#FightCOVID19

- መርካቶ ውስጥ የሚገኘው የአንፀባራቂ ኮከብ ሕንፃ ውስጥ ተከራይተው ለሚገኙ 76 ነጋዴዎች አክሲዮን ማህበሩ የሚያዝያ ወር ወርሀዊ ኪራይ ነፃ ማድረጉን አክሲዮን ማህበሩ ገልጾልናል። በብር 504,730 ይደርሳል።

- የጀቡላኒ መሃል መርካቶ ንግድ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የአንድ ወር የቤት ኪራይ (የሚያዚያ) ነፃ አድርጓል።

- ሀዋሳ 'ሰፈረ ሰላም' የሚገኘው አዲስ የገበያ ማዕከል የሁለት ወር የቤት ኪራይ ነፃ ማድረጉን አሳውቆናል። በገንዘብ 300,000 ብር ይደርሳል።

- አደይ አበባ የሚገኘው የማሜ ህንፃ ባለቤት 'መሃመድ አወል' የአንድ ወር የቤት ኪራይ 50 % ቀንሰዋል።

- ሄልዘር ቢዝነስ ኃ/የተ/የግል/ማህበር በህንፃው ለሚገኙ ሁሉም ተከራዮች ቅናሽ በማድረግ የሁለት ወር (መጋቢት እና ሚያዚያ) የኪራይ ክፍያ ሙሉ በሙሉ እንደማያስከፍል አሳውቋል።

- ፌንድሺፕ የንግድ ማእከል ለ266 ተከራዮች የ3 ወር የኪራይ ክፍያ 50% ቅናሽ አድርጓል። መልዕክቱ ከኢ/ር ታከለ ኡማ የተገኘ ነው።

- 22 አከባቢ የሚገኘው KW የንግድ ማእከል ባለቤት ለ64 ለሚሆኑ ተከራዮች የአንድ ወር የኪራይ ክፍያ ነፃ አድርገዋል። መልዕክቱ ከኢ/ር ታከለ ኡማ የተገኘ ነው።

- Century Mall, የንግድ ማእከል 16.2 ሚልዮን ብር (የ3 ወራት ) የኪራይ ክፍያ 50 % ነፃ አድርገዋል። መልዕክቱ ከኢ/ር ታከለ ኡማ የተገኘ ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia