ነው የወባ ቁጥር ከፍ ብሎ እዲታይ እያደረገ ያለው። ምዕራብ ኦሞ ፣ ካፋ ዞን በሚገኙ አካባቢዎች ላይ አርብቶ አደሮች ናቸው በተለይ ተጋላጭ የሆኑት።

* ከጤና ኬላ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ሆስፒታል ድረስ የወባ ህክምና አለ።

* ሞት እያስከተለ ያለው ቆይተው ስለሚመጡ ነው። ቆይተው ሲመጡ ደግሞ በክልላችን #ከ65 ፐርሰት በላይ ፋልሲፋረም የሚባል በባህሪው #ገዳይ የሆነ ዝርያ ነው ያለው።

* በእኛ ክልል ላይ የሚበዛው ያ " ፋልሲፋረም " ነው። ሰዎች ወዳውኑ ምልክቱን እንዳዩ የመወሳሰብ ደረጃ ላይ ሳይደርስ ወደ ጤና ተቋማት ሂደው መታከም አለባቸው። ችግሩ ሲወሳሰብ ደም ሊፈልግ ይችላል፣ #ነፍሰ ጡሮችን በተለይ ወዲያው የመግደል ዕድሉ ከፍተኛ ነው።

ለ2ቱም ወረርሽኞች ለሞት አደጋው መከሰት ምክንያቱ ፦

° የሕሙማን ወደ ሕክምና #ዘግይቶ መምጣት፣

° #የጤና_ኤክስቴንሽኖች ወረርሽኝ አካባቢዎች ላይ አክቲቭ አለመሆንና በወቅቱ ለይቶ አለመላክ ነበር።

* በዘላቂነት ችግሮቹን ለማስወገድ ክልሉ የንቅናቄ መድረክ እንያዘጋጀ ነው። አሁንም ዝናብ ወጣ እየገባ እያለ ስለሆነ ለወባ መራባት እጅግ በጣም ምቹ አጋጣሚ ስለሚፈጥር ማህበረሰቡ ጥንቃቄ ሊያደግ ይገባል።

ጥንቅሩ በአዲስ አበባ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አቶ ታዬ ደንደአ በቁጥጥር ስር ዋሉ። የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ የነበሩት አቶ  ታዬ ደንደአ በህግ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፀጥታ እና ደኀንነት የጋራ ግብረ ኃይል አሳውቋል። @tikvahethiopia
#Update

የአቶ ታዬ ደንአደን በቁጥጥር ስር መዋል በተመለከተ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረኃይል ምን አለ ?

ግብረ ኃይሉ አቶ ታዬ ደንደአ፥ ከለውጡ በፊት የኦነግ አባል የነበሩና በእስር ቤት የቆዩ መሆኑን ገልጿል።

የለውጡ መንግስት ባደረገላቸው ምህረት ከማረሚያ ቤት ተለቀው በተሰጣቸው እድል በተለያዩ የክልል እና የፌደራል መንግስት የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ሲሰሩ ነበር ብሏል።

ይሁን እንጂ አቶ ታዬ ከህዝብና የመንግስት የተሰጣቸውን ኃላፊነት በተለይም ደግሞ የሰላም ሚንስትር ዴኤታ ሆነው ሰላምን ለማስፈን መሥራት ሲገባቸው በተቃራኒዉ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱ ፀረሰላም ኃይሎች ጋር በመተሳሰር ለጥፋት ተልዕኮ በህቡዕ ሲሰሩ እንደተደረሰባቸው ገልጿል።

በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በንፁሃን ዜጎች ላይ ሲፈፀሙ በነበሩ የሽብር ተግባራት በተለይም ደግሞ #ከእገታ_ጋር በተያያዘ እጃቸው እንደአለበት ተደርሶበታል ብሏል።

አቶ ታዬ ደንደአ፤ በመንግስት ቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደሚችሉ ሲገምቱ ታጋይ ለመምሰል በራሳቸውና በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጾች አፍራሽና ፀረ ሰላም ፅሁፎችን፣ ንግግሮችንና መግላጫዎችን በማን አለብኝነት ሲያስተላልፉና ሲሰጡ ቢቆዩም ከተጠያቂነት ማምለጥ ባለመቻላቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል ብሏል።

ግብረኃይሉ አቶ ታዬ መንግስታዊ ኃላፊነታቸውን ተቀብለው እየሰሩ በነበረበት ወቅት መንግስታዊና የፓርቲ መዋቅሩን በሴራ ለመናድ በህቡእ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ መቆየታቸውና ጥናትና ክትትል ሲደረግበት እንደነበር አመልክቷል።

በተደረገው ክትትልም አቶ ታዬ " ከኦነግ ሸኔ " አመራሮችና በሽብር ወንጀል ከተጠረጠሩ ጽንፈኛ ኃይሎች ጋር ትስስር በመፍጠር መንግስትን በአመጽ፣ በሽብርና፣ በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲያሴሩ እንደ ተደረሰበት ገልጿል።

ተጠርጣሪ ታዬ በህግ ቁጥጥር ሥር ሲውሉ በመኖሪያ ቤታቸው ዉስጥ በተደረገ ፍተሻ ፦
* በህቡዕ ለሚያደርጓቸው ፀረ-ሰላም እንቅስቃሴ ሲገለገልባቸዉ የነበሩ የተለያዩ 9 ሞባይሎች፣
* 4 ላፕቶፖች፣ 3 አይፖዶች፣ በርካታ ፍላሾች፣
* 4 የተለያዩ ተሸከርካሪ ሰሌዳዎች
* ልዩ ልዩ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች፣
* ክላሽንኮቭ ጠመንጃና ሽጉጦች ከመሰል ጥይቶች ጋር
* የኦነግ ሸኔ አርማዎችና በተለያዩ ግለሰቦች ስም የተዘጋጁ የኦነግ ሸኔ መታወቂያዎች፣ ሰነዶችና ማስታወሻዎች ተገኝተዋል ብሏል።

ከዚህም በተጨማሪ በብርበራ ወቅት በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በ3 መታወቂያዎች የሚጠቀም አንድ " የኦነግ ሸኔ " አባል ተደብቆ መገኘቱንና በቁጥጥር ሥር መዋሉንም ገልጿል።

ግብረኃይሉ አቶ ታዬ ደንደአ በተመደቡባቸው ከፍተኛ የመንግስት ስልጣን ላይ ሆነው በተደጋጋሚ መንግስትን #ገዳይ እና #ጨፍጫፊ እያሉ ሲወቅሱ የሚደመጥ ቢሆንም፤ በተግባር ግን ከሽብርተኞች፣ ጽንፈኛችና ነፍሰ ገዳዮች ጋር የጥፋት ትስስር የነበራቸው ራሳቸው መሆኑ በተደረገ ክትትል ተረጋግጧል ብሏል።

@tikvahethiopia