TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#FightCOVID19

ከኖህ ሪልስቴት የተላከልን መልዕክት ፦

ኖህ ሪልስቴት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመግታት የሚደረገው ጥረት የሁሉንም ትብብር የሚጠይቅ መሆኑ አጥብቆ እንደሚያምን ገልፆ ይህን አስከፊ በሽታ ለመግታት ከመንግስትና ከህዝብ ጎን ሆኖ እንደሚሰራ አሳውቋል።

በዛሬው ዕለት ኖህ ሪልስቴት በመንግስት እየተደረገ ያለውን ጥረት ለማገዝ እና ሀገራዊ ግዴታውን ለመወጣት ከተጠናቀቁና ለርክክብ ዝግጁ ከሆኑት ፕሮጀክቶች መካከል 'ኖህ ፊጋን' ለኳራንታይ እንዲሆን አስረክቧል።

ይህኛው የኖህ ሪልስቴት ሳይት አጠቀላይ የወለል ስፋቱ 9,200 ስኩ.ሜትር ሲሆን 48 የመኖሪያ አፓርትመንቶች አሉት። እያንዳንዳቸውም 184 ስኩዌር ሜትር ባለ አራት መኝታ ክፍሎችን ከሶስት መፀዳጃ ቤቶች ፣ ኪችን ካቢኔት እና ቁምሳጥን የያዘ ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FightCOVID19

- መርካቶ ውስጥ የሚገኘው የአንፀባራቂ ኮከብ ሕንፃ ውስጥ ተከራይተው ለሚገኙ 76 ነጋዴዎች አክሲዮን ማህበሩ የሚያዝያ ወር ወርሀዊ ኪራይ ነፃ ማድረጉን አክሲዮን ማህበሩ ገልጾልናል። በብር 504,730 ይደርሳል።

- የጀቡላኒ መሃል መርካቶ ንግድ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የአንድ ወር የቤት ኪራይ (የሚያዚያ) ነፃ አድርጓል።

- ሀዋሳ 'ሰፈረ ሰላም' የሚገኘው አዲስ የገበያ ማዕከል የሁለት ወር የቤት ኪራይ ነፃ ማድረጉን አሳውቆናል። በገንዘብ 300,000 ብር ይደርሳል።

- አደይ አበባ የሚገኘው የማሜ ህንፃ ባለቤት 'መሃመድ አወል' የአንድ ወር የቤት ኪራይ 50 % ቀንሰዋል።

- ሄልዘር ቢዝነስ ኃ/የተ/የግል/ማህበር በህንፃው ለሚገኙ ሁሉም ተከራዮች ቅናሽ በማድረግ የሁለት ወር (መጋቢት እና ሚያዚያ) የኪራይ ክፍያ ሙሉ በሙሉ እንደማያስከፍል አሳውቋል።

- ፌንድሺፕ የንግድ ማእከል ለ266 ተከራዮች የ3 ወር የኪራይ ክፍያ 50% ቅናሽ አድርጓል። መልዕክቱ ከኢ/ር ታከለ ኡማ የተገኘ ነው።

- 22 አከባቢ የሚገኘው KW የንግድ ማእከል ባለቤት ለ64 ለሚሆኑ ተከራዮች የአንድ ወር የኪራይ ክፍያ ነፃ አድርገዋል። መልዕክቱ ከኢ/ር ታከለ ኡማ የተገኘ ነው።

- Century Mall, የንግድ ማእከል 16.2 ሚልዮን ብር (የ3 ወራት ) የኪራይ ክፍያ 50 % ነፃ አድርገዋል። መልዕክቱ ከኢ/ር ታከለ ኡማ የተገኘ ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FightCOVID19

- ሜክሲኮ የሚገኘው የኬኬር ሕንፃ ባለቤቶች ወ/ሮ አስካል ሀብቴ እና አቶ ሣህሌ ልጋ ከሶስት መቶ ሃምሳ በላይ ለሚሆኑ የግል ድርጅቶች እና ለግል ተከራይ ደንበኞቻቸው የሁለት ወር ኪራይ ነፃ ማድረጋቸውን አረጋግጠናል።

- ሳውዝ ጌት ፕላዛ ለተከራዮቹ የሁለት ወር ኪራይ ነፃ ማድረገን ከኢ/ር ታከለ ኡማ ሰምተናል።

- ኮሜት ህንፃ በህንፃው ላይ ለሚገኙ ተከራዮች (1ሚሊየን ብር) የሚገመት የአንድ ወር ኪራይ ነፃ ማድረጉን ከኢ/ር ታከለ ኡማ ሰምተናል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FightCOVID19

በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክ/ከተማ የሚገኘው ኤም ኤም ዲ /MMD/ ህንፃ ባለቤት ዶክተር ከበደ ከቻራ እና ሲ/ር ንግስት በየነ ህንፃቸውን ለተከራዩት ቅዱስ ያሬድ ሆስፒታል በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የሶስት ወር የህንፃ ኪራይ በግማሽ መቀነሳቸው ተነግሮናል። በገንዘብ ሲተመን ወደ 1,000,000 ብር ይደርሳል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FightCOVID19

የአሶሼትድ ፕሬስ /Associated Press/ ዓለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝን ለመግታት በሚደረገው ጥረት ሀገራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በዛሬው ዕለት ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ40,000 ብር እገዛ ማድረጉን ከኢ/ር ታከለ ኡማ ሰምተናል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FightCOVID19

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ አሳሳ ከተማ የሚገኙ የጤና ባለሞያዎች በዛሬው ዕለት በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ወረርሽኝ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ሲሰሩ መዋላቸውን ገልፀውልናል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FightCOVID19

በጋምቤላ ክልል በተለያዩ የኢንቨስትመንት ስራዎች ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ዲያቆን አልሸሽም ተካ የተባሉ ባለሀብት የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ለሚደረው ጥረት የሚያግዝ 15 የሙቀት መለክያ መሳርያዎችን ድጋፍ አድርገዋል።

(ከጋምቤላ ፕረስ ሴክረታሪያት ጽህፈት ቤት)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FightCOVID19

ከፌም ኢምፔክስ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር (ሴፍ ወይ ሱፐር መርኬት) የተላከ መልዕክት ፦

- በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን ለገዳዲ ለገጣፎ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በዝቅትኛ ኑሮ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ለህፃናት ለአዋቂ የሚሆን የታሽጉ ምግቦች እና የፅዳት እቃ ፣ እገዛ አድርጓል። ዋጋው 105,000.00 ብር በላይ እንደሚሆንም ተነግሮናል።

- በተጨማሪም የድርቅ ጭነት ለማጓጓዝ የሚያገለግል ቫን ተሽከርካሪ ጥሪ በተደረገለት ወቅት የነዳጅ ወጪን በመሸፈን አገልግሎቶች እንዲሰጥ ተውስኗል። የድርጅቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተርም ትእዛዝ አስተላልፈዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FightCOVID19

የኦሮሚያ ክልል የኮሮናቫይረስ [ኮቪድ-19]ን ለመከላከል የሚውል እስካሁን ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዝብ ከተለያዩ አካላት ቃል ተገብቶ ገቢ እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።

በአጠቃላይ እስካሁን የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በክልሉ በአይነትና በጥሬ ገንዘብ  ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መገኘቱን የክልሉ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ገልጿል።
 
የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴው ዛሬ ባካሄደው አራተኛ ዙር የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ላይ ባለኃብቶችና ድርጅቶች 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርገዋል።

(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FightCOVID19

'ፋልከን አካዳሚ' በላከልን መልዕክት በአዲስ አበባ ከተማ በንፋስ ስልክ ወረዳ 09 የሚገኘውን B+G+5 የትምህርት ቤት ሕንፃ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ በማቆያነት እንዲያገለግል ለክፍለ ከተማው አስተዳደር በማስረከብ ማህበራዊ ግዴታውን መወጣቱን አሳውቆናል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia