TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" ችግሮች መፍታት የሚቻል ከሆነ በፍጥነት ቢፈቱ እና ህዝቡ ወደ ቀድሞው ኑሮው እንዲመለስ ቢደረግ መልካም " - የቲክቫህ አባላት

ቤተሰቦቻቸው በትግራይ ክልል ውስጥ የሚኖሩ ዜጎች በክልሉ ላለው ችግር እካሁን ይሄ የሚባል መፍትሄ ባለመምጣቱ ህዝቡ ስቃዩ እየተራዘመ ነው ብለዋል።

በቅርብ ሳምንት የታዩት በጎ ነገሮች መልካም ቢሆንም በፍጥነት ወደ ታች ወርዶ በችግር ላይ ያለውን ህዝብ መታደግ ይገባል ሲሉም ገልፀዋል።

ነዋሪዎች ባለፉት በርካታ ወራት ፦
👉 ያለ ባንክ፣
👉 ያለ ስልክ፣
👉 ያለ ትራንስፖርት ፣
👉 ያለ የንግድ ልውውጥ፣
👉 ያለ ስራ፣
👉 ያለ ትምህርት
👉 ከምንም በላይ ደግሞ ያለ በቂ ህክምና ላይ ነው የሚገኙት ይህን ለአንድ ቀን እንኳን ለማሰብ የሚከብድ ሁኔታ ከግምት በማስገባት ያሉት ችግሮች የሚፈቱበት አግባብ ቢፋጠን ፤ ዜጎችም ወደ ቀደመ ህይወታቸው እንዲመለሱ ቢደረግ ሲሉ ጠይቀዋል።

ለበርካታ ወራት ባለው ሁኔታ ምንም ፖለቲካ የማያውቁ ፣ ስላለው ሁኔታ በቅጡ የማይረዱ እጅግ ብዙ ሰዎች አብረው የችግሩ ገፈጥ ቀማሽ ሆነዋል፤ ሌላው ቢቀር ለትንንሽ ህፃናት፣ ሴቶች እና አረጋዊያን ተብሎ ፈጣን መፍትሄ ቢፈግ ሲሉም ተማፅነዋል።

በተለይም ፤ ከባንክ አለመኖር ጋር በተያያዘ ብዙ ችግር መከሰት ከጀመረ ወራት መቆጠሩንና ይህም ችግር ለማንም ግልፅ እንደሆነ አንስተዋል።

መልዕክታቸውን ከላኩ ቤተሰቦቻችን አንዱ " ቤተሰቦቼ የሚኖሩት ትግራይ ክልል ነው። ታድያ በጦርነቱ ምክንያት በትግራይ ላይ ባንኮች አገልግሎት እየሰጡ ባለመሆናቸው ምክንያት ህዝቡ በብዙ ችግሮች ውስጥ እየኖር ነው " ብሏል።

አክሎም ፤ " ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም በአቋራጭ መበልፅግ የሚፈልጉ እራስ ወዳዶች ትግራይ ክልል ውስጥ የሚገኙት ቤተሰቦቹ ብር መላክ ከሚፈልግ ሰው አላማጣ ላይ ባሉት ሰዎቻቸው ሆነው አዲስ አበባ ከተማ እና ሌሎች ቦታዎች ላይ መቀመጫቸውን ካደረጉ ግለሰቦች እስከ 50 በመቶ ማስላክያ ክፍያ በመቁረጥ ከሚልከውና ከሚቀበለው ህዝብ እየዘረፉ ይገኛል " ሲል አስረድቷል።

በዚህ ላይ አስፈላጊውን እርምት ሊወሰድ እንደሚገባና በአፋጣኝ በትግራይ የባንክ አገልግሎት እንዲጀመር ሊደረግ ይገባል ሲል ጠይቋል።

በትግራይ ፤ በብር እጦት ምክንያት ስላለው የፖለቲካ ሁኔታ ምንም የማያውቁ ንፁሃን እየሞቱ እና እየተንገላቱ ነውና ፈጣን መፍትሄ ያስፈልጋል ብሏል።

ከዚህ ቀደም የቤተሰቦቻችን አባላት ፤ በክልሉ ውስጥ ስላለው ሁኔታ በተደጋጋሚ መግለፃቸው እና በተለይ በተለይ ለ #ህፃናት#ሴቶች እንዲሁም #አረጋዊያን ካለው ችግር እንዲወጡ ፈጣን መፍትሄ እንዲፈለግ መማፀናቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ግጭት ከተቀሰቀሰ በኃላ እስካሁን ምን ሆነ (እጅግ በጥቂቱ) ?

- ህወሓት ቆቦና የአካባቢው ቦታዎችን መቆጣጠሩን ተከትሎ ከፍተኛ የሰው ቁጥር ሰላም እና ደህንነት ፍለጋ ወደ አጎራባች ከተሞች እንዲፈናቀል ምክንያት ሆኗል።

- እንደ ዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል በመቐለ በተፈፀመ የአየር ጥቃት 4 ሰዎች ተገድለዋል ፤ 2ቱ ህፃናት ናቸው። የኢትዮጵያ መንግስት ግን ንፁሃንን ዒላማ ያደረገ ጥቃት እንደማይፈፅም በመግለፅ የወጡ ክሶችን አስተባብሎ ነበር።

- ህወሓት በአፋር ክልል " ያሎ " በኩል በሰነዘረው የከባድ መሳሪያ ጥቃት በአካባቢው ንፁሃን ነዋሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የዱብቲ ጠቅለላ ሆስፒታል የገለፀ ሲሆን በጥቃቱ ህፃናት ተገድለዋል። አንዲት እናት ሁለት ህፃናት ልጆቿ በከባድ መሳሪያ ጥቃት ተገድለውባታል። የቆሰሉም በርከት ያሉ ናቸው።

- የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር እንደገለፀው " ወለህ " አካባቢ ህወሓት 10 ሰላማዊ ሰዎችን በግፍ መግደሉን፣ ከሟቾች መካከል አንዲት እናት ከነ ልጆቿ እንደምትገኝበት ገልጿል። በተጨማሪ ቡድኑ ወደ ወለህ መጠለያ ጣቢያ በመግባት 25 ሰዎችን መግደሉን አስተዳደሩ ገልጿል።

- ህወሓት በአፍሪካ ህብረት (AU) መሪነት ለሰላም ንግግር ዝግጁ መሆኑ በገለፀ በሰዓታት ውስጥ ይዟቸው በሚገኙ የራያ ቆቦ ወረዳዎች በንፁሃን ላይ ጥቃት መዘንዘሩን ነዋሪዎች መግለፃቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። ህወሓቶች በቀበሌ 02 ሰው መግደላቸው፣ ማቁሰላቸው ነዋሪዎች ገልፀዋል። ከጥቂት ቀናት በፊትም አራዱም ላይ ሰላማዊ ሰው መግደላቸውን ገልፀዋል። ባለፉት 18 ቀናት ሌሎች ያልታጠቁ ንፀሃን ሰዎችን መግደላቸውና በተጨማሪ ዝርፊያ እንደፈፀሙ ለሬድዮ ጣቢያው ገልፀዋል።

- የመቐለ ዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል እንደገለፀው 2 ጊዜ በተፈፀመ የአየር ጥቃት 10 ሰዎች ተገድለዋል። ከእነዚህ መካከል አብዛኞቹ የመጀመሪያዎቹን ተጎጂዎች ለመርዳት በተሰበሰቡበት ወቅት በተፈፀመ ጥቃት የተገደሉ ናቸው ብሏል። (ይህ የሆነው ትላንት ነው)

- UN OCHA በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ዳግም ባገረሸ ግጭት በርካታ ሰዎች መፈናቀላቸውን አመልክቷል።

እንደ UN OCHA መረጃ ፦

👉 በአማራ ፣ አፋር፣ እና ትግራይ ክልሎች በ10 ሺዎች መፈናቀለቸውን ገልጿል።

👉 የሰብዓዊ እርዳታ ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ መግባት እንዳቆሙ፣ ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ በረራ እንደተቋረጠ መሆኑን ገልጿል።

👉 በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ለመገኙ ተፈናቃዮች ድጋፍ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

👉 በመርሳ ከተማ በ5 ት/ቤቶች አብዛኞቹ #ህፃናት እና #ሴቶች ከቆቦ እና አካባቢው ተፈናቅለው ተጠልለው የሚገኙ ሲሆን ለእነሱ ምግብ እና ምግብ ያልሆኑ ድጋፎችን ማሰራጨት ጀምራለሁ ብሏል።

- የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጠው ቃል በዞኑ የተፈናቃዮች ቁጥር እጅግ እየጨመረ መሆኑን ገልጾ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ገልጿል። መርሳ በሚገኙ ት/ቤቶቹ ውስጥ ያሉት ሴቶች እና ህፃናት ሲሆኑ ወንዶች ወጣቶች እንዲገቡ አልተደረገም። በአጠቃላይ ወልድያ እና መርሳ ከተሞች ላይ 92,400 ተፈናቃይ አለ።

- ጦርነቱ ዳግም ካገረሸ ወዲህ በርካታ ንብረቶች ወድመዋል።

- የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ወደ ባህርዳር ቢሮው የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መልዕክቶች እየመጡለት ሲሆን አካባቢዎቹ ላይ ምቹ ሆኔታ ሲፈጠር ምርመራ አድርጎ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።

NB. የተዘረዘሩት ክስተቶች ግጭት ዳግም ካገረሸ ወዲህ #በተለያዩ_ጊዜያቶች የተሰሙ ናቸው።

የሰላም ሂደቱ ምን ያህል ተስፋ ሰጪ ነው ?

የኢትዮጵያ መንግስት በአፍሪካ ህብረት (AU) መሪነት ለሰላማዊ ንግግር ዝግጁ መሆኑን ከሳምንታት በፊት ገልጾ ነበር።

ህወሓት በአፍሪካ ህብረት (AU) አፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦባሳንጆ ላይ እምነት እንደሌለውና በሂደቱ መተማመን እንደሌለው ሲገልፅ ከቆየ በኃላ ከቀናት በፊት በህብረቱ መሪነት ለሚደረግ የሰላም ንግግር ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።

ይህንን የህወሓት የሰላም ሂደት መቀበል እና ግጭት ለማቆም ዝግጅቱነት እንዳለው መግለፁን በተመለከተ በርካታ አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን የተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት ውሳኔውን በማድነቅ የሰላም ሂደቱ እንዲፋጠን ጥሪ አቅርበዋል።

ዳግም ያገረሸው ጦርነት ግን አሁንም አልቆመም።

የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን ህወሓት ላወጣው መግለጫ በግልፅ ቀጥተኛ ምላሽ ባይሰጥም ትላንት ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋር በተወያዩበት ወቅት መንግስት ለአፍሪካ ህብረት የሰላም ሂደት ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል።

በሌላ በኩል ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላም ቁርጠኛ መሆኑን በዩናይትድ ኪንግደም ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ገልጿል።

የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ሰላማዊ የሆነ መፍትሄ እንዲያገኝ መንግስት ዝግጁነት እንደነበረው ነገር ግን ህወሓት በቅርቡ ወረራ መፈፀሙን ኤምባሲው ዛሬ አመልክቷል።

አሁንም ቢሆን የኢትዮጵያ መንግስት ግጭቱ እንዲፈታ የሚያምንበት ብቸኛ አማራች ሰለማዊ መፍትሄ መሆኑን ገልጿል።

በተጨማሪ አምባሳደር ተፈሪ መለሰ አልጀዚራ ላይ ባወጡት ፅሁፍ መንግስት በየትኛውም ጊዜ እና ቦታ ለሰላም ውይይት ዝግጁ እንደሆነ አስታውሰው ህወሓት የሰላም ጥሪ ገፍቶ ጦርነት ከፍቷል ብለዋል።

ህወሓት የጀመረውን ጥቃት በማቆምም ወደ ሰላም ድርድር እንዲመለስ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና ሊያደርግ ይገባልም ብለዋል።

በአፍሪካ ህብረት ስር ለሚደረገው ድርድር ፍላጎቱን ማሳየቱን ተከትሎ በቃሉ እንዲፀና ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ሚናውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል።

ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ከዝምታው በመውጣት የመንግስትን የሰላም አማራጭ በመደገፍ ህወሓት ታጣቂዎቹን ትጥቅ በማስፈታት ወደ ድርድር እንዲገባ ጫና ማድረግ አለበት ሲሉም አሳውቀዋል።

ህወሓት ወደሰላም እንዲመለስና ሰላምን ለማረጋገጥ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና ማድረግ ያለበት አሁን ነው ያሉት አምባሳደሩ ይህ ካልሆነ መንግስት ህዝብን የመጠበቅ ግዴታ ስላለበት ግዴታውን ይወጣል ብለዋል።

ከቀናት በፊት " ህወሓት " ፤ በአፍሪካ ኅብረት (AU) የሚመራ ተዓማኒ የሰላም ሒደት እንደሚጠብቅ ፤ በአፍሪካ ህብረት መሪነት ለመደራደር ዝግጁ መሆኑን ፤ ለድርድሩ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ፣ ለአፋጣኝ እና በሁለቱም ወገኖች ስምምነት ተግባራዊ ለሚደረግ የተኩስ አቁም ዝግጁ መሆኑን መግለፁ እንዲሁም ለግጭት ዘላቂ የሆነ መፍትሄ ማምጣት የሚቻለድ በሰላማዊ ውይይት ብቻ እንደሆነ እግጠኛ መሆኑን ማሳወቁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሶማሌክልል በሶማሌ ክልል በተከሰተው የጎርፍ አደጋ እስካሁን 28 ሰዎች ሲሞቱ ከ300,000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው ተጠቆመ። በሶማሌ ክልል ከ33 ወረዳዎች በላይ ተከሰተ የተባለውን የጎርፍ አደጋ በተመለከተ ተጎጂዎችና ተፈናቃዮች በምን ሁኔታ እንደሚገኙ ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቦታው እርዳታ እያደረገ የሚገኘውን Save the Childrenን ጠይቋል። የድርጅቱ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ዳይሬክተር አቶ አብዲራዛቅ…
#ሱማሌ_ክልል

" እስካሁን ከ700 በላይ ሰዎች በኮሌራ ተጠቅተዋል። 23 ሰዎች መሞታቸው ተረጋግጧል። ከ23ቱ ወደ 11 የሚሆኑት #ህፃናት ናቸው " - አቶ አብዲሪዛቅ አህመድ

በሱማሌ ክልል በሚገኙ ተፈናቃዮች ላይ የከፋ ኮሌራ ወረርሽኝ መከሰቱን፣ ወረርሽኙን ለመከላከል የመድኃኒት እጥረት ፈተና በመሆኑ ርብርብ ካልተደረገ ከ500,000 በላይ ተፈናቃዮች በወረርሽኙ የመጠቃት ዕድላቸው ሰፊ መሆኑን ሴቭ ዘ ችልድረን (Save the children) የሱማሌ ክልል ቅርንጫፍ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።

የሱማሌ ክልል ሴቭ ዘ ችልድረን ቅርንጫፍ ዳይሬክተር አቶ አብዲሪዛቅ አህመድ ምን አሉ ?

- እስካሁን #ከ700 በላይ ሰዎች በኮሌራ ተጠቅተዋል። 23 ሰዎች መሞታቸው ተረጋግጧል። ከ23ቱ ወደ 11 የሚሆኑት ህፃናት ናቸው። ከ700ዎቹ ተጠቂዎች መካከል 319ኙ ህፃናት ናቸው።

- በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ምክንያት ብዙ መጸዳጃ ቤቶች ወድመዋል። የተፈናቀሉ ሰዎች መጸዳጃ ቤት የላቸውምና ይሄ ሁኔታ በጣም አሳሳቢ ሆኗል። ተፈናቃዮቹ የሚኖሩበት ቤት የላቸውም።

ኮሌራ የተከሰተው መቼ ነው ?

- ኮሌራ ከተከሰተ ከሁለት እስከ ሦስት ወራት አስቆጥሯል። ሆኖም ግን ዝናብ መዝነብ ከጀመረ በኋላ ነው ኬዞቹ በጣም እየበዙ የመጡት።

- ሕክምና ካላገኙ #ይሞታሉ። ኮሌራ በጣም መጥፎ ተላላፊ በሽታ ነው። መድኃኒት እንዴት ይገኛል የሚለው ግን አሁንም አጠያያቂ ጥያቄ ነው። 

- በተለይ ቀላፎ ወረዳ መንገዱ ስለተጎዳ አክሰስ የለም፣ የመድኃኒት እጥረት ሲያጋጥም ለማድረስ እንኳ ለትራንስፖርት ያስቸግራል። ተፈናቃናቃዮቹ በጠባብ መጠለያ ውስጥ ከአሥር ሰዎች በላይ ሆነው ተጣበው ነው የሚኖሩት። መጸዳጃ ቤት የላቸውም፣ ኮሌራው የመዛመት ዕድሉ ከፍተኛ ነው።

በጎርፍ ሳቢያ የተፈናቃዮችና የተጎጂዎች ቁጥር  ጨመረ ወይስ ቀነሰ ?

-የተፈናቃዮች ቁጥር ከ300,000 ወደ #500,000፣ የተጎጂዎች ቁጥር ከ600,000 ወደ #1.4 ሚሊዮን ደርሷል። ካሉበት ቦታ እስከመቼ እንደሚቀመጡ አይታወቅም፣ ምክንያቱም ጎርፉ እስካሁን እንደቀጠለ ነው።

- ከእነዚህ ተጎጂዎች መካከል እስካሁን ድጋፍ ያገኙት #10 በመቶዎቹ ብቻ ናቸው። ቀሪዎቹ #90 በመቶዎች አፋጣኝ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል።

- የጎርፍ አደጋው እስካሁን እየተስፋፋ ነው። ብዙዎች እየተጎዱና እየተፈናቀሉ ነው።  ሰሞኑን ዝናቡ ስለቀነሰ ምናልባት ከዚህ በኋላ አደጋው ሊቀንስ ይችላል የሚል ተስፋ አለ።

ምን ተሻለ ?

ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ ስላለ ማኅበረሰቡ የሚዛመትበትን መንገድ እንዲያውቅ አዌርነስ እንዲፈጠር፣ መድኃኒትና ነርስ በቂ ስላልሆነ እንዲጨመር፣ ኬዙ ያለባቸው ቦታዎች ኮሌራ ትሪትመንት ሴንተር እንዲገነባ፣ የታመመ ሰው ቶሎ ወደ ሆስፒታል እንዲደርስ የሚያስችል ቲም እንዲቋቋም አቶ አብዲሪዛቅ ጠይቀዋል።

የተከሰተው ኮሌራ ዋና ምንጩ ምን እንደሆነ መለየትና በአፋጣኝ ከምንጩ ማድረቅ ዋነኛው ተግባር መሆን እንዳለበት ጠቁመው፣ ንጹህ የውሃ ችግር ስላለ ተፈናቃዮች የተበከለ ውሃ እንዳይጠቀሙ የውሃ ሳኒታይዘር እንደሚያስፈልግም አክለዋል።

ድጋፍ ካልተገኘ በቀጣዮቹ ሳምንታት ብዙ ሰዎች ሊሞቱ ይችላሉ ያሉት ዳይሬክተሩ፣ ችግሩ ሰፊና የከፋ፣ ከመንግሥት አቅም በላይ ስለሆነ አለም አቀፍ ኤጀንሲዎች ጋር ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

መረጃውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ነው።

@tikvahethiopia
#ትግራይ - ያልመከኑ የጦር መሣሪያዎች !

" መቐለ ወደ #ስድስት_ቦታዎች አሁን ራሱ ያልመከኑ ቦንቦች አሉብን። … እስካሁን ድረስ ሞትና አደጋ 1,038 ነው በቢሯችን የያዝነው " - የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ

ባለፉት 2 አመታት የነበረው ከፍተኛ ጦርነት በግንባር ብቻ ሳይሆን በትግራይ ክልል ውስጥ ባሉ የተለያዩ ቦታዎች ላይም ስለተካሄደ አርሶ አደሮችን ጨምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ህፃናትና የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ባልመከኑ የጦር መሣሪያዎች ሞትና የአካል ጉዳት አደጋዎች እየደረሱባቸው መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከትግራይ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ ሰምቷል።

የትግራይ ጤና ቢሮ ፤ የድንገተኛ ሕክምና አስተባባሪ አቤንዘር እፀድንግል (ዶ/ር) ስለ ጉዳዩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲያስረዱ፣ " በትምህርት ቤቶች፣ በሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎች፣ መቀሌ ወደ ስድስት ቦታዎች አሁን ራሱ ያልፈነዱ ቦንቦች አሉብን፣ ያልተነሱ ማለት ነው " ያሉ ሲሆን፣ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረቡላቸው የተለያዩ ጥያቄዎችም ማብራሪያዎች ሰጥተዋል።

ያልመከኑት የጦር መሣሪያዎች #መቐለ የት የት ቦታዎች ይገኛሉ ?

- አንደኛው #ከፕላኔት_ጀርባ አካባቢ ነው።

- ሁለተኛው ቦታ የህፃናት መጫወቻ ስፍራ የተመታበት #የአፄ_ዮሐንስ_ቤተመንግሥት_ጀርባ በኩል ነው።

- ሦስተኛው #05 አካባቢ ነው።

- ሌሎቹ ደግሞ መቐለ ውስጥ ሆነው ግን #እርሻ ቦታ ላይ ነው ያሉት።

በርግጥ በኅብረተሰቡ ላይ #አደጋን_እንደሚያደርሱ የሚገልፅ ምልክት (አጥር) ተደርጓል ግን በከፍተኛ ጥንቃቄ እና በባለሙያ መነሳት አለባቸው " ብለዋል።

ባልመከኑ የጦር መሣሪያዎች ምን ያህል ሰዎች ላይ ሞትና የአካል ጉዳት ደረሰ ?

" ሁሉንም ወደ ጤና ተቋማት አምጥተን ለማከም ሁኔታው አልተመቸም ነበር። ስለዚህ ሙሉ ዳታ የለንም።

ሙሉ ዳታ አባባሌ አንዳንዶቹ አደጋ ደርሶባቸው የሞቱ አሉ፣ ሌሎች መምጣት ያልቻሉ ብዙ ሰዎችም እንዳሉ ግምት ውስጥ ማስገባት አለብን። ባልፈነዱ የጦር መሣሪያዎች ፣ በተጣሉ ተተኳሽ እና የተቀበሩ ቦንቦች አደጋ የደረሰባቸው ባለን ዳታ መሠረት ፦

- እስካሁን ሞትና አደጋ በአጠቃላይ 1,038 ነው ያለን በእኛ በቢሯችን የያዝነው። #163 ሞት፣ 875 ደግሞ ከባድ ጉዳት ማለት ነው።

- ከ163ቱ መካከል 84ቱ ዕድሜአቸው ከ17 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት፣ 79ኙ ደግሞ ዕድሜአቸው ከ18 በላይ የሆኑ አዋቂዎች ናቸው።

- ከ84 #ህፃናት ውስጥ 75ቱ ወንዶች፣ 9ኙ ደግሞ #ሴቶች ናቸው ብለዋል።

ችግሩ አሁንም እንደቀጠለ ነው ? አሁንም የሚመጡ አሉ ?

- አዎ አሁንም ድረስ ይመጣሉ። በተለይ ክረምት ላይ በእርሻ ሥራ መቀሳቀስ ስለሚኖር፣ በመነካካትም ሳያውቁ እያረሱ እያለ መፈዳት ያጋጥማቸው ስለነበሩ ቁጥሩ እየቀነሰ ቢሄድም አልፎ አልፎ እየመጡ ነው። ምክንያቱም በተጠናከረ ደረጃ አልተጠረገም። 

- ፈንጅ ነገሮችን የማጥራት ሥራ ካልሰራን ትልቅ ችግር ነው ያለው። የመንግሥት ተዋጊ አካሎች ትምህርት ቤቶችን እንደ አውደ ማቆያ ሲጠቀሙባቸው ስለነበር እዛ ላይ የተጣሉ ጦር መሳሪያዎች አሁን ትምህርት ሲጀምሩ #ህፃናት በተለያየ ጊዜ አደጋ ይደርስባቸዋል።

- በተለያዩ መንገዶች ሰው ተሸክሟቸው ፣ በጋሪ ፣ በፈረስ ፣ በበቅሎ ሕክምና ቦታ መድረስ የቻሉ ሰዎች እንኳ (በተለይ ደግሞ ሽረ አካባቢ የመጡ ብዙ ታካሚዎች) መድኃኒት በበቂ ሁኔታ ስላልነበረ የጤና ተቋማት በቂ ሕክምና ሊሰጧቸው ባለመቻላቸው ብዙ ያጣናቸው አሉ።

- አካል ጉዳተኞችም ሆነዋል ሕክምና ቢደረግላቸው መትረፍ እየቻሉ ግን የሰርጀሪ እቃዎች እጥረት ስለነበረ አካል ጉዳተኛ የሆኑት በርከት ያሉ ሰዎች ናቸው። በአጠቃላይ በነበረው ሁኔታ ከባድ ነበር ግን አሁን ባለዉ ሁኔታ በተቻለ መጠን ባለን አቅም አገልግሎት እየሰጠን ነው።

ከመድኃኒት እጥረቱ ጋር በተያያዘ የአካል ጉዳተኛ የሆኑ ሰዎችን በቁጥር ደረጃ መግለፅ እችላለን ?

- በቁጥር እንኳ ያስቸግራል፣ ግን እኔ የማስታውሳቸው ወደ ሦስት #ህፃናት በአንድ ወቅት ገብተው የሕክምና እቃዎችን ማግኘት ስላልተቻለ ለአካል ጉዳት ተጋልጠዋል። ይህ በአንድ ወቅት ብቻ ነው። በተጠና መልኩ ግን ብዙ ሊሆኑ ይችላሉ በቁጥር ደረጃ አጋጣሚ አልያዝነውም።

ምን ተሻለ ?

- አንደኛ ከሁሉ በላይ በመጀመሪያ እንዲህ አይነት መሣሪያዎችን መነካካት እንደሌለባቸው ህፃናት፣ ማኅበረሰቡ ማወቅ እንዳለባቸው ትምህርት መሰጠት አለበት።

- የፈንጅ #አምካኝ ባለሙያዎች በስፋት በማሰማራት በእያንዳንዱ ቦታዎች ተሰብስበው ያልመከኑ የጦር መሣሪያዎች መወገድ አለባቸው ፤ በየአካባቢው በጣም በርከት ያሉ #ያልተነሱ ፈንጂዎች አሉብን።

- ከተነሱ ነው በዘላቂነት መፍትሄ የሚገኘው። ሕዝብ ባለበት ቦታ ምንም አይነት ጦርነት አለማካሄድ ላለማካሄድ የሚደነግጉ መርሆዎችም መከበር አለባቸው። የህዝብ መገልገያ ቦታዎች ለወታደራዊ አላማ አለማዋል እንሰ እሪኮመዴሽንም መወሰድ አለበት።

ዘገባው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የተላከ ነው።

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ

" በምዕራብ ኦሞ ዞን ባለፉት ሦስት ወራት 9,000 #ህፃናት በኩፍኝ ተጠቅተዋል። 11 ሞት ተመዝግቧል " - የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ፦
° 65 በመቶ የሚሆን #ገዳይ የወባ ዝርያ እንዳለ፣
° በአንድ ዓመት ውስጥ 101 ሰዎች በወባ እንደሞቱ፣
° ማኅበረሰቡ ወደ ሕክምና ተቋማት እንዲሄድና አጎበር የመጠቀም ልምዱን እንዲያዳብር የክልሉ ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ዳይሬክተር አቶ ተስፋፅዮን ተረፈ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ኩፍኝ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ?

* ምዕራብ ኦሞ ዞን ባለፉት 3 ወራት 9,000 #ህፃናት በኩፍኝ ተጠቅተዋል። 11 ሞት ተመዝግቧል። በክልሉ በአንድ ዓመት ውስጥ 12,700 የኩፍኝ ኬዞች ተገኝተዋል። 

* ከሌሎች ቦታዎች በተለዬ መልኩ በምዕራብ ኦሞ ዞን አሁንም ከፍተኛ ሥራ የሚጠይቅ የኩፍኝ ወረርሽኝ ስርጭት አለ። በመቀጠልም በቤንቺ ሸኮና ከፋ ዞኖች በተወሰኑ ወረዳዎች ይስተዋላል።

* አርሶ አደሮች በሚኖሩባቸው ( #በተለይም ምዕራብ ኦሞ)፣ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች የክትባት አሰጣጡን አፌክት ያደርገዋል።

* #አርሶ_አደሮች ባሉባቸው አካባቢዎች ላይ ችግሩ እንዲቀረፍ ለማድረግ የጤና ባለሙያዎች በአካባቢው ተንቀሳቀሰው ሕክምና እንዲሰጡ እየተደረገ ነው።
 
* የኩፍኝ ኬዞች ያሉባቸው አራት ዞኖች ናቸው። ቤንቺ ሸኮ ዞን ላይ ወደ 3,000፣ ከፋ ዞን ከ1,000 በላይ ኬዞች ነበሩ ፤ አሁን መቆጣጠር ተችሏል።

* ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ የኩፍኝ ክትባት ዘመቻ ለማድረግ ጤና ሚኒስቴር ፈቅዷል። ከአምስት ዓመት በታች ለሚሆኑ ሕፃናት ክትባት ይደረጋል።
 
ወባ በምን ደረጃ ይገኛል?

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃልፊ አቶ ኢብራሄም ተማሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፦

- ለሁለት ዓመታት #የወባ_ወረርሽኝ በክልሉ ተከስቶ ቆይቷል። የኩፍኝ ወረርሽኝም በተለይ በምዕራብ ኦሞ ዞን ልዩ ትኩረት ይሻል። ከእስከዛሬው ጋር ሲነጻጸር ግን ኬዞቹ እየቀነሱ ነው። ግን አሁንም ሥራ ይጠይቃል።

- የወባ ወረርሽኝ ቆዬ ስንል በርካታ ሥራዎችን ሰርተናል ከወባ ጋር ተያይዞ ወደ 1.2 ሚሊዮን የአጎበር ስርጭት ተካሂዷል። ከ6,000 ኪ.ግ በላይ እርጭት ተካሂዷል።

- አሁንም ውሃ ያቆሩ ቦታዎች ላይ እርጭት እያካሄድን ነው ፤ በጣም በተለየ መንገድ ምዕራብ ኦሞ ላይ ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ያለው ግብዓት አሰራጭተን የመከላከሉን ሥራ እየሰራን ነው።

አቶ ተስፋፅዮ በበኩላቸው ስለ ወባ ምን አሉ ?

* የተወሰኑ ወረዳዎችን ላያካትት ይችል ይሆናል እንጂ ሁሉም  ዞኖች በጣም ከፍተኛ የወባ ጫና ያለባቸው ናቸው።

* በአመት ውስጥ #በ6_ዞኖች በወባ ወደ 101 ሞት ተመዝግቧል። አሁን ግን ማኅበረሰቡ  በአቅራቢያቸው ህክምና እያገኙ ስለሆነ የህመም (የኬዝ)፣ የሞት መጠኑ በዛው ልክ ቀንሷል።

* ላለፉት ሁለት ዓመት ለዚህ መንስኤ የሆኑ ጥናቶች ለማድረግ ሞክረናል፣ የምላሽ ሥራው ተሰርቷል።

* እስካሁን ባለው በአጠቃላይ ወደ 400,054 ሰዎች በአንድ ዓመት የወባ አይነቶች ተለይተው ህክምና ያገኙ ናቸው።

* በተሰሩ ሥራዎች በተለይ ከአራት ወራት በፊት እስከ 15,000 ሰዎች በወባ ይጠቁ ነበር። አሁን ባለንበት በሳምንት በወባ የመጠቃቱ ሁኔታ ከ7,000 እስከ 6,000 ሰዎች ዝቅ ለማድረግ ተችላል።

* በመከላከል ላይ ያለ ክፍተት ነው የወባ ቁጥር ከፍ ብሎ እዲታይ እያደረገ ያለው። ምዕራብ ኦሞ ፣ ካፋ ዞን በሚገኙ አካባቢዎች ላይ አርብቶ አደሮች ናቸው በተለይ ተጋላጭ የሆኑት።

* ከጤና ኬላ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ሆስፒታል ድረስ የወባ ህክምና አለ።

* ሞት እያስከተለ ያለው ቆይተው ስለሚመጡ ነው። ቆይተው ሲመጡ ደግሞ በክልላችን #ከ65 ፐርሰት በላይ ፋልሲፋረም የሚባል በባህሪው #ገዳይ የሆነ ዝርያ ነው ያለው።

* በእኛ ክልል ላይ የሚበዛው ያ " ፋልሲፋረም " ነው። ሰዎች ወዳውኑ ምልክቱን እንዳዩ የመወሳሰብ ደረጃ ላይ ሳይደርስ ወደ ጤና ተቋማት ሂደው መታከም አለባቸው። ችግሩ ሲወሳሰብ ደም ሊፈልግ ይችላል፣ #ነፍሰ ጡሮችን በተለይ ወዲያው የመግደል ዕድሉ ከፍተኛ ነው።

ለ2ቱም ወረርሽኞች ለሞት አደጋው መከሰት ምክንያቱ ፦

° የሕሙማን ወደ ሕክምና #ዘግይቶ መምጣት፣

° #የጤና_ኤክስቴንሽኖች ወረርሽኝ አካባቢዎች ላይ አክቲቭ አለመሆንና በወቅቱ ለይቶ አለመላክ ነበር።

* በዘላቂነት ችግሮቹን ለማስወገድ ክልሉ የንቅናቄ መድረክ እንያዘጋጀ ነው። አሁንም ዝናብ ወጣ እየገባ እያለ ስለሆነ ለወባ መራባት እጅግ በጣም ምቹ አጋጣሚ ስለሚፈጥር ማህበረሰቡ ጥንቃቄ ሊያደግ ይገባል።

ጥንቅሩ በአዲስ አበባ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ #ዋግኽምራ " ዞኑ ከነበሩት 33 አምቡላንሶች አሁን ላይ 9 አምቡላንሶች ብቻ ነው ያሉት። … የህፃናትና የእናቶች የህክምና አገልግሎት አደጋ ውስጥ ነው " - የዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ፦ * የመድኃኒት፣ * የትራንስፖርት፣ * የሕክምና መሣሪያዎች እጥረት በማጋጠሙ በዞኑ የሚገኙ የሕክምና ተቋማት አገልግሎት ለመስጠት ፈተና እንደሆነባቸው በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሄረሰብ…
#ዋግኽምራ

" ድርቁ በጣም እየባሰ ነው። መታከም ያለባቸው ህፃናት ለተከታታይ 2 ወራት ምንም አልተደረገላቸውም" - ዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ

በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ በዞኑ ስላሉ አሳሳቢ ጉዳዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

- ድርቁ በጣም #እየባሰ ነው። ባለፈው ጥናት ካጠናን በኋላ ሊደረግ የሚገባው ግን ያልተደረገ በጣም በስፋት ነው ያለው።

- የምግብ እጥረት እንዳለባቸው በተረጋገጠው መሠረት #ህፃናት #ነፍሰጡር#አጥቢ እናቶች ወደ ተለያዩ ፕሮግራሞች ገብተው ሊደገፉ ነበር። እስቲል ማሟያ ምግብ በምንለው እጥረት እስካሁን ምንም  አልተደረገላቸውም። እኛ #እየጮህን ነው። እስካሁን የመጣ፣ የተደረገ ድጋፍም የለም።

- በሌላ በኩል ድርቅ በተከሰተባችው አካባቢዎች አጠቃላይ የጤና መድህን የምንለው ፕሮግራም የአመት ክፍያው የሚያልቀው አሁን ነው። አልፎ ለማስከፈልም አልቻልንም። በጠቅላላ የጤና አገልግሎታቸው በጣም #የሚያሳዝን ሁኔታ እየገባንበት ያለንበት ሁኔታ ነው ያለው።

ምን ያህል ህፃናትና እናቶች ናቸው አሁን አስቸኳይ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው? 

* በድርቅ የተጎዱት ወደ 33,000 የሚሆኑ ሰዎች ናቸው ከአንድ ወረዳ ብቻ። በአጠቃላይ እንደ ዞን በዚህ ድርቅ ተጎድተዋል ብለን የምናስባቸው ከ180,000 በላይ ህዝቦች ናቸው። 

* ከእዚህ ውስጥ የሚበዙት ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች ናቸው። ወደ 7,000 ይደርሳሉ #ነፍሰጡርና አጥቢዎች ብቻ። ከአምስት ዓመት በታች #ህፃናት ኦልሞስት ወደ #18,000 አካባቢ ይደርሳሉ። እነዚህ ሁሉ አስቸኳይ ምግብ የሚፈልጉ ናቸው።

አቶ አሰፋ ታጣቂዎችን በተመለከተ ምን አሉ ?

° ታጣቂዎች የመጀመሪያ ታርጌታቸው ጤና ተቋማትን መዝርፍ ነው። እኛ አገልግሎት ላለማቋረጥ እየታገልን ነው እንጂ እስካሁን 3 የሚደርሱ ጤና ጣቢያዎች፣ ወደ 12 የሚደርሱ ጤና ኬላዎች አሁንም በየቀኑ በታጣቂ ኃይሎች ይዘረፋሉ።

° መጀመሪያ በስፋት #ፕላምፕሌት አልሚ ምግቦችን ሲወስዱ ነበር። እነርሱ ምግቦች ለሕፃናትና ለእናቶች ካልደረሱ ወደዛ መውሰድ አስፈላጊ አይደለም ብለን  ስናስቆማቸው ጤና ኤክስቴሽኖችን እናንተ ናችሁ የደበቃችሁት አምጡ አስልኩ አይነት ነገር ማስፈራሪያ፣ ዛቻ፣ ድብደባዎች እያደረሱ ነው።

° ጋዝጊቭላና ድሀና ወረዳዎች አዚላ የሚባል ክላስተር አለ፣ በዚያ ስር ያሉ ጤና ኬላዎች፣ በጋዝጊብላ ወረዳ ደግሞ አዱፍቃ፣ አርካ ጤና ጣቢያዎች ስር ባሉ ጤና ኬላዎች ላይ ነው እንግልት እየተደረገ ያለው።

° የጤና አገልግሎቱ እየተቆራረጠ ነው። በቋሚነት እየተሰጠ አይደለም። ከአንድ እስከ ሶስት ቀናት በተከታታይ ይሰጣል። ከሆነ ጊዜ በኋላ ይመጡና እደገና ያቋርጡታል። ኮሚዩኒቲ ሰርቪስ የምንለው በጤና ኬላ ደረጃ የሚሰጠው ኦልሞስት እየቆመ ነው። 

ለመፍትሄው ከማን ምን ይጠበቃል?

☑️ የአጋር ድርጅት ድጋፍ የተቀዛቀዘ ነው። ድጋፍ ማድረግ ቢችሉ የሰዎችን ሕይወት ይታደጋሉ። ከጸጥታው  ጋር ተያይዞ ሊሆን ይችላል ኤኒይወይስ ስለ ረሀብ ደግሞም ስለ ህፃናት፣ ነፍሰጡር አጥቢ እናቶች ረሃብ ነው እያወራን ያለነው። 

☑️ አይደለም እንደዚህ ድርቅ ተከስቶ አፍጦ መጥቶ ኖርማል በመደበኛ ሁኔታ እንኳ እንደዚህ ለይተናቸው የምግብ እጥረት እንዳለባቸው ሲታወቅ ወዲያውኑ ወደ ፕሮግራም ገብተው መታከም ያለባቸው ህፃናት ለተከታታይ 2 ወራት ምንም አልተደረገላቸውም።

ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
“ ከተጎጂዎች መካከል 30,427 ህፃናት ናቸው። የሟቾች ቁጥር ከ40 በላይ ደርሷል ” - ሴቭ ዘ ቺልድረን በሶማሌ ክልል ከተከሰተ የወራት ያለፈው የጎርፍ አደጋ የውሃ መጠኑ እየቀነሰ የመጣ ቢሆንም ትንበያዎች የሚያመለክቱት በመጪው የዝናብ ወቅት ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት እንዲሚችል ስለሆነ፣ ህብረተሰቡም አሁንም ካለፈው የጎርፍ አደጋ ገና እያገገመ በመሆኑ፣ ትልቅ ፈተናና ስጋት መፍጠሩን በቦታው የሚገኘው…
#SavetheChildren

“ በሚያሳዝን ሁኔታ 70 ሰዎች በኮሌራ ሕይወታቸውን አጥተዋል። 9 ሰዎች በኩፍኝ ሞተዋል ” - የህጻናት አድን ድርጅት

በሶማሌ ክልል በተለይም #የጎርፍ_አደጋ በደረሰባቸው ወረዳዎች በተፈናቀሉ ወገኖች የተከሰተ የኮሌራ ወረርሽኝ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሆነ የክልሉ የህጻናት አድን ድርጅት (Save the children) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የድርጅቱ ምሥራቅ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ አብዲራዛቅ አህመድ ፣ የኮሌራ ወረርሽኙ እንደቀጠለ መሆኑን በሴፕተምበር 2023 ወረርሽኙ ከተከሰተ ጀምሮ በድምሩ 7, 480 ሰዎች እንደተጎዱ ገልጸዋል።

ዳይሬክተሩ በሰጡት ቃል፣ “ በሚያሳዝን ሁኔታ 70 ሰዎች በኮሌራ ሕይወታቸውን አጥተዋል። 9 ሰዎች ደግሞ በኩፍኝ ሞተዋል ” ብለዋል።

በተጨማሪም ከ2024 መጀመሪያ ጀምሮ 533 ሰዎች በኩፍኝ በሽታ እንደተያዙ፣ 9ኙ ሰዎች ለሞት የተዳረጉት በጎዴ ከተማ፣ ጎዴ ወረዳ፣ በራኖ አካባቢዎች መሆኑን አስረድተዋል።

ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ምንድናቸው ?

📣 በጎርፍ ለተጎዳ ማህበረሰብ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚደረግ ምላሽ፣ የአደጋ ጊዜ መጠለያ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ድጋፍ ለማደረግ አቅርቦቶችን ማጎልበት። የኮሌራ ክትባቶች ከፍተኛ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ላሉ የህብረተሰብ ክፍሎች መስጠት ይገባል።

📣 የጎርፍ መጥለቅለቅ፣ መሠረታዊ እና አስፈላጊ የጤና አገልግሎቶችን ለማቅረብ ወሳኝ በሆኑ የጤና ተቋማት ላይ ጉዳት እንዳደረሰ በመገንዘብ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የጤና መሠረተ ልማት ግንባታ ላይ መዋዕለ ነዋይ ሊፈስ ይገባል።

📣 #ህፃናት በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በመሆናቸው ልዩ እንክብካቤ ያስፈልጋቸዋል። 

#ጥሪ

(አቶ አብዲራዛቅ አህመድ)

" ለለጋሽ ማህበረሰቡ አንድ ጥሪ ማቅረብ እፈልጋለሁ። ወረርሽኝ እና ተደጋጋሚ የጎርፍ መጥለቅለቅ የሚያመጣውን ከፍተኛ ጉዳትና ተጽዕኖ ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመቀነስ የገንዘብ ድጋፍ ያስፈልጋል። "

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia