TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የደኢህዴን ስብሰባ ተጠናቋል!

በሐዋሳ ሲካሔድ የቆየው የደኢሕዴን ስብሰባ መጠናቀቁን ንቅናቄው አስታውቋል። ደኢሕዴን «በክልሉ እየተነሱ ያሉ የአደረጃጀት ጥያቄ ላይ በተደረገው የጥናት ግኝት ላይ ከሐምሌ 18 ጀምሮ» ስብሰባ ላይ ከርሟል፤ ከደቂቃዎች በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።

Via #EshetBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል በ319 ወረዳዎች እና በ19 ከተሞች ከ7 ሺሕ 426 ቀበሌዎች የተውጣጡ ከ57,000 በላይ የቀበሌ አመራሮች ከዛሬ ጀምሮ የ10 ቀናት የአመራር ስልጠና መጀመራቸውን የኦሮሚያ ኮምዩንኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አድማሱ ዳምጠው ተናግረዋል።

Via #EshetBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
«የጄኔራል ሰዓረ ገዳይ ወታደር መሳፍንት ጥጋቡ «ስለ ቆሰለ እስካሁን በሕክምና ላይ ይገኛል፣ የቆሰለው አንገቱ አካባቢ ስለሆነና መናገር ስለማይችል አዳዲስ ነገር አልተገኘም። በደንብ ሲሻለው የበለጠ መረጃዎች ይገኛሉ» ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ

Via #EshetBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update 33 የፖለቲካ ፓርቲዎች ከየምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች ረቂቅ ሕግ 20 አንቀጾች እንዲሰረዙ 13 እንዲሻሻሉ በዛሬው ዕለት ጠይቀዋል ጠይቀዋል። የመንግሥት ሰራተኞች ለምርጫ ሲወዳደሩ ሥራቸውን ሊለቁ ይገባል የሚለው አጨቃጫቂ ሆኗል። ከኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ኮንግረስ አቶ ገረሱ ገሳ «የመንግሥት ሰራተኞች መልቀቅ ካለባቸው ከጠቅላይ ምኒስትሩና አፈ-ጉባኤው ጀምሮ መልቀቅ አለባቸው» ብለዋል።

Via #EshetBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ፓርቲዎች ከ140-160

የኢትዮጵያ ፓርቲዎች ከ140-160 ደርሰናል እያሉ ነው ሲሉ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ ተናግረዋል። ዛሬ ባደረጉት ውይይት ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሚከፍለው የስብሰባ አበል ለምን ቀረ? የሚለው ዋንኛ አጀንዳ ነበር ተብሏል።

Via #EshetBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደቡብ አፍሪካ ካሰረቻቸው 600 በላይ የውጭ ዜጎች 150 ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ነቢያት ጌታቸው ተናግረዋል። ጆሐንስበርግ የሚኖሩ ኢትዮጵያውን ግን ቁጥሩን 600 ገደማ ያደርሱታል።

Via #EshetBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኢሕአዴግ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪክ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ፦

ኢሕአዴግ "ዝርዝርና ብስል" ግምገማ አድርጊያለሁ ብሏል። አቶ ፍቃዱ ተሰማ እንዳሉት ሥራ አስፈጻሚው በኢሕአዴግ አባል ፓርቲዎች መካከል አንድነትን የሚጎዱ ነገሮች እንዲታረሙ፣ ፓርቲዎቹም እርስ በርስ #ከመወነጃጀል እንዲቆጠቡ ድምዳሜ ላይ ተደርሷል።

"የተቀመጡ አቅጣጫዎችን በሙሉ ልብ ሁሉም ወስደው በተመሳሳይ ሁኔታ ያለመፈጸም" ችግር በኢሕዴግ አባል ፓርቲዎች መካከል መኖሩን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው እንደደረሰበት አቶ ፍቃዱ ተናግረዋል። በጋራ የተወሰኑ ጉዳዮች እኩል ተግባራዊ አይሆኑም ብለዋል።

የሕግ የበላይነትን ማስከበር ፣ ለውጡን ተቋማዊ ማድረግ፣ "የለውጡን ምንነት ማስረዳት"፣ በ2012 "ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትኃዊ ምርጫ" ለማካሔድ መዘጋጀት፣ ደኢሕዴን ላሰራው "ሳይንሳዊ ጥናት" ድጋፍ ማድረግ ከኢሕአዴግ ውሳኔዎች መካከል ይገኙበታል።

Via #EshetBekele
@tsegabwode @tikvahethiopia
#የመን

ትናንት - ራሱን የደቡብ የሽግግር ምክር ቤት (southern transitional council) ብሎ የሚጠራው የየመን ተገንጣይ ቡድን በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ድጋፍ ኤደንን ተቆጣጠረ -- #ዛሬ-በሳዑዲ አረቢያ ትዕዛዝ እና ዛቻ ጥሎ መውጣት ጀመረ።

Via #EshetBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
68 አነስተኛ የኮኬይን ጥቅሎች ውጦ በአዲስ አበባ በኩል ወደ ታይላንድ የተጓዘ ኬንያዊ በባንኮክ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ባንኮክ ፖስት ዘግቧል። ግሌን ቺባሴሎ ኦኮ የተባለው ኬንያዊ 1.2 ኪ.ግ. ኮኬይን ውጦ ነበር ተብሏል።

Via #EshetBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ቻይና ከተሞች በሳምንት የሚያደርጋቸውን 35 በረራዎች ወደ 50 ለማሳደግ መዘጋጀቱን አቶ ተወልደ ገብረማርያም ተናግረዋል። ወደ ጃፓንና ኢንዶኔዥያ የሚያደርጋቸውን ለማሳደግ ወደ ቪየትናም ለመጀመር ወጥኗል።

Via #EshetBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia