TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኦብነግ🤝የሱማሌ ክልል⬆️

የሱማሌ ክልል መንግስትና የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) #ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ተሰምቷል።

ስምምነቱ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ጉዳዮች የሚያካትት ነው፦

▪️ኦብነግ በክልሉ በነፃነት እንዲንቀሳቀስ የክልሉ መንግስት #ድጋፍ ያደርጋል።

▪️የክልሉ መንግስት የኦብነግ ወታደሮች ድጋፍ የሚያገኙበትን እንዲሁም ከህብረተሰቡ ጋር የሚቀላቀሉበትን ሁኔታ ያመቻቻል።

▪️የሱማሌ ክልል ሆነ ኦብነግ ከትንኮሳ እና ከጠብ አጫሪነት ድርጊት ይቆጠባሉ።

▪️ለክልሉ ሰላም በጋራ ይሰራሉ።

▪️ኦብነግ ከፌድራል መንግስት ጋር እንዲወያይ የክልሉ መንግስት የድጋፍና የማስተባበር ስራ ይሰራል።

▪️የክልሉ መንግስት ኦብነግ እንደድርጅት በክልሉ ውስጥ ለሰላማዊ የፖለቲካ ትግል እንዲንቀሳቅስ እገዛ ያደርጋል።

▪️የክልሉ መንግስት ከሁለት አመት በኋላ ምርጫ እንዲደረግ በቁርጠኝነት ይሰራል።

📌ከላይ በተደረሱት ስምምነቶች መሰረት የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጪ ግንባር(ኦብነግ) ለአዲሱ የክልሉ አስተዳደር በይፋ እውቅና እንደሚሰጥ እና አብሮም እንደሚሰራ አስታውቋል።

©RAJO
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert

የሱዳን ጦርና ተቃዋሚዎች የሽግግር መንግስት ለመመስረት #ከስምምነት ደረሱ። ከአልበሽር መውደቅ በኃላ በአፍሪካ ህብረት እና #በኢትዮጵያ አደራዳሪነት በሱዳን ወታደራዊ አመራሮችና ተቃዋሚዎች መካከል ሲካሄድ የነበረው ድርድር ዛሬ ላይ ህገ መንግስታዊ ስምምነት በመድረስ ተቋጭቷል።

የአፍሪካ ህብረት እንዳስታወቀው ከሆነ ሁለቱ አካላት ሱዳንን አዲስ ህገ መንግስታዊ የሽግግር መንግስት አቋቁመው ወደ አዲስ ምሽራፍ ለማሻገር ተስማምተዋል።

የህብረቱ አደራዳሪ #ሞሐመድ_ሀሰን ለመገናኛ ብዙሃን እንዳሉት ከሁለቱም ወገን በስምምነቱ ዝርዝር አፈፃፀሞች ላይም ወይይቱን ለመቀጠል ተስማምተዋል። የሁለቱ ወገኖች ስምምነት ሰነድም የሽግግር መንግስቱና የመንግስት መዋቅሮች የስልጣን ግንኙነትና ክፍፍልንም ያማላከተ ነው ተብሏል።

ሱዳን የቀድሞ ፕሬዝዳንቷ #ኦማር_አልበሽር በህዝባዊ ተቃውሞ ከስልጣን ከተወገዱ በኃላ ካለፈው ሚያዚያ ጀምሮ በከባድ ቀውስ ውስጥ ለመሰንበት ተገዳለች። ወታደራዊ ኃይሉና የተቃዋሚዎች ጎራ የሽግግር መንግስት መስርተው ወደፊት ለመራመድ ከስምመነት መድረሳቸውን ተከትሎ ሱዳናዊያን በዛሬው ዕለት በካርቱም አደባባዮች ወጥተው ደስታቸውን እየገለፁ መሆኑ ተዘግቧል።

ምንጭ፦ #አልጀዚራና #ቢቢሲ/#etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ... ትግራይ ክልልም የክልሉን ግዛት እና ህዝቡን ለመጠበቅ በቂ የፖሊስ ኃይል፣ በቂ ልዩ ኃይል ፣ በቂ ሚሊሻ ይኖረዋል " - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ቅዳሜ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የሰላም ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት " ህወሓት "ን ትጥቅ ስለማስፈታት እና በትግራይ ክልል ውስጥ ምርጫ ተከናውኖ የክልል መንግስት…
በሰላም ስምምነቱ መሰረት ፦

👉 በኢትዮጵያ ውስጥ #አንድ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ብቻ ይኖራል።

👉 በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት መሰረት የህወሓት ተዋጊዎችን ትጥቅ ማስፈታት፣ መበተን እና ወደ ማኅበረሰቡ መልሶ ለመቀላቀል የሚያስችል ዕቅድ ተነድፎ ተግባራዊ የሚሆንበትን ዝርዝር ይዘጋጃል።

👉 ከስምምነቱ መፈረም በኃላ የመንግስት እና ህወሓት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ይነጋገራሉ (የጦር አመራሮች የስልክ ንግግር ማድረጋቸው መነገሩ ይታወቃል) ።

👉 ስምምነቱ በተፈረመ በአምስት ቀናት ውስጥ በክልሉ ካለው ተጨባጭ ፀጥታ ሁኔታ በመነሳት ስብሰባ በማዘጋጀት የጦር አመራሮች የህወሓት ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታቱ ሂደት ላይ ይነጋገራሉ ፤ ስለሂደቱም ዝርዝር ያወጣሉ። (ይህ ከሰኞ ቀን 28/2/2015 ጀምሮ በኬንያ፣ ናይሮቢ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አዛዥ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና ከህወሓት ጄነራል ታደሰ ወረደ በተገኙበት ተጀምሯል)

👉 ከፍተኛ የጦር መኮንኖች #ከስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ባሉት #አስር_ቀናት ውስጥ የከባድ መሳርያ ትጥቅ የመፍታቱ ሂደት #ይጠናቀቃል። የተቀመጠው አስር ቀናት ጊዜ ገደብ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች በሚሰጡት ሀሳብ እና በሁለቱ ወገኖች አጽዳቂነት ሊራዘም ይችላል።

👉 ከስምምነቱ በኋላ ባሉ 30 ቀናት ቀላል የጦር መሳርያዎችን ጨምሮ የህወሓት ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታቱ ሂደት ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል።

👉 የህወሓት ታጣቂዎችን የማሰናበት እና መልሶ ወደ ማኅበረሰቡ የመቀላቀል ሥራ ሂደት የክልሉን ሕግ እና ፍላጎት መሠረት ያደርጋል።

@tikvahethiopia