TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሀሰተኛ መረጃ‼️

አርቲስት #ኤፍሬም_ታምሩ ከጀርመን ራድዮ ጋር ቃለ ምልልስ አላደረገም። ሰሞኑን በማኅበራዊ መገናኛ ብዙሃን አርቲስት ኤፍሬም ታምሩ ከጀርመን ራድዮ ጋር ቃለ ምልልስ አድርጓል በሚል የተሰራጨዉ መረጃ #የተሳሳተ ነዉ።

አርቲስቱ በምንም ዓይነት ጉዳይ ላይ ከጀርመን ራድዮ ጋር በቅርቡ ቃለ ምልልስ ያልሰጠ መሆኑን የዝግጅት ክፍሉ ገልጿል። አርቲስት ኤፍሬም #የአገውን_ሕዝብ አስመልክቶ ሰጠ የተባለዉ መረጃ የጀርመን ራድዮ በሚያሰራጫቸዉ የሬዲዮ፣ የፌስ ቡክ፣ የዋትስ አፕ እና የቲዩተር ገጾች ላይ ፈፅሞ ያልቀረበ መሆኑንም አድማጮች ተከታታዮች እንዲረዱለት አሳስቧል።

Via ዶቼ ቨለ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የተሳሳተ ፎቶ ነው‼️

በሶሻል ሚድያ ላይ የካፒቴን #ያሬድ_ጌታቸው #እጮኛ እየተባለ በፎቶ የተለቀቀው ሁሉ #የተሳሳተ መረጃ ነው። ቤተሰቡም ሆነ ጏደኞቹ የሚያውቋት እጮኛው ካፒቴን #ቃልኪዳን ትባላለች።

(ከካፒቴን ያሬድ የቅርብ ጓደኛ የተላከልኝ!)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ‼️

የኢትዮጵያ አየር መንገድ #አብራሪዎቹን ለማሰልጠን የሚያስችሉ የተሟሉ ሰባት ምስለ በረራዎች ወይም የበረራ ማሰልጠኛዎች አሉት።

•በአሁን ወቅት ብቁና የተሟሉ ኪው 400፣ ቢ737 ኤን ጂ፣ ቢ 737 ማክስ፣ ቢ 767 ፣ ቢ 787 ፣ ቢ 777 እና ኤ 350 የተሰኙ ሰባት ምስለ በረራዎች አሉት።

•በዋሽንግተን ፓስት የወጣው መረጃ በመረጃ ላይ ያልተደገፈና #የተሳሳተ ነው።

•ማነነታቸው ካልታወቁ አካላት ተገኙ ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ በአለም አቀፍ ደረጃ ከበረራ ስለታገደው #ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን ትኩረት ለማስቀየር ነው፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ባለቤት...

ባሳለፍነው ሳምንት የሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ባለቤት የ11.3 ሚሊዮን ብር የፍትሐ ብሔር ክስ ተመሠረተባቸው ተብሎ የተሰራጨው ዜና #የተሳሳተ መረጃ ነው ሲል የናፍያድ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ህዝብ ግንኙነት ክፍል ገለፀ፡፡

እንደ ተቋሙ ገለፃ የተቋሙ ባለቤት #ናፍያድ_ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በሚል ድርጅት ስም በከፈቱት አካውንት ከሳሽ ለተባሉት አቶ አንተነህ ዘለቀ ምንም አይነት ቼክ እንዳልሰጡ እና ከግለሰቡ ጋርም በስራ ዘርፍም ሆነ በሌላ ጉዳይ የማይገናኙ እንደሆኑ ጠቅሶ ተሰጠ የተባለው ቁጥሩ ኤ 4178436 የሆነ ቼክ መሰረቁን ቀደም ተብሎ ለፖሊስ ሪፖርት እንዳደረገ ገልጾአል።

በጉዳዩ ላይ ክስ ተመስርቶ እየታየ እንደነበር የገለፀው የህዝብ ግንኙነት ክፍሉ ለዚህም ድርጅቱ ከሚገኝበት ከኦሮምያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የአዳማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ፖሊስ የደረሰበትን ውጤት የሚያሳይ ለተቋሙ የተፃፈን ደብዳቤን አቅርቧል፡፡

ፖሊስ ቁጥሩ ኤ 4178436 የሆነ ቼክ ከወጋገን ባንክ አዳማ ቅርንጫፍ ስለመሰረቁ በተመለከተ እየተደረገ ስላለው የወንጀል ምርመራ በሚመለከት የፃፈው ደብዳቤ ጉዳዩ ላይ ምርመራ እያደረገ መሆኑንም ይጠቁማል፡፡

"በዚህ ጉዳይ ከሳሽ ነኝ ያሉት አቶ አንተነህ ዘለቀ የተባሉት ግለሰብ በጠፋው ቼክ ጉዳይ ተጠርጥረው በአዲስ አበባ ፖሊስ እና በኦሮምያ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩ እና በዋስ መብት የተለቀቀቁ" ናቸው ያለው የህዝብ ግኝኑነት ክፍሉ “ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮኃል እንዲሉ በተገላቢጦሽ ግለሰቡ ከሳሽ ሆኖ መቅረባቸው አስገራሚ ሆኖብናል” ያለ ሲሆን ጉዳዩ በህግ የተያዘ መሆኑን አስታውሶ "ክሱ ሆን ተብሎ የድርጅቱን ባለቤት እና የተቋሙን መልካም ስም ለማጉደፍ የተቀናባበረ" መሆኑንም ጠቅሷል፡፡

Via ሸገር ታይምስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጦላይ ማሰልጠኛ ጣቢያ ሥልጠና ላይ ያሉ ከ150 በላይ የኦነግ የቀድሞ ታጣቂዎች መመረዛቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ችግሩ የተከሰተው ትናንት በቁርስ ሰዓት በሚጠጡት ሻይ ነው፡፡ 129ኙ ትናንቱን ለሕክምና ወሊሶ ሆስፒታል የገቡ ሲሆን 20ዎቹ ደሞ ዛሬ እንደገቡ የሆስፒታሉን ሐኪም ተናግረዋል፡፡ አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት እንደታየባቸውም ተገልጧል፡፡ የኦሮሚያ ክልል ኮምኒኬሽን ቢሮ ዛሬ ከቀትር በኋላ ባወጣው መግለጫ ሁሉም ታማሚዎች በጥሩ ጤንነት ሁኔታ እንደሚገኙ ኢቢሲ ዘግቧል፡፡ የህመማቸው መንስዔ እየተጣራ ቢሆንም የምግብ መመረዝ እንደሆነ የተወራው ግን #የተሳሳተ መረጃ ነው ሲል አስተባብሏል፡፡

በተያያዘ ዜና ...

ዛሬ ማለዳ የወሊሶ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸውን ሪፖርተር አስነብቧል፡፡ የአድማው መንስዔ ጦላይ ማሰልጠኛ ጣቢያ ያሉ የኦነግ የቀድሞ ታጣቂዎች ተመርዘዋል የሚል ዜና መሰራጨቱ ነው፡፡ በአድማው ሳቢያ ከወሊሶ-አዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ-ወሊሶ የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጧል፡፡ ወጣቶች መንገዱንም ዘግተዋል፡፡ በከተማዋ የመንግሥት ተቋማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ሰጭ ተቋማትም አገልግሎታቸውን አቋርጠዋል፡፡

Via #BBC(#WAZEMA)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
37 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ‼️

ባለፈው #ቅዳሜ በደቡብ ፖሊስና በወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለቦች መካከል ሊካሄድ በነበረው ጨዋታ ላይ #ግጭት እንዲፈጠር በማነሳሳት የተጠረጠሩ 37 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጉዳዮች መምሪያ ሃላፊ አቶ ደስታ ዳንጊሶ ጉዳዩን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።

ሃላፊው በመግለጫቸው የራሳቸውን ፖለቲካዊ አጀንዳ የሚያራምዱ አካላት በሸረቡት ሴራ በዕለቱ በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።

በተፈጠረው ግጭትም በአንዲት ሴት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባት ሆስፒታል እንደምትገኝና 17 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል።

ከዚህ ባለፈም የ10 መኪናዎች መስታወት ሙሉ በሙሉ የተሰባበረ ሲሆን ፥ አንድ ግሮሰሪ ላይም ዘረፋ ተፈጽሟል ነው ያሉት።

ግጭቱ የከፋ ጉዳት ከማድረሱ በፊት የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎችና የፀጥታ አካላት በመቀናጀት ባደረጉት ርብርብ በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉንም አንስተዋል።

ስለሆነም መገናኛ ብዙሃን የተከሰተውን ችግር ከማጋነንና #የተሳሳተ መረጃ ከማሰራጨት #እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽንም ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ በደቡብ ፖሊስና በወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለቦች መካከል የሚደረገውን ጨዋታ ጨምሮ ሀዋሳ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ጋር የሚያደርጉትን ጨዋታ ላልተወሰነ ጊዜ ማራዘሙ ታውቋል።

Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNews "ይህ መረጃ ፈፅሞ #የተሳሳተ እንደሆነ እንገልፃለን።" የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር!

#share #ሼር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

#የተሳሳተ_ዜና_ጥቆማ - #MisinformationAlert
ዛሬ መስከረም 27 ቀን 2012 ዓ.ም “የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የፓለቲካ ፓርቲዎች ሊያደርጉት የነበረው ውይይት ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ” በሚል ርእስ በኢትዮጵያ ብርድካስቲንግ ኮርፓሬሽን ፌስቡክ ገጽ የተዘገበው ዜና የተሳሳተ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለማሳወቅ ይወዳል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬ እለት ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ያደረገው ምንም አይነት ውይይትም ሆነ ድርድር ያላደረገ ሲሆን የኢቢሲም ሆነ የኢቢሲን ዜና መሰረት በማድረግ የዘገቡ ሌሎች ሚዲያዎች ዜናዎችን ከማሰራጨታቸው በፊት ማጣራት እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳስባል፡፡ ቦርዱ ማንኛውንም የመረጃ ጥያቄዎች ለመመለስ ዝግጁ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለመግለጽ ይወዳል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse

ኮሮና ቫይረስ ሁሉንም የእድሜ ክልል ነው የሚያጠቃው!

(በዶክተር ሊያ ታደሰ - የጤና ሚኒስትር)

በሀገራችን በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎችን የእድሜ ስብጥር ብንመለከት እስካሁን በቫይረሱ ከተያዙት 272 ሰዎች ከህፃናት እስከ አረጋዊያን ድረስ በሁሉም የእድሜ ክልል ያሉ ተይዘዋል።

ትልቁ ቁጥር 99 ሰዎች ከ15-24 የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ናቸው ፤ ከዛ የሚቀጥለው ከ25-34 የእድሜ ክልል ውስጥ (75 ሰዎች) የሚገኙ ሲሆን ከ60 ዓመት በላይ የሆኑ ሰዎች ቁጥርም 19 ነው። በህፃናት ላይ አነስተኛ ቁጥር ቢታይም ህፃናትም በሽታው እንደሚይዛቸው ያሳያል።

ይህ በሽታ የማያጠቃው የእድሜ ክልል የለም። በዓለም አቀፍ ደረጃ #ወጣቶች አይጠቁም የሚል #የተሳሳተ ግንዛቤ አለ ፤ በተለይ በእኛ ሀገር ያለው ስርጭት ትልቁ ቁጥር በወጣቶች ላይ የታየ ነው። ስለዚህ እያንዳንዳችን የምንወስደው ጥንቃቄ እጅግ አስፈላጊ ነው።

የዚህ በሽታ ስርጭት #እየጨመረ የሚሄድ ሊሆን ቢችልም ምን ያህል ይጨምራል የሚለውን የምንወስነው በየዕለቱ በምንወስናቸው ውሳኔዎች ፣ በየዕለቱ በምንመርጣቸው ምርጫዎች እንዲሁም በምንወስዳቸው እርምጃዎች ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መንግስት በኮቪድ-19 ዙሪያ እርምጃዎችን እያላላ ነው ?

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ባስተላለፉት መልዕክት በቅርቡ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መመሪያው ላይ የተደረጉት ማሻሻያዎች መንግስት በኮቪድ-19 ዙሪያ እርምጃዎችን እያላላ ነው የሚል #የተሳሳተ ግንዛቤ በማህበረሰቡ ውስጥ እየተሰራጨ እንደሆነ ተናግረዋል።

ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ማሻሻያዎቹ የተደረጉት በሀገር አቀፍ ደረጃ ወረርሽኙ #እየጨመረ በመምጣቱ መንግስት ያለውን ውስን ሃብት የት ላይ ማፍሰስ አለበት የሚል ለወረርሽኙ ምላሽ የስትራቴጂክ ለውጥ አስፈላጊ በመሆኑና ይበልጥ ለወረርሽኙ ጠንከር ያለ ምላሽ ለመስጠት የተደረጉ እንጂ እርምጃዎችን የማላለት እቅድ እንደሌለ አስገንዝበዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbabaPolice

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በአራዳ ክፍለ ከተማ በልመና ስራ በሚተዳደሩ አንዲት ግለሰብ ቤት ውስጥ ከ45 ሺህ ብር በላይ መገኘቱን ገለፀ፡፡

በአ/አ "በርሜል ሙሉ ገንዘብ ተከማችቶ ተገኘ" በሚል በተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች እየተላለፈ ያለው መረጃ #የተሳሳተ መሆኑን ኮሚሽኑ አስታዉቋል፡፡

* የአ/አ ፖሊስ ኮሚሽን በጉዳዩ ዙሪያ የሰጠው ዝርዝር መረጃ ከፎቶ ጋር ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#የተሳሳተ_መረጃ

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ዛሬ ETHIO FM የኮሚሽኑ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ሃላፊ የሆኑት ም/ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ ገልፀዋል በሚል '38 የህውሓት አመራሮች በቁጥጥር ስር ውለዋል' ሲል ያስተላለፈው መረጃ ሐሰት እና በም/ኮሚሽነር ጀነራሉ ያልተላለፈ መሆኑን አሳወቀ።

ተያዙ በሚል ሃላፊው የገለፁትም በመከላከያ ውስጥ የግንኙነት መስመር ያቋረጡና ከዚህ ድርጊት ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ ሜጀር ጀነራል ገብረመድህን ፍቃዱን (ወዲ ነጮን) ጨምሮ 38 ግለሰቦች ፍርድ ቤት ስለመቅረባቸው ነው።

በህግ ከሚፈለጉት የህወሓት ቡድን አባላት እስከአሁን የተያዙ አለመኖራቸው ታውቆ ሌሎች ሚዲያዎችም ይህንን "የተዛባ መረጃ" ለህበረተሰቡ ከማሰራጨት እንዲቆጠቡ የፌዴራል ፖሊስ #በጥብቅ አሳስቧል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#ምርጫ2013_እና_አዲስአበባ

ማንነታቸው የማይታወቁ ጣቢያዎች ተከፍተው ነበር ? (ባልደራስ ፓርቲ ያቀረበው ቅሬታ)

ወ/ሪት ሶሊያና : ፍፁም ሀሰት ነው። አዲስ አበባ ላይ ማንነታቸው የማይታወቁ ጣቢያዎች የሉንም። ሁሉም ጣቢያዎች ኮድ አላቸው፤ ኮድ የሌላቸው ያገኘናቸው 2 ጣቢያዎችን እንኳን ድጋሚ ኮድ ሰጥተን ምርጫ እንዲካሄድ አድርገናል።

አንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች የባልደራስ ፓርቲን ውጤት እያሳነሱ እንዲፅፉ ተደርገዋል ? (የባልደራስ ፓርቲ ቅሬታ)

ወ/ሪት ሶሊያና : ይህ ፍፁም ሀሰት ነው። ፓርቲ ወኪሎች ያሉባቸው ቦታዎች ከሆኑ የፓርቲ ወኪሎቻቸው እራሳቸው ይህን አይተው ዝም አይሉም። ወኪሎቹ እራሳቸው እንደዚህ ያለ አቤቱታ አቅርበው (በእኔ ፓርቲ ላይ ያለው ውጤት በትክክል አልተቆጠረም/በትክክል አልተፃፈም ብለው) ያቀረቡት ሪፖርት የለም። ያን አይነት አቤቱታ የቀረበበት የምርጫ ጣቢያም የለንም።

በወረቀት እጥረት የተነሳ ደጋፊዎቻችን ወደቤቶቻቸው ሄደዋል ተብሎ ስለተነሳው ቅሬታ ?

ወ/ሪት ሶሊያና : እስከ ለሊቱ 7 ሰዓት ከ10 ድረስ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት አከናውነናል። የድምፅ መስጫ ወረቀት ባለመኖሩ የተቋረጠብን ምርጫ ጣቢያ የለም። ምርጫ ጣቢያዎች ላይ የድምፅ መስጫ ወረቀት እጥረት ነበር ነገር ግን ባለው እያካሄዱ እያለ ተጨማሪ ወረቀቶችን ማድረስ ችለናል። ስለዚህ መሰረታዊ የሆነ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ተቋርጦ የድምፅ መሥጫ ወረቀት ባለመኖሩ የተነሳ ሰው ተበትኖ/ተመልሶ ኑ ወረቀት መጥቷል እና ድምፃችሁን ስጡ የተባለበት አንድም ቦታ የለም፤ ስለዚህ ወረቀት አልቆ ደጋፊዎቼ ተመለሱ የሚለው በከፍተኛ ደረጃ #የተሳሳተ መረጃ ነው።

ይቀጥላል👇
animation.gif
7.9 KB
" ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስናትን ድንበር አልዘጋችም " - የኬንያ ፖሊስ አገልግሎት

‘Citizen TV’ የተባለው የኬንያ ቴሌቪዝን ጣቢያ በትናንትናው ዕለት “ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስናትን ድንበር ዘጋች” የሚል መረጃ አስረጭቶ ነበር። የቴሌቪዥን ጣቢያው ኬንያ ከ800 ኪሎሜትር በላይ የሚረዝመውን የሁለቱን ሀገራት ድንበር ላልተወሰነ ጊዜ መዝጋቷን ለዘገበበት ዜና ምንጭ አልጠቀሰም።

የኬንያ ፖሊስ አገልግሎት (Kenya Police Service) ዛሬ እንዳስታወቀው የኬንያ-ኢትዮጵያ ድንበር መዝጋቱን በተመለከተ በሚዲያ የተሰራጨው መልዕክት #የተሳሳተ መሆኑን አስታውቋል።

“አንዳንድ ሚዲያዎች በተሳሳተ መንገድ እንደዘገቡት ሳይሆን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስነው ድንበር አልተዘጋም” ያለው የኬንያ ፖሊስ “ያደረግነው በድንበር አካባቢ ያለውን የጸጥታ ቁመናችንን ማጠናከር ነው” ሲል አብራርቷል። የኬንያ ፖሊስ በተጨማሪም በድንበር አካባቢ ያለው ሁኔታ የተረጋጋ መሆኑን ገልጿል።

የኬኒያ ፖሊስ በትናንትናው ዕለት “አጎራባች” ባላቸው ሀገሮች እየታዩ ነው ካላቸው የጸጥታ ሁኔታዎች አኳያ አምስት ነጥቦችን የያዘ መግለጫ አውጥቶ የነበረ ሲሆን ከነጥቦቹ መካከል በድንበር አካባቢ የጸጥታ ቁጥጥርን ማጠናከር የሚል ይገኝበታል።

Credit : ኢትዮጵያ ቼክ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ትምህርት የሚጀምረው መስከረም 7 ነው " - የአ/አ ትምህርት ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት የፊታችን ሰኞ መስከረም 7 /01/2016 ዓ.ም በሁሉም ትምህርት ተቋማት እንደሚጀምር አስታወቀ።

ቢሮው ይህን ያሳወቀው የትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ/ም የትምህርት ካላንደርን ለህዝብ ካሰራጨ በኃላ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባወጣው አጭር መልዕክት ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ፤ " የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት መስከረም 14 /1/2016 ዓ.ም እንደሚጀመር በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ #የተሳሳተ ነው " ብሏል።

ቢሮው በየትኞቹ የማህበራዊ ሚዲያዎች የተሳሳተ መረጃ እንደተሰራጨ በግልፅ አላሰፈረም።

የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ቅዳሜ በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ይፋ ባደረገው የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት #ሀገር_አቀፍ የትምህርት ካላንደር መሰረት ከመስረም 7 እስከ 11/2016 ዓ/ም ድረስ የትምህርት ሳምንት ሆኖ ይከበራል ብሏል።

መስከረም 14 ደግሞ የአንደኛ ሴሚስተር መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት እንደሚጀምር አሳውቋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ካላንደሩ ላይ ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ #የተወሰኑ የቀናት ለውጦች ሊያደርጉ እንደሚችሉ ታሳቢ ይደረግ ብሏል።

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ከዚህ ቀደም ይፋ ባደረገው መሰረት የ2016 ዓ/ም ትምህርት ሰኞ መስከረም 7 ቀን 2016 ዓ/ም በሁሉም ተቋም እንደሚጀምር #አስረግጦ ተናግሯል ፤ መላው የትምህርት ማህበረሰብ ይህን እንዲያውቀው ብሏል።

ከቀናት በፊት የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ/ም የትምህርት መስከረም 7/2016 ዓ/ም እንደሚጀምር ማሳወቁን መዘገባችን ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአማራ ክልል የሚገኙ የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዜዳንቶች በቅርቡ ከክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ አኳያ የመማር ማስተማር ሂደትን ማስቀጠል ይቻል እንደሆነ ውይይት እንዳደረጉ ቪኦኤ ዘግቧል። የክልሉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ዋና ፀሀፊ ዶ/ር አስማረ ደጀን ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል፤ የዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዜዳንቶች ባደረጉት ውይይት ወቅታዊው የክልሉ የፀጥታ ችግር በቅርቡ ተማሪዎችን ተቀብሎ…
#Amhara

በአማራ ክልል የሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ዋና ጸሐፊ ዶ/ር አስማረ ደጀን፤ የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎችን አቋም በተመለከተ በማኅበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር የነበረው መረጃ " #የተሳሳተ ነው " አሉ።

ከሰሞኑን በአማራ ክልል ስላሉ ዩኒቨርሲቲዎች ምንድነው የተባለው ?

ከቀናት በፊት ቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ የፎረሙን ዋና ጸሐፊ የሆኑትን ዶ/ር አስማረ ደጀንን ዋቢ በማድረግ ባወጣውና ቲክቫህ ኢትዮጵያም ባጋራው ዘገባ ፤ በአማራ ክልል የሚገኙ የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዝዳንቶች ከክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ አኳያ የመማር ማስተማር ሂደትን ማስቀጠል ይቻል እንደሆነ ውይይት ካደረጉ በኃላ ሁኔታው #በቅርቡ ተማሪዎችን ተቀብሎ የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማስቀጠል የሚያስችል እንዳልሆነ የጋራ መግባባት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል።

በተጨማሪ ዶ/ር አስማረ ደጀን ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል፤
*  ተማሪዎች ገብተው ግጭቶች በሚመጡበት ጊዜ ዩኒቨርሲቲዎች ኃላፊነት እንደማይወስዱ፤

* ዩኒቨርሲቲዎች ለ2016 የሚሆን የምግብ አቅርቦት ማዘጋጀት የነበረባቸው ቢሆንም አቅራቢዎቹ ከቦታ ቦታ ፤ ምርት ካለበት ቦታ ሄደው ተዘዋውረው መግዛት ስላልቻሉ የምግብ ግብአቶች በጠቅላላው ተማሪን ሊያስጠራ የሚችል እንዳልሆነ ገልፀዋል።

ፎረሙ ትምህርት ሚኒስቴር " ለ2016 ትምህርት በአሁን ሰዓት ተማሪዎችን ጥሩ እያለ ነው " ብሎ ለፀጥታው ኃላፊነት የሚወስድ አካል ከሌለ ይህን ማድረግ #እንደሚያስቸግር ነው የገለፀው።

ከዚህ ባለፈ የፎረሙ አባልና የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ታፈረ መላኩ፤ በአካባቢው የቀጠለው አለመረጋጋት ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ እንደማያስችል ከተስማሙት የፎረሙ አባላት እንደሆኑ ገልጸዋል።

ያለው ሁኔታ ካልተሻሻለ በስተቀር አሁን ባለው ሀገራዊ ሁኔታ ላይ ግቢ ውስጥ ተማሪ ማስገባት በእጅጉ ፈታኝ እንደሚሆንና ለልጆችም ደህንነት በጣም አስጊ መሆኑን ፕሬዜዳንቱ ለጣቢያው ተናግረዋል።

ይህ መረጃ ከተሰራጨ ከቀናት በኃላ የፎረሙ ዋና ጸሐፊ ዶ/ር አስማረ ደጀን ለአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዛሬ በሰጡት ቃል " ሰሞኑን የተሰራጨው መረጃ በአማራ ክልል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ያልተባለና ስህተት ነው " ብለዋል።

በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን ለመቀበል አመች ሁኔታዎችን እየተጠባበቁ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

በክልሉ የሚገኙ አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን መጥራት መጀመራቸውንም ገልጸው፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ጥሪ ማስተላለፉን ለአብነት አንስተዋል፡፡

"አብዛኞቹ በክልሉ ውስጥ የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሁለተኛ እና የሦስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን እየጠሩ ነው" ያሉ ሲሆን " ብዙ ተማሪዎችን በአንድ ጊዜ ለመጥራት ግን የግብዓት ችግር ለተቋማቱ እንቅፋት ሆኗል " ብለዋል።

ዶ/ር አስማረ፤ በክልሉ በተፈጠረው የሰላም እጦት ግብዓት አቅራቢዎች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው ለማቅረብ የተቸገሩ ቢሆንም ዩኒቨርሲቲዎች የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየሠሩ መሆኑን አሳውቀዋል። በየአካባቢው ያሉ አቅራቢዎች ግብዓት እንዲያቀርቡ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ትምህርት ሚኒስቴር ተማሪዎችን ተቀበሉ በሚልበት ጊዜ የማይቀበሉበት ምክንያት እንደሌለም ገልጸዋል።

" ክልሉ ያጋጠመው የጸጥታ ችግር እየተሻሻለ ከመጣ ተቋማቱ ተማሪዎቻቸውን ወዲያው ይጠራሉ፤ ተማሪዎችን አይጠሩም የተባለው ስህተት ነው፤ አልተባለምም " ሲሉ ተናግረዋል።

አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ግብዓት ለማግኘት ከመቸገራቸው ውጭ የመማሪያ ክፍሎችን አጽድተዋል፣እድሳት የሚያስፈልጋቸውንም አድሰው ለትምህርት ዘመኑ የመማር ማስተማር ዝግጁ ሆነዋል ሲሉ ለክልሉ ሚዲያ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia