TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Amahara በአማራ ክልል ከሚገኙ ከተሞች አንፃራዊ የሚባል ሰላም እና መረጋጋት የነበራት ባህር ዳር ዛሬ በተለያዩ አካባቢዎች በተኩስ ስትናጥ መዋሏን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ከስፍራው ዘግቧል። ምንም እንኳን ስለደረሰው ጉዳት የሚታወቅ ነገር ባይኖርም ትላንት ማታ ቦምብ የፈነዳ ሲሆን ዛሬ ቅዳሜ ከጥዋት ጀምሮ በተለይ  " ቀበሌ 14 " በሚባለው አካባቢ ላይ መንገዶች ተዘግተው ፤ የንግድና ትራንስፖርት እንቅስቃሴ…
#Amhara

በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች ያለው ውጥረት አሁንም የቀጠለ ሲሆን በተለያዩ ቀጠናዎች ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ስለመኖራቸው ለማወቅ ተችሏል።

በክልሉ ባለው ግጭት እና ፍጥጫ የየብስ እና የአየር ትራንስፖርት ተስተጓጉሏል ፣ የኢንትርኔት አገለግሎት ተቋርጧል፣ አንዳንድ አካባቢዎች በታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ናቸው።

" የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ " ዋና ሰብሳቢ እና የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አግልግሎት ዳይሬክትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ትላንት እሁድ በሰጡት ማብራሪያ፤ በአማራ ክልል የተጣለውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚያስፈጽመው ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ሕግ የማስከበር ሥራውን በማከናወን ክልሉን ወደ መደበኛ እንቅስቃሴው በአጭር ጊዜ እንዲመለስ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።

አቶ ተመስገን ፤ አማራ ክልል የተከሰተው በትጥቅ የታገዘው እንቅስቃሴ " የክልሉን መንግሥት በማፍረስ ወደ ፌደራል መንግሥቱ የሚዞር ግብ ያለው " ነው ብለዋል።

በክልሉ የተለያዩ ክፍሎች ሕገወጥነት ተከስቷል ያሉት ሰብሳቢው ፤ " የተደራጁ ዘራፊ ቡድኖች " ሲሉ የጠሯቸው አካላት በክልሉ ውስጥ የዞን እና የወረዳ ከተሞችን #ተቆጣጥረው የፍትሕ እና የሕዝብ ተቋማት አገልግሎት እንዳይሰጡ ከማስተጓጎል ባሻገር " በአንዳንድ አካባቢዎች ማረሚያ ቤቶችን ሰብረው ወንጀለኞችን እንዲያመልጡ እስከማድረግ የደረሰ ውንብድና ፈጽመዋል " ብለዋል።

በክልሉ ሕግ እና ሥርዓትን ለማስከበር እንዲሁም የመንግሥት እና የፓርቲ መዋቅርን የማጠናከር ሥራዎችን ለማከናወን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ክልሉን በአራት ኮማንድ ፖስቶች ማዋቀሩን አስታውቀዋል።

• የመጀመሪያው የምዕራብ አማራ ኮማንድ ፖስት ፦
- ምሥራቅ እና ምዕራብ ጎጃም
- ደብረ ማርቆስ ከተማ፣
- የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን
- ባሕር ዳር ከተማ ያሉበት ነው።

• ሁለተኛው የሰሜን ምዕራብ አማራ ኮማንድ ፖስት ፦
- ሰሜን፣ ምዕራብ፣ ማዕከላዊ እና ደቡብ ጎንደር
- ጎንደር ከተማ
- ደብረታቦር ከተማ የሚገኙበት ነው።

• ሦስተኛው ኮማንድ ፖስት ማዕከላዊ ሸዋ ፦
-  ሰሜን ሸዋ፣
- የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን
- ደብረ ብርሃን ከተማን ያካተተ ነው።

• አራተኛ የምሥራቅ አማራ ኮማንድ ፖስት ፦
- ኮምቦልቻ እና ወልዲያ ከተሞች - ሰሜን እና ደቡብ ወሎ
- ዋግ ኽምራን ያካተተ መሆኑን የዕዙ ሰብሳቢ ገልጸዋል።

አቶ ተመስገን ፤ በክልሉ ውስጥ የተፈጠረውን ችግር እና የሚነሳ የትኛውንም ጥያቄ መንግሥት #በሰላም_ምላሽ_ማግኘት_አለበት ብሎ በጽኑ እንደሚያምን የገለፁ ሲሆን ሕግ እና ሥርዓት የማስከበሩ ሥራም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በአማራ ክልል ፤ ባለፉት ጥቂት ወራት ተቃውሞና ግጭቶች የነበሩ ሲሆን ከሰሞኑን ግን ግጭቶቹ ተስፋፍተው ወደ ትልልቅ ከተሞች ደርሰዋል።

ከመንግሥት ፀጥታ ኃይል ጋር ግጭት ውስጥ የገቡት የፋኖ ታጣቂዎች ፤ በተለይ " ከአማራ ልዩ ኃይል መፍረስ ጋር በተያያዘ የ #አማራ_ህዝብ እና #ክልልን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥል ውሳኔ ነው የተወስነው ፤ ሌሎችም የህልውና ጥያቄዎች አሉብን " በማለት ወደ ግጭት መግባታቸው ይነገራል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የታሰሩት የምክር ቤት አባላት የት ናቸው ? በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተያዙ የም/ቤት አባላት ታስረውበት ከነበረው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የማቆያ ቦታ እንደሌሉ እና ያሉበትን ቦታ ማወቅ እንዳልቻሉ ከጠበቆቻቸው አንዱ ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት በሰጡት ቃል ተናግረዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እንዲሁም በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ፣ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ…
#EHRC

አዋሽ አርባ ላይ ታስረው የሚገኙ አብዛኞቹ እስረኞች ለእስር የተዳረጉት #በብሔር ማንነታቸው ብቻ መሆኑን እንደሚያምኑ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለን ጨምሮ 5 የኮሚሽኑ ባለሙያዎች የሚገኙበት ቡድን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት በቁጥጥር ሥር ውለው አዋሽ አርባ አካባቢ በሚገኘው የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የምዕራብ ዕዝ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ ውስጥ ተይዘው የሚገኙትን ታሳሪዎች ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ጎብኝቷል።

እነዚህ ታሳሪዎች ፦
- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ፣
- የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ዮሐንስ ቧያለው፣
- የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር ካሳ ተሻገር፤
- ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ፣ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ፤
- የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባል አቶ ስንታየሁ ቸኮል፣ አቶ በለጠ ጌትነት፤
- በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ውስጥ በኃላፊነት ይሠሩ የነበሩት አቶ ከፋለ እሱባለውን ጨምሮ በአጠቃላይ 53 ወንድ እስረኞች ሲሆኑ ከአዲስ አበባ ከተማና ከአማራ ክልል የተለያዩ ቦታዎች በተለያየ ጊዜ ተይዘው ከነሐሴ 15 ቀን እስከ ነሐሴ 24 ቀን 2015 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ወደ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ የሚገኝ ጊዜያዊ / መደበኛ ያልሆነ ማቆያ ጣቢያ የተወሰዱ ናቸው፡፡

ኮሚሽኑ በተለመደው አሠራሩ መሠረት ታሳሪዎቹን ለብቻቸው አነጋግሯል፣ ቦታውን ጎብኝቷል እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸውን የፖሊስ ኃላፊዎች አነጋግሯል፡፡

የፖሊስ ኃላፊዎች ለኮሚሽኑ እንደገለጹት ፤ ታሳሪዎችን ወደዚህ ጊዜያዊ ማቆያ ጣቢያ ማምጣት ያስፈለገው አዲስ አበባ የሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ማቆያ ጣቢያ ላይ ከፍተኛ መጣበብ በመፈጠሩ መሆኑን ገልጸዋል።

ታሳሪዎች ምን አሉ ?

እጅግ አብዛኛዎቹ ታሳሪዎች ብሔራቸው #አማራ፣ እምነታቸው ኦርቶዶክስ ክርስቲያን መሆኑንና ለእስር የተዳረጉት ደግሞ #በብሔር ማንነታቸው ብቻ መሆኑን እንደሚያምኑ ገልጸዋል።

ከፊሎቹ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተያዙበትና ቤታቸው በተበረበረበት ወቅት በራሳቸውና በቤተሰብ አባል ላይ ድብደባ፣ ብሔር ተኮር ስድብ፣ ማጉላላት፣ ዛቻና ማስፈራራት እንደደረሰባቸው ሆኖም በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ከሆነ በኋላ የተፈጸመ ድብደባ ወይም አካላዊ ጥቃት አለመኖሩን አመልክተዋል።

ከፊሎቹ በተለይም ከአማራ ክልል ተይዘው የመጡ ሰዎች ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ ቤተሰቦቻቸው የት እንዳሉ እንኳን እንደማያውቁ አስረድተዋል።

ታሳሪዎቹ የአዋሽ አርባ አካባቢ እጅግ ከፍተኛ ሙቀት ያለው በመሆኑና ከአካባቢው የአየር ጠባይ እንዲሁም ቦታው የወታደራዊ ካምፕ እንጂ መደበኛ የተጠርጣሪዎች ማቆያ ስፍራ ስላልሆነ ለጤንነታቸው፣ ለደኀንነታቸውና ለሕይወታቸው ሥጋት እንዳላቸው፣ አልባሳትን ጨምሮ ከቤተስብ የሚፈልጉትን አቅርቦት ለማግኘት እንዳልቻሉ፣ ከፊሎቹ በሥራቸውም ሆነ በግል ሕይወታቸው ፈጽሞ በፖለቲካ ነክ ጉዳይ ተሳትፎ እንደሌሉና እንዴት ለእስር እንደበቁ መገረማቸውንና መደንገጣቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ፤ ከፖሊስ ኃፊዎች ጋር ውይይት ያደረገ ሲሆን በእስር ወቅት ተፈጽመዋል ስለተባሉ የሥነ ምግባር ጥሰቶች ተገቢው ማጣራት እንዲደረግ፣ ታሳሪዎቹ ከቤተሰብ ለሚፈልጉት አቅርቦት አዲስ አበባ በሚገኘው የፖሊስ ቢሮ አማካኝነት እንዲመቻች፣ ከቤተስብ መገናኛ ስልክና ጉብኝት ለሚፈልጉም በአፋጣኝ እንደሚመቻች መግባባት ላይ ተደርሷል።

(ከኢሰመኮ የተላከልን መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#አማራ

ዋዜማው እና የአዲስ አመቱ አቀባበል በአማራ ክልል እንዴት ነው ?

በአማራ ክልል በቅርቡ ባጋጠመው ደም አፋሳሽ ግጭት ምክንያት የዘንድሮው አዲስ ዓመት አቀባበል ቀዝቃዛ እንደሆነ ነዋሪዎች እየገለፁ ናቸው።

ባለፉት ዓመታት የነበሩ የአዲስ ዓመት አቀባበሎችም ክልሉ ባስተናገደው አስከፊ ጦርነት ምክንያት ዜጎች በተሟላ ሰላም በዓሉን መቀበል እንዳልቻሉ የሚታወቅ ነው።

በዘንድሮው ዓመትም ባጋጠመው ጦርነት ሰላም በመራቁ የአዲስ አመት አቀባበሉ ጥላ ያጠላበት ነው።

የኢተርኔት አገልግሎት በክልሉ እንደተቋረጠ ነው።

ዛሬ ቃላቸውን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ የሰጡ የክልሉ ነዋሪዎች የበዓሉ ድባብ ቀዝቃዛ ነው ብለዋል።

የደብረታቦር ከተማ ነዋሪ ፦

" በዓሉን በተመለከተ የተለየ ነገር በከተማው አይታይም።

የማህበራዊ ሚዲያ አገልግሎት በመቋረጡም የመልካም ምኞት መልዕክቶችን መለዋወጥ አልቻልንም። "

የደንበጫ ከተማ ነዋሪ ፦

" አካባቢው እንስሳት የሚደልቡበት አካባቢ ነው። በነበረው አለመረጋጋት እንስሳት መድለብ አልቻሉም። ከሌላ ቦታ ሄዶ የእርድ እንስሳትንም መግዛት አልተቻለም።

አጋጣሚው በአዲሱ ዓመት አቀባበል ላይ አሉታዊ ጫና ፈጥሯል። "

ሌላ የዚሁ ከተማ ነዋሪ ፦

" የዓመት በዓሉን መድረስ የሚያመላክቱ ሙዚቃዎች አይሰሙም፣ ለእርድ እንስሳት የተዘጋጄ ሰው አላየሁም። "

የቢቸና ነዋሪ ፦

" ከዚህ ቀደም በነበሩ የበዓል ዝግጅቶች የእርድ እንስሳትን ቀደም ብለው ይገዙ ነበር።

አርሶ አደሩም ሆነ የእንስሳት ነጋዴው የደህንነት ስጋት ስላደረበት እንስሳቱን ወደ ገበያ ማውጣት አልቻለም። "

የደብረ ማርቆስ ነዋሪ ፦

" በጦርነት ቆፈን ሆኖ በዓል ማክበር አይቻልም። "

የፈረስ ቤት ከተማ ነዋሪ ፦

" ሁሉም ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ወደ ሥራ ባለመግባታቸው በአዲሱ ዓመት አከባበር ላይ ከፍተኛ ጫና ተፈጥሯል። "
ይህች ከተማ በቅርብ ብርቱ ውጊያ ያስተናገደች ናት።

የደሴ ከተማ ነዋሪ ፦

" ወቅታዊ ሁኔታው በበዓሉ ድምቀት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል። "

የባህርዳር ነዋሪዎች ፦

" የባሕር ዳር ከተማ የዓመት በዓል ድባቡ ብዙ ባይታይም የእንስሳት አቅርቦት አለ።

ካለፈው ዓመት ሲነፃፀር የዋጋ መጨመር ይታያል ብለዋል፡፡ "

የእንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ ነዋሪ ፦

" ሰሞኑን በዋለው ገበያ የእንስሳቱም ሆነ ሌሎች ለምግብ ፍጆታ የሚውሉ ሸቀጦች ዋጋ እጅግ ጨምሯል።

ምክንያቱም ወደ ከተማዋ የሚያስገቡ መንገዶች በሙሉ ባለመከፈታቸው ሸቀጦች እንደልብ እየገቡ ባለመሆናቸው ነው፡፡ "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ_ክልል ከትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ #አሳሳቢነታቸው የቀጠለ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የተላከልን መግለጫ ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopia
#አማራ

በአማራ ክልል የተለያዩ ዞኖች ውስጥ ንጹሐን ሰዎች መገደላቸውንና የአካል ጉዳት መድረሱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ።

በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ገላን ክፍለ ከተማ ጎዳና ላይ የነበሩ ሰዎች ማቆያ መገኘቱ ይፋ ተደርጓል።

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሠረት የታሰሩ ሰዎችም የተጠረጠሩበት ወንጀል ምርመራ በአስቸኳይ በማጠናቀቅ ፍትሕ የማግኘት መብታቸው እንዲረጋገጥ ተጠይቋል።

ኮሚሽኑ ዛሬ መስከረም 4 ቀን 2016 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ በአማራ ክልል የተለያዩ ዞኖች ንጹሐን ሰዎች መገደላቸውን እና የአካል ጉዳት መድረሱን አስታውቋል።

ኮሚሽኑ ፦
- ከነዋሪዎች፣
- ከተጎጂዎች፣
- ከተጎጂ ቤተሰቦች
- ከዐይን ምስክሮች ባሰባሰባቸው መረጃዎች መሠረት የትጥቅ ግጭቱ ወደ ክልሉ ልዩ ልዩ ወረዳዎች መስፋፋቱን ተረድቷል" ሲል የጠቀሰው መግለጫው፣ "በነዋሪዎች ላይ የሚያደርሰው ጉዳትም ተባብሶ ቀጥሏል" ብሏል።

" ለምሳሌ ከነሐሴ 19 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ በተለይም ፦
- በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስ ከተማ፣
- በሰሜን ጎጃም ዞን አዴትና መራዊ፣
- በደቡብ ጎንደር ዞን ደብረታቦር፣
- በማእከላዊ ጎንደር ዞን ደልጊ፣
- በሰሜን ሸዋ ዞን ማጀቴ፣ ሸዋ ሮቢት እና አንጾኪያ ከተሞች እና በአካባቢዎቻቸው በሚገኙ አንዳንድ የገጠር ቀበሌዎች በግጭቱ ዐውድ በርካታ ሲቪል ሰዎች መሞታቸውን " አስታውቋል።

ኢሰመኮ አክሎ፣ " ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን እና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው ለመረዳት ተችሏል " ብሏል።

ኮሚሽኑ በመግለጫው፣ " በተኩስ ልውውጦች ወይም በከባድ መሣሪያ ተኩስ ከሚሞቱ ሰዎች መካከል በመንገድና በእርሻ ሥራ ላይ እንዲሁም በቤታቸው ውስጥ የነበሩ ሰዎች ጭምር የሚገኙ መሆኑን ቤተሰቦች እና የዐይን ምስክሮች ያስረዳሉ " ሲል አስገንዝቧል።

" በዚሁ የግጭቱ ዐውድ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች በመንግሥት የጸጥታ አካላት ከሕግ/ፍርድ ውጭ የተፈጸሙ ግድያዎች (extrajudicial killings) እጅግ አሳሳቢ ነው "ም ብሏል።

" ለምሳሌ ከሐምሌ 24 እስከ ጳጉሜን 4 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ በተለይም ፦
- በአዴት፣
- በደብረማረቆስ፣
- በደብረ ታቦር፣
- በጅጋ፣
- በለሚ፣
- በማጀቴ፣
- በመራዊ፣
- በመርጦ ለማርያምና ሸዋ ሮቢት ከተሞች ተስፋፍተው በተፈጸሙ ከሕግ/ፍርድ ውጪ የሆኑ #ግድያዎች ሰለባ " የሆኑ ሰዎች እንዳሉ መግለጫው ያስረዳል።

ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች " በተፈጸመ ከሕግ አግባብ ውጭ ከሆኑ ሰዎች መካከል ቤት ለቤት በተደረገ ፍተሻ የተያዙ ሰዎች፣ በግጭቱ ወቅት መንገድ ላይ የተገኙ እና ያልታጠቁ ሰዎች፣ ' የጦር መሣሪያ ደብቃችኋል አምጡ ' በሚል የተያዙ ሰዎች፣ የሰዓት እላፊ ገደቦችን ተላልፈው የተገኙ ሲቪል ሰዎችና በቁጥጥር ስር የዋሉ የታጣቂው ቡድን (በተለምዶ ፋኖ በመባል የሚታወቀው) አባላት የሚገኙበት ሲሆን፤ በኮሚሽኑ እና በአስቸኳይ ጊዜ መርማሪ ቦርዱ አማካኝነት የተሟላ ምርመራ ሊደረግበት የሚያስፈልግ ነው " ይላል መግለጫው።

" ከዚህ በተጨማሪም የአስቸኳይ ጊዜ መምሪያ ኮማንድ ፖስት በይፋ ካሳወቃቸው እስሮችና ቦታዎች ውጪ በተለይ በአማራ ክልል፣ በኦሮሚያ ክልል እና በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በአስቸኳይ ጊዜ ዐውዱ የተስፋፋና የዘፈቀደ እስር የተፈጸመ "ም ተመላክቷል።

ኮሚሽኑ ይህን ሲያብራራም፣ "ለምሳሌ በአማራ ክልል ፦
- በባሕር ዳር፣
- በደብረ ታቦር፣
- በደብረ ማርቆስ፣
- በፍኖተ ሰላም፣
- በጎንደር፣
- በላሊበላ፣
- በመካነሰላም፣
- በቆቦ እና በሸዋ ሮቢት ከተሞች፤ በኦሮሚያ ክልል በተለይ #በሸገር ከተማ እና #በአዲስ_አበባ ከተማ የተፈጸሙ የዘፈቀደ እስሮች ይገኙበታል " ሲል አክሏል።

" ከእነዚህ ታሳሪዎች ውስጥ በደቡብ ክልል ፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ግቢ (በተለምዶ አቦስቶ በመባል የሚታወቀው ቦታ) የነበሩ ታሳሪዎችን ጨምሮ ከተለያየ ጊዜ መጠን በኋላ የተለቀቁ መኖራቸውን ማወቅ የተቻለ ቢሆንም፤ በአንጻሩ ገና ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቀ ሰዎች ይህ መግለጫ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ በእስር ላይ ይገኛሉ " ነው ያለው።

እንደ ኮሚሽኑ መግለጫ፣ " በመንግሥት የጸጥታ አካላት የሚታሰሩ ሰዎች በአብዛኛው ' ለታጣቂ ቡድኑ ድጋፍ ታደርጋላችሁ ' እና/ወይም 'የጦር መሣሪያ ደብቃችኋል ' በሚል ምክንያት ነው " ብሏል።

አክሎም ፣ " በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ገላን ክፍለ ከተማ ውስጥ ሲዳ አዋሽ ወረዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው ጊዜያዊ ማቆያ ማእከል ውስጥ ተይዘው የነበሩ " ሰዎች ማረጋገጡን አስታውቋል።

" ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በፊትና በኋላም ከተለያዩ ክልሎች የመጡ ሕፃናት እና ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ውሏቸውን ጎዳና ያደረጉ ነዋሪዎች ከጎዳና ላይ ተነስተው እንዲቆዩ የሚደረግበት ቦታ መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው ፤ በቅርቡ ወደ ማእከሉ ከተወሰዱት ውስጥ 29 ሰዎች በመታወቂያ ካርዳቸው ተለይተው እንዲለቀቁ መደረጉን " አትቷል።

አክሎም ፤ " የተወሰኑት ደግሞ በመልሶ ማቋቋም ፕሮግራም ወደየመጡበት አካባቢዎች እንዲመለሱ የተደረገ መሆኑን፣ በጣቢያው ውስጥ ተከስቶ የነበረው ተላላፊ በሽታ በቁጥጥር ስር የዋለ መሆኑን ኮሚሽኑ በክትትሉ ተመልክቷል " ብሏል።

ኮሚሽኑ በመጨረሻም የተለያዩ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን ጨምሮ ፤ " በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሠረት የታሰሩ ሰዎችም የተጠረጠሩበት ወንጀል ምርመራ በአስቸኳይ በማጠናቀቅ ፍትሕ የማግኘት መብታቸው እንዲረጋገጥ " ሲል ጠይቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ያዘጋጀው #ከኢሰመኮ በተላከለት መግለጫ ነው።

@tikvahethiopia
#ኮሌራ #አማራ_ክልል

በአማራ ክልል በኮሌራ ወረርሽኝ ሳቢያ የበርካታ ኢትዮጵያውያን ጨምሮ የሱዳን ጦርነትን ሸሽተው አማራ ክልል የገቡ የሱዳን ዜጎች ህይወት ማለፉ ተነገረ።

የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር /UNHCR/ ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ በሰጠው ቃል ፤ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ውስጥ በተቋቋመ የኩመር መጠለያ ጣቢያ፣ የኮሌራ ወረርሽኝ እንደተከሠተና ዘጠኝ #ሱዳናውያን ስደተኞች እንደሞቱ አሳውቋል።

395 ሰዎች ደግሞ እንደታመሙም ገልጿል።

የኢትዮጵያ ምክትል ተወካይ ማርጋሬት አትዬኖ ፤ በሱዳኑ ግጭት ምክንያት ተፈናቅለው ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ብዛት፣ ከ35 ሺሕ በላይ መድረሱን ተናግረዋል፡፡

ከእኒዚም ውስጥ፣ 10 ሺሕ የሚደርሱት ፤ በአማራ ክልል በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ በሚገኝ የኩመር መጠለያ ጣቢያ እንደተጠለሉ ሌሎቹ ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የሸርቆሌ መጠለያ ጣቢያ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል ፤ በአማራ ክልል ከዛሬ ጀምሮ ለቀጣይ 6 ቀናት የኮሌራ በሽታ ክትባት መሰጠት ዘመቻ እንደተጀመረ ተጋጿል።

ክትባቱ እድሜያቸው አንድ ዓመትና ከዚያ በላይ ለሆኑ ሰዎች  ነው የሚሰጠው።

የክትባት ዘመቻው አስቻይ ሁኔታዎች አሉባቸው በተባሉት ባሕር ዳርና ጎንደር ከተማን ጨምሮ 9 ወረዳዎች ላይ ይሰጣል ፤ በዚህም ለ1 ነጥብ 8 ሚሊየን ሰዎች ክትባቱን ለመስጠት ታቅዷል ተብሏል።

አሁን ላይ በአማራ ክልል በ28 ወረዳዎች የኮሌራ ወረርሽኝ መከሰቱን የክልሉ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳውቋል።

በዚህም ከ3 ሺህ 8 መቶ በላይ ሰዎች በበሽታው የተጠቁ ሲሆን ከ70 በላይ ሰዎች ደግሞ ሕይወታቸው አልፏል።

በየቀኑ ከ15 እስከ 20 ሰዎች በአዲስ በበሽታው እየተጠቁ መሆኑን ኢንስቲትዩቱ ጠቁሟል።

(ስለ ኮሌራ መተላለፊና መከላከያ መንገዶች ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንዲኖርዎት ከላይ የተያያዘውን ምስል ይመልከቱ)

@tikvahethiopia
#አማራ

ቤተሰቦቻቸው በአማራ ክልል የሚገኙ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በክልሉ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት በየዕለቱ የበርካታ ሰዎች ህይወት እያለፈ፣ ንብረት እየወደመ ፣ ቀድሞም የደቂቀው ኢኮኖሚና የኑሮ ሁኔታ እየባሰበት እየሄደ መሆኑን ገለፁ።

ለችግሮች መፍትሄ እንዲፈለግም ጠይቀዋል።

ስማቸውን መናገር ያልፈለጉ ቤተሰቦቻቸው ጎጃም ውስጥ እንደሚኖሩ የገለፁ አንድ የቤተሰባችን አባል፤ " ህዝቡ በሰላም እጦት መሰቃየት ከጀመረ ወራት ተቆጠሩ " ብለዋል።

እሳቸው ባላቸው መረጃም በጦርነቱ በርካታ ሲቪል ሰዎች ሰለባ እንደሆኑ ገልጸዋል።

ቤተሰቦቻቸው ባሉበት አካባቢ ያለው ግጭት አንዴ እየቀዘቀዘ ዳግም ደግሞ እያገረሸ ወራት መቆጠሩን በመግለፅ ሁኔታው ለእርሻ፣ ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴ አዳጋች እንደሆነና በዚህም ህዝቡ ሁለንተናዊ ስቃይ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል።

" ያለፉት ዓመታት ጦርነት ያሳጣንን ማስታወስ ይገባል " ያሉት እኚሁ ግለሰብ በአስቸኳይ ሰላማዊ መፍትሄ ተገኝቶ ህዝቡ በተለይ ገበሬው ወደቀደመው ስራ ካልተመለሰ ቀጣይ የሚመጣው ቀውስ እጅግ የከፋ ነው ብለዋል።

ደብረ ማርቆስ ውስጥ እናት እና አባቷ እንዳሉ የገለፀች የአዲስ አበባ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ስለ ቤተሰቦቿ መጨነቅ ከጀመረች ወራት እንዳለፈ ተናግራለች።

" ዘውትር እንቅልፍ የለኝም፤ ከዛሬ ነገ ምን ይፈጠራል እያልኩኝ በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ከወደኩ ይኸው ሳምንታት አልፈዋል " ብላለች።

ጦርነቱ የሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ከመሆኑም በላይ ኑሮ ውድነቱን እያባባሰው ነው የምትለው ይህች የቤተሰባችን አባል መፍትሄ እንዲፈለግ ርብርብ ይደረግ ስትል ተማፅናለች።

ሌላው አንድ በአማራ ክልል ቤተሰቦቹ የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል፤ እሱን ጨምሮ ሌሎችም ያለ አንዳች ጥፋት " የፋኖ ደጋፊ ናችሁ " በሚል ለእስር ተዳርገው እንደነበር በመግለፅ ጦርነቱ እየፈጠረው ያለው ቀውስ ሁለንተናዊ ነው ብሏል።

በርካቶች አሁንም በጥርጣሬ ብቻ በእስር እየማቀቁ፣ ቤተሰብም እየተሰቃየ ነው፣ ይህንን ስሜት በቦታው ላይ ካልሆነ ማንም አይረዳውምና ስቃዩና መከራው ያበቃ ዘንድ መፍትሄ እንዲፈለግ ተማፅኗል።

ሌላው አንድ የሚወዳቸውን ሰዎች በዚሁ ጦርነት የተነጠቀ የቤተሰባችን አባል #አሉታዊ ነው ያለውን የማህበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴ የተቃወመ ሲሆን ለተገደሉት ለተገፉት ወገኖች ፍትህ ጠይቋል።

" #አንዳንዶች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ብቻ ቀኑን ሙሉ ሲሰዳደቡ፣ ሲበሻሸቁ፣ በዘፈን፣ በድለቃ ፣ በወሬ የሚጮሁ ከግጭት ቀጠናው ፍፁም የራቁ፣ ወንድም እህታቸውን እናት አባታቸውን ያላጡ፣ የሰላምን አየር እየተነፈሱ ያሉ፤ ጦርነት ምን እንደሆነ ፈፅሞ የማይያውቁ ናቸው " ብሏል።

" የአማራ ህዝብ ኢንተርኔት ካጣ ወራት አልፎታል፣ የሰላም እጦቱ ሰለባ እሱ ነው፤ #አንዳንዶቹ አንድም ቀን የጥይት ድምፅ ሰምተው የማያውቁ፣ ሰው ያልሞተባቸው ናቸው " ሲል ተችቷል።

ከምንም በላይ እየተካሄደ ባለው ግጭት ያለ ሃጢያታቸው ነፍሳቸውን ለተነጠቁ ንፁሃን ወገኖች፣ በሀዘን ላይ ለሚገኙ ቤተሰቦች፣ ለተጎዱ፣ ለተገፉ ወገኖች ሁሉ ፍትሕ ይስፈን፤ ንፁሃንን የገደሉ፣ ያስገደሉ፣ ትዕዛዝ ያስተላለፉ ሁሉም ጥፋተኞች ይጠየቁ፤ በዚህ ጉዳይ ሁሉም ድምፁን ሊያሰማ ይገባል ሲል አሳስቧል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጣይም ከቤተሰቦቹ የሚደርሱትን መልዕክቶች እያሰባሰበ ያቀርባል።

@tikvahethiopia
#አማራ

በአማራ ክልል ፤ ሰሜን ሸዋ ዞን ከ88,000 በላይ ለሚሆኑ ተፈናቃዮች የድጋፍ እጥረት ማጋጠሙ ተገልጿል።

በአማራ ክልል ደብረ ብርሃን፣ ሰሜን ሸዋ በመጠለያ ካምፓችና ከመጠለያ ውጪ በዘመድ ወዳጅ ቤት ተጠልለው ለሚገኙ ከ88,000 በላይ ተፈናቃዮች የድጋፍ እጥረት ማጋጠሙን የሰሜን ሸዋ ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ገልጿል።

እጥረቱ ያጋጠመው፣ በግጭት ምክንያትና መንግሥት የሚሰጠው ወርሀዊ ድጋፍ ገና ባለመሰጠቱ ነው ተብሏል።

" ከግጭቱ ጋር ተያይዞ የሚደግፉ አካላት እንደልባቸው ገብተው መደገፍ አልቻሉም " ሲሉ የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት የቅድመ ማስጠንቀቂያና ምላሽ ቡድን መሪ አቶ ደረጀ ይነሱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

" አሁን የድጋፍ እጥረት አለ። ሁለተኛ ደግሞ አሁን የመስከረም ወር ድጋፍ ራሱ ማግኘት አለባቸው። የመስከረም ወር ድጋፍ ገና አልገባም። እየጠበቅን ነው " ብለዋል።

" በአብዛኛው ሰሜን ሸዋ ወረዳ ላይ በግጭት የተሞላ ስለሆነ ከኅብረተሰቡም ድጋፍ ማሰባሰብ አይታሰብም " ያሉት አቶ ደረጀ፣ " በመንግሥት የሚሰጠው የመስከረም ወር ድጋፍ እስካሁን መድረስ ነበረበት። ገና እየጠበቅን ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

ድጋፉ እንዲገኝ ምን እየተደረ እንደሆነ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ደረጀ ፣ " በእኛ በኩል ያለውን ነገር ችግሩን ለመንግሥት ማሳወቅ ነው። አሳውቀናል " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ በመጠለያ ካምፕ ያለ ዕድሜ ጋብቻ መፈጸሙ፣ የሥጋ ዝምድና የሌላቸው ወንድና ሴት ተፈናቃዮች አንድ ላይ በመኖራቸው የመደፈር ጥቃት ይፈጸማል የሚል ሥጋት እንዳለ ተመላክቷል።

ያለ ዕድሜ ጋብቻን በተመለከተ አቶ ደረጀ በሰጡት ማብራሪያ፣ " ወይንሸት መጠለያ ካምፕ ዕድሜዋ 15 የሆነች ልጅ ያለ ዕድሜ ጋብቻ ተፈጽሞ ነገሩ በፓሊስ ጣቢያ ተይዟል " ብለዋል።

አክለውም፣ " ባቄሎ መጠለያ ካምፕ ላይ ግን ሁለት ወንዶችና አንዲት ሴት (አባውራዎች ማለት ነው) በአንድ ቤት ውስጥ እንዲኖሩ ተደርገው ሴቷ ቀን ቀን እዚያው ቤት ትውላለች፣ ማታ ማታ ደግሞ ሌሎች ጓደኞቿ ጋ እየሄደች ነው የምታድረው። ይሄ ነገር ለመደፈር ጥቃት ሊያጋልጥ የሚችል ነው " ሲሉ ሥጋታቸውን ገልጸዋል።

ችግሩን ለመቅረፍም፣ በተለይ ቤተሰብ ያልሆኑ ሰዎች በአንድ ሼድ ውስጥ መቀመጥ በተለይ ባቄሎ መጠለያ ካምፕ የሥጋ ዝምድና የሌላቸውና አብረው የሚኖሩ ሰዎችን መለየት ያስፈልጋል የሚል ሀሳብ እንዳለ ጠቁመዋል።

" በእርግጥ ችግሩ በርካታ ነው። አንዳንዱ አንለይም የሚል አለ። በሌላ መልኩ ደግሞ የመጠለያ ችግርም ለመለየት የሚያመች አይደለም " ብለዋል።

በደብረ ብርሃን በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ከ25,000 በላይ፣ በሰሜን ሸዋ በሚገኙ የመጠለያ ካምፖች ከ63,000 በላይ በአጠቃላይ በሰሜን ሸዋ ዞን ከ88,000 በላይ ተፈናቃዮች ይገኛሉ ተብሏል።

መረጃው የቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#አማራ

ከፊታችን ያሉት ሃማኖታዊ በዓላት በአደባባይ እንዲከበሩ ተፈቀደ።

የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መምሪያ ዕዝ በአማራ ክልል ለመውሊድ ፣ ደመራ እና መስቀል በዓላት መሰባሰብን ፈቀደ።

ዕዙ ፤ መስከረም 16 እና 17 /2016 የሚከበሩት የመውሊድ፣ የደመራና የመስቀል በዓላት በአማራ ክልል የሃይማኖቶቹ ሥርዓት በሚፈቅዱት መንገድ እንዲከበሩ እየሰራሁ ነው ብሏል።

ምንም እንኳን የሕዝብ ስብሰባዎች በአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁ ቢከለከሉም መስከረም 16 እና 17 የሚከበሩት ሃይማኖታዊ በዓላት የአደባባይ በዓላት በመሆናቸው ለበዓላቱ ሥነ ሥርዓት ሲባል የአደባባይ መሰባሰብን መፍቀዱን ገልጿል።

ዕዙ ፤ እነዚህ መሰባሰቦች ለሃይማኖታዊ የበዓል አከባበር ሥነ ሥርዓት ብቻ  የሚውሉ እንደሆነ አሳውቋል።

የአደባባይ መሰባሰቦች የበዓላቱ አከባበር ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ብቻ የሚከናወኑ ገልጿል።

በእነዚህ አከባበሮች ወቅት ለሕዝብ ደኅንነት ሲባል ከጸጥታ አካላት ጋር መተባበር #ግዴታ እንደተጣለ አሳውቋል።

በአማራ ክልል የፀጥታ ሁኔታ ከክልሉ አስተዳደር አቅም በላይ በመሆኑ ክልሉ ለፌዴራል መንግሥት ባቀረበው ጥሪ መሰረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ ይታወሳል።

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከተቀመጡ ክልከላዎች አንዱ ደግሞ " መሰባሰብ " ነው። ከቀናት በኃላ በሚከበሩት ሃይማኖታዊ በዓላት ላይ ስነሥርዓቶቹ ተከናውነው እስኪያልቁ መሰባሰብ መፈቀዱ ይፋ ተደርጓል።

@tikvahethiopia
#አማራ

በአማራ ክልል ወቅታዊ የክልሉ የሰላም መደፍረስ በፈጠረው የመንገዶች መዘጋጋት እና መድኃኒቶች በቀላሉ ወደ ጤና ተቋማት መድረስ ባለመቻላቸው ህሙማን ተገቢውን ህክምና እያገኙ እንዳለሆነ የጤና ባለሙያዎች መናገራቸውን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

በደምና በኦክስጅን አቅርቦት ችግር ወላዶች ለሞት እየተዳረጉ እንደሆነም ተገልጧል።

ከሐምሌ 2015 ዓ/ም መጨረሻ ጀምሮ በአማራ ክልል በተቀሰቀሰው ጦርነት በርካታ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ሥራቸው ተስተጓጉሏል።

ችግር ካጋጣማቸው ተቋማት መካከል የፀጥታ ችግሮች ባሉባቸው የምዕራብ አማራ አካባቢ የጤና ተቋማት ይጠቀሳሉ።

ነዋሪዎች እና የጤና ባለሞያዎች ምን ይላሉ ?

በምዕራብ ጎጃም ዞን ፈረስ ቤት ከተማ የሚገኙ አንድ ታካሚ ያጋጠማቸውን የመድኃኒት እጥረት ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል

" ኤሌክትሪክ አደጋ ደርሶብኝ ለመታከም ወደ ሆስፒታል ሄጀ ነበር፣ መድኃኒት በሀኪም ቤቱ ባለመኖሩ ከግል መድኃኒት ቤት መድኃኒት በ12 ሺህ ብር ገዝቻለሁ፣ በግል መድኃኒት ቤት ያሉ መድኃኒቶችም እያለቁ ነው። "

በምዕራብ ጎጃም ዞን የቡሬ ሆስፒታል ባለሙያ ፦

" በመድኃኒትና በደም እጥረት ምክንት  ህሙማን  በተለይ እናቶች እየሞቱ ነው። የደምና የኦክስጅን እጥረት በከፋ ሁኔታ በሆስፒታሉ ይስተዋላል። "

የፍኖተሰላም ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ  አቶ ማናየ ጤናው ፦

" በደምና በኦክስጅን አቅርቦት እጥረት በቅርቡ ሁለት ወላዶች ሕይወታቸው አልፏል። "

በምሥራቅ ጎጃም ዞን የየጁቤ ሆስፒታል ሐኪም፦

" በአካባቢ ከሚገኙ ወረዳዎች በመበደርና በትብብር በመውሰድ የመድኃኒት አገልግሎት ለታማሚዎች እያቀረብን ነበር። አሁን ግን ወረዳዎችም መድኃኒት በመጨረሳቸው ያን ማድረግ አልተቻለም። "

ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ የደብረማርቆስ ሆስፒታል ሐኪም ፦

" የመድኃኒትና የጀነሬተር እጥረቶች፣ እንዲሁም የመብራት መቆራረጥ በተለይ የቀዶ ህክምና አገልግሎት ለመስጠት ፈተና ሆኗል።

ያለ መድኃኒት በሆስፒታሉ ውስጥ መሥራት፣ ያለ ጥይት መሳሪያ ይዞ ጦርሜዳ እንደመዋል ነው። "

የደብረ ማርቆስ የደም ባንክ አስተባባሪ አቶ ከፋለ ገበየሁ ፦

" ወቅታዊ ሁኔታው ደም ለመሰብሰብ አላስቻለንም።

ደም ለመሰብሰብ ሁለት ዓይነት መንገዶች አሉ፤ አንዱ ጊዜያዊ ድንኳኖችን አቁሞ ከፈቃደኞች ደም መውሰድ ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ ወደ ደም ባንክ ማዕከሉ የሚመጡ በጎ ፈቃደኞችን መቀበል ነው። ይሁን እንጂ አሁን ያን ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ የለም።

ናሙናዎችን ወደ ባሕር ዳር ለመውሰድም የመንገዶች በፀጥታ ሁኔታ መዘጋጋት ሌላው አስቸጋሪ ሁኔታ ነው። "

የመድኃኒት አቅርቦትን በተመለከተበኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ምን ይላል ?

የባሕር ዳር ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ አምሳሉ ጫኔ ፦

" የፕሮግራም የሚባሉ መድኃኒቶች ከለጋሽ ድርጅቶች በእርዳታ የሚሰጡ ሲሆን በራሳችን መሥሪያ ቤት በግዥ የሚፈፀሙ ደግሞ አሉ፣ ሁለቱንም ለማጓጓዝ አውሮፕላን እንጠቀማለም ከዚያም መድኃኒቱ ባሕር ዳር ከደረሰ በኋላም አንፃራዋ ሰላም ባለባቸው አካባቢዎች መድኃኒቶቹ ይሰራጫሉ።

የመንገድና የፀጥታ ችግሮች እያሉም ሰሞኑነ የተወሰኑ መድኃኒቶችን ወደ ምሥራቅ ጎጃም ማድረስ ችለናል።

ወደ ምዕራብ ጎጃም አካባቢዎችም ለማድረስ ጥረት እየተደረገ ነው ሆኖም አሁንም የመንገዶች ሁኔታ አስቸጋሪ ነው። "

Credit - #ዶቼቨለ

@tikvahethiopia