TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በአፋር፣ በጋምቤላ እና በሶማሌ አካባቢዎች በአምስት ኩባንያዎች #ነዳጅ እየተፈለገ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ለማምረት #ተስፋ ሰጪ ስራ እየሰራች መሆኗን የኢትዮጵያ የፔትሮሊየም ፈቃድ አስተዳደር ዳይረክቶሬት ዳይሬክተር ዶክተር #ቀጸላ_ታደሰ ተናግረዋል፡፡ኢትዮጵያ ባሳለፍናቸው ጥቂት ወራት ነዳጅ የማምረት ሙከራ ላይ ናት፡፡ ከዚህም በቀን ከ120 እሰከ 130 በርሚል ነዳጅ እየተመረተ መሆኑን የኢትዮጵያ የፔትሮሊየም ፈቃድ አስተዳደር ዳይሬክተር ዶክተር ቀጸላ ታደሰ ገልጸዋል፡፡

ምንጭ፦ የመንግስት ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ስለ ህዳሴ ግድብ...

- የሲቪል ስራው (በሳሊኒ እየተሰራ ያለ) 82 ፐርሰንት ደርሷል።

- የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራው (ለረጅም ግዜ በሜቴክ ስር የነበረ) 25 ፐርሰንት ላይ ይገኛል።

- በአጠቃላይ ፕሮጀክቱ ወደ 65 ፐርሰንት ገደማ ላይ ነው።

- እስካሁን የተበየደው ያ ሁሉ ብረታ ብረት ልክ ነው አይደለም የሚለው ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።

- ብዙ ኮንትራቶችን እንደ አዲስ እየተደራደርን ሲሆን በጥቂት ሳምንታት ውስጥ በሙሉ ሀይል ወደ ስራ እንገባለን።

- ለሜቴክ የተሰጠው ክፍያ 65 ፐርሰንት ሲሆን የፈፀመው ስራ ግን 25 ፐርሰንት ገደማ ነው። ይህም ትልቅ ችግር እና imbalance አስከትሏል።

- ያለፈው አልፏል። #ተስፋ የሚያስቆርጥ ነገር የለም።

Via-Elias Meseret
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ ሂርጳ 'ዳግም' ሞቱ‼️

ከሁለት ወራት በፊት የሞትን ብርቱ ክንድ አሸንፈው ተነሱ የተባሉት አቶ #ሂርጳ_ነገሮ ሞተው ሳሉ የገጠማቸውን ለቢቢሲ አጫውተው የነበረ ሲሆን ከ70 ቀናት በኋላ ትናንት 'ዳግም' ማረፋቸውን ከሁለት ጊዜ ገናዣቸው ተሰምቷል።

መቃብር ፈንቅለው ከወጡ በኋላ ጤናማ የነበሩት አቶ ሂርጳ ላለፉት ሁለት ሳምንታት ግን በፅኑ ታመው ከፈሳሽ ውጭ ምንም ነገር ይወስዱ እንዳልነበር BBC ከቤተሰቦቻቸው ማረጋገጥ ችሏል። እሳቸው አይሆንም ቢሉም ቤተሰቦቻቸው ነቀምት ሆስፒታል ወስደዋቸው ነበር። ቤተሰቦቻቸው አቶ ሂርጳ ዳግም መቃርብር ፈንቅለው ይነሳሉ የሚል #ተስፋ እንደሌላቸው ገልፀዋል።

Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሀገራችን #ተስፋ አንቆርጥም.../TIKVAH-ETHIOPIA/ ማለት ተስፋ ኢትዮጵያ ማለት ነው!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፍቅር #ጉዟችንን በተመለከተ...

በTIKVAH-ETH በኩል #የተሰባሰቡት ወጣቶች ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የተውጣጡ ትክክለኛውን የኢትዮጵያ ቀለም የያዙ ናቸው። ሁሉም ወጣቶች እናት ሀገራቸውን የሚወዱ እና በሀገሪቱ ላይ አዲስ ታሪክ ለመፃፍ ከሳምንት እስከ ሳምንት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ፤ የትምህርት እና የግል ጊዜያቸውን ትተው ለሰላምና ፍቅር የሚጓዙ ናቸው። ለዚህም ሰላም ወዳዱ የኢትዮጵያ ህዝብ #ሊያመሰግናቸው ይገባል።

ዩኒቨርስቲዎችን በተመለከተ፦

#StopHateSpeech በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄድ ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ ከተማሪዎች ጋር የሚደረግ #ውይይት እና #ንግግር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነው። ምክንያቱም ወጣቶች ከጥላቻ እና ከስሜታዊነት ርቀው ሀገር መገንባትና ለህዝብም #ተስፋ የሚሰጡ ዜጎች እንደሆኑ ማስመስከር ስለምንፈልግ ነው።

ይህ ጉዞ እና እንቅስቃሴ ከየትኛውም አይነት የፖለቲካ አመለካከት ነፃ የሆነ፤ ከየትኛውም ድርጅትም ሆነ ቡድን ገለልተኛ የሆነ በወጣቶች የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው። ወጣቶቹም ትክክለኛ የሀገሪቱን ቅርፅ የያዙ በፍቅር እና በንግግር የሚያምኑ ሀገሪቷን ከጥላቻ አላቀው ትልቅ ሀገር የመገንባት ህልም ያላቸው ናቸው።

√ወጣቶቹ የሰላምን አርማ ይዘው በየሄዱበት የሚሰብኩት ስለፍቅር እና መተባበር እና መተጋገዝ ብቻ ነው። በሚዘጋጁት መድረኮችም የጥላቻ መዘዞችን ማስገንዘብ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸውን እንዲያሻሽሉ ማስገንዘብ ነው።

√ውይይቶች በጠቅላላ የሚደረጉት #በወጣት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች #መካከል ብቻ ነው። ሌላው ተናጋሪዎች ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው አካላት ብቻ ናቸው።

በቀጣይ ምዕራፍ 2፦ ከዩኒቨርሲቲ #አመራሮች እና #ሰራተኞች ጋር ተመሳሳይ መድረክ ይኖረናል።

ኢትዮጵያን በፍቅር እንገንባ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የአንድ እናት ልጆች ነን መስመር አይለየን...
የአንድ ቤት ልጆች ነን መስመር አይለየን...

#መቐለ_ዩኒቨርሲቲ የሰላም አምባሳደር!
#ፍቅር #ተስፋ #አንድነት #መቐለ_ዩኒቨርሲቲ
#ለጥያቄው_ምላሽ፦ TIKVAH-ETH የተመሰረተው እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በሃምሌ 19/2009 ዓ/ም ነው። TIKVAH በተመሰረተበት ወቅት የቤተሰቡ አባላት 20 አይደርሱም ነበር። የነበሩትም #ንቁ ተሳታፊ አልነበሩም። ዛሬ በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል የሚገኘው የቤተሰባችን አባል ከ320 ሺ በላይ ነው። በተመሰረተበት ወቅት ቀለል ያሉ የመዝናኛ ነክ ጉዳዮችንና ፎቶዎችን ያቀርብ ነበር። ለጥቂት ጊዜ ትውውቅ ከተደረገ በኃላ በወቅቱ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በነበረው ችግር ሳቢያ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ተማሪ ድምፅ ሆኖ አገልግሏል።

TIKVAH ማለት #ተስፋ ማለት ነው!

√እኛ ማንም ሰው በሰውነቱ ብቻ የሚከበርበት፤ ሰውነቱ ሲከበር ብሄሩ፣ ቋንቋው፣ ባህሉ፣ አመለካከቱ፣ እምነቱ የሚከበርበት ሀገር እንደምትኖረን ተስፋ እናደርጋለን።

√እኛ አስተማማኝ ደህንንነት እና ሰላም ያለባት ሀገር እንደምትኖረን ተስፋ እናደርጋለን።

√እኛ ማንም ሰው በአመለካከቱ የማይገፋበት ለሁሉም ዜጎች እኩል የሆነች ሀገር እንደምትኖረን ተስፋ እናደርጋለን!

√እኛ አይደለም ለኢትዮጵያዊ በምድር ላይ ላለሰው ሁሉ የምትሆን ሀገር እንደምትኖረን ተስፋ እናደርጋለን።

√እኛ ዜጎቿ የማይበደሉባት ሀገር እንደምትኖረን ተስፋ እናደርጋለን።

#ተስፋችን_ደግሞ_በፍጡር_ሳይሆን_በፈጣሪ_ብቻ_ነው!

ይህ አቋማችን የዛሬ ሳይሆን የነበረ፤ ያለና ወደፊትም የሚኖር ነው!! #ETHIOPIA

🏷ይሄ ቤተሰብ "የኢትዮጵያ ተስፋ" ነው ብለን እናምናለን!! በመነጋገር የሚያምን ከጥላቻ የራቀ፤ ስድብ የሚፀየፍ አንድ ጠንካራ የሆነችን ሀገር ለመገንባት ዘውትር የሚተጋ የሰለጠኑ ኢትዮጵያዊያን ስብስብ ነው።

ፈጣሪ ሀገራችንን ይጠብቅልን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዕለቱ መልዕክት፦

ከጭፍን ጥላቻ መላቀቅ ይቻላል!

አብዛኞቹ ሰዎች ጭፍን ጥላቻን በመሠረተ ሐሳብ ደረጃ የሚያወግዙ ቢሆኑም ከጭፍን ጥላቻ መዳፍ የሚላቀቁ ግን ጥቂቶች ናቸው። እንዲያውም ሥር የሰደደ ጭፍን ጥላቻ ያላቸው ብዙ ሰዎች ጥላቻ እንደሌላቸው ሊናገሩ ይችላሉ። ሌሎች ደግሞ ሰዎች ጭፍን ጥላቻቸውን ይፋ እስካላወጡ ድረስ ምንም ጉዳት የለውም ይላሉ።

ይሁን እንጂ ጭፍን ጥላቻ ሰዎችን የሚጎዳና የሚከፋፍል መጥፎ ነገር ነው። ጭፍን ጥላቻ የድንቁርና ልጅ ነው ቢባል የልጅ ልጁ ደግሞ ጠላትነት ነው። ቻርልስ ካለብ ኮልተን የተባሉት ደራሲ (1780-1832) “አንዳንድ ሰዎችን ስለማናውቃቸው #እንጠላቸዋለን። ስለምንጠላቸውም #ልናውቃቸው አንችልም” ብለዋል። ጭፍን ጥላቻን ሰዎች መማር እንደሚችሉ ሁሉ ማስወገድም ይችላሉ።

Via #JW

#ፍቅር #ሰላም #አንድነት #ተስፋ #ኢትዮጵያ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
342,200 የቤተሰብ አባላት #HOPE #ተስፋ #TIKVAH #ETHIOPIA

Voice of Hope🇪🇹TIKVAH-ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ማህበረሰብ ተስፋ ሲቆርጥ ምን ይፈጠራል?

"...እንደ ህዝብ ደግሞ ህዝብ ተስፋ ከቆረጠ እሴቶቹን ይጥላል፤ ነገ ለውጥ የለም፤ ምንም ተስፋ የለንም ብሎ ካሰበ፤ ይጋደላል፣ ይሰዳደባል፣ ተስፋ የቆረጠ ሰራዊት ልታይ ትችላለህ ፌስቡክም ላይ ሚዲያም ላይ፤ ህዝብ ተስፋ ከቆረጠ መከባበሩ ይጠፋል፤ ትህትናው ይጠፋል፤ ፍቅሩ ይጠፋል፤ ሚታየው ነገር የለም። ሰውን ስነ ስርዓት ከሚያሲዙትና እሴቶቹን ጠብቆ እንዲኖር ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱ ነገ መልካም ይሆናል የሚል #ተስፋ ነው" ዶክተር #ወዳጄነህ_ማሀረነ

#HOPE #TIKVAH/#ተስፋ/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA💪ክብር ይገባችኃል!

ስንተባባር በአንድነት ስንቆም ምንም ነገር አያቅተንም!! 6710 የልብ ህሙማን ህፃናትን አለንላችሁ እንበላቸው!!

#TIKVAH_ETHIOPIA_FAMILY

Screenshot ወደዚህ ግሩፕ👇

https://publielectoral.lat/joinchat/FCD9AhWFZJX_rX95-4rWNQ

#አንድነት #ተስፋ #መተሳሰብ #ፍቅር #ቲክቫህ
❤️ከ3000 በላይ አባል❤️

6710 ላይ የህፃናት የልብ ህክምናን ለማገዝ በተከፈተው ግሩፕ ላይ እስካሁን ከ3 ሺህ የሚበልጡ የቤተሰባችን አባላት ተቀላቅለውናል!! በሺዎች የሚቆጠር ገንዘበ እንደ አቅማችን አስተዋፆ እያደረግን እንገኛለን!! ሀገር ወዳድነት መገለጫው ይህ ነው!!

Screenshot ወደዚህ ግሩፕ👇

https://publielectoral.lat/joinchat/FCD9AhWFZJX_rX95-4rWNQ

እኔ ካለኝ ላይ አካፍያለሁ?? እናተስ??

ለአንድ መልዕክት የሚቆርጠው 1 ብር ብቻ ነው!!


በትንሹ 3 መልዕክት ይላኩ!

#አንድነት #ተስፋ #መተሳሰብ #ፍቅር #ቲክቫህ
TIKVAH-ETH 2011 ዓ/ም- የፎቶ ማጠቃለያ⬆️

•ሀረማያ
•ወሎ
•ደብረብርሃን
•ወልዲያ
•መቐለ
•ዋቸሞ
•መቐለ
•ወላይታሶዶ
•ሀዋሳ
•አርባምንጭ
•ጅማ

#ተስፋ #ፍቅር #ሰላም #TIKVAH

#STOP_HATE_SPEECH

በጎዞው ላይ ያልተሳተፋችሁ ደግሞ በያላችሁበት ሆናችሁ ዓላማውን በሀሳብ ስትደግፉ ነበር። ተመስግናችኃል!!

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

🔖በበጎ አድራጎቱ ስራም በአቅማችሁ ለቻላችሁት ሁሉ ፤ድጋፍ ለሚፈልጉ ወገኖችም ድጋፍ ያደረጋችሁበት አመት ነበር።

🔖የየአካባቢያችሁን እውነተኛ ክስተቶችም በማካፈል ፍፁም የተሳካ አመት ነበር። በተለይ ሀሰተኛ መረጃዎችን በመከላከል ትልቅ ስራ ሰርታችኃል።

🔖መልካምነት ጎልቶ እንዲታይ በየአካባቢው መልካም ስራዎችን ሰርታችሁ ያለፋችሁበት ዓመት ነበር።

🔖የቤተሰቡ አባላት ለሀገሪቱ ችግር ከመሆን ይልቅ የመፍትሄ አካል ለመሆን በሁሉም አቅጣጫ የሰራችሁበት ነበር።
.
.
.
ብዙ ብዙ ሌሎች ስራዎች!

በአጠቃላይ ጥሩ የሚባል አመት ነበር። ሁላችሁም የዚህ ቤተሰብ አባላት እንኳን አደረሳችሁ። አዲሱ አመት ደግሞ ትልልቅ ስራዎችን የምንሰራበት ነው። ተዘጋጁ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በደንብ ተመልከቱ⬆️

እኛ እንዲህ ነን፤ ተያይዞ፣ ተቻችሎ፣ ተዋዶ መኖር ካልቻልን ተያይዞ መጥፋት ነው የሚሆነው፤ አንዱን ጠጠር ብታነሱት ሁሉም ይፈርሳል፤ ለሁሉም መኖር የአንዱ መኖር ወሳኝ ነው።

#እንዋደድ #እንከባበር #እንፋቀር #ሰላም #ፍቅር #ተስፋ

ሀሳቡ ከማህበራዊ ሚዲያ ተወሰደ!


🚪መስከረም 2 ቀን 2012 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እንኳን ደስ አላችሁ!

#TIKVAH_ETH በሁለት ዓመት ከአንድ ወር ከሃያ አንድ ቀን ከመላው ሀገሪቱ እንዲሁም ከተለያዩ የውጭ ሀገራት ከ400,000 በላይ የቤተሰብ አባላት ማፍራት ችሏል።
_______________________________________

ሰው በሰውነቱ ብቻ የሚከበርባት ሀገር እንድትኖረን እንመኛለን፤ መመኘት ብቻ አይደለም ለዚህ እውን መሆን ያለእረፍት እንሰራለን፡፡

TIKVAH-ETHIOPIA❤️ተስፋ ኢትዮጵያ

አንዱ የአንዱን ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት ማክበር ከቻለ፤ ከጥላቻ እና ከቂም በቀል ነጻ የሆነ አስተሳሰብ መፍጠር ከተቻለ፤ ልዩነቶችን በውይይት መፍታት ከተቻለ፤ ለመልካም ነገር ለመተባበር ደግሞ ልዩነታችን መሰናክል ካልሆነ #ተስፋ_አለን የኛ ኢትዮጲያ ለሁላችንም የምትመች ሀገር ትሆናለች፡፡ TIKVAH-ETH ውስጥ የተሰባሰብነው እርስ በእርሳችን በመከባበር እና በመዋደድ የተሻለች ሀገር ገንብተን ለመጭው ትውልድ ለማስረከብ ነው።

ሁላችሁንም እናከብራችኃለን!

ረጅም ርቀት አብረን እንጓዛለን!
ሰላም፤ ፍቅር፤ ተስፋ!
TIKVAH-ETH
እንኳን ደስ አለን፤ እንኳን ደስ አላችሁ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለኮሮና ቫይረስ በፍጥነት ክትባት ይገኝለት ይሆን ?

በአሜሪካ የጤና ተቋም CDC በኃላፊነት የሚሰሩት ዶክተር ኤርሚያስ በላይ #ETHIOTUBE ላይ ቀርበው ይህን ተናግረዋል ፦

ክትባትን ለመፍጠር ብዙ ሰዎች በተለያዩ ሀገሮች ብዙ ስራ እየሰሩ ነው ያለው። ይሄ ክትባት ሊገኝ እንደሚችል ብዙ ተስፋ አለኝ። በቫይረስ ጥቃት ለሚመጡ በሽታዎች ክትባት ማግኘት በአብዛኛው ጊዜ ብዙ አይከብድም። የሚከብድባቸው ሆኔታዎችም ግን አሉ።

የኢንፉሌንዛ ቫይረስን ብንመለከት በተመሳሳይ ሁኔታ ነው የሚተላለፈው፤ ለኢንፉሌንዛ ቫይረስ ክትባት በየአመቱ ይሰራል። ለዚህኛውም ቫይረስ ክትባት እንደሚገኝለት #ተስፋ አደርጋለሁ። ግን ይሄን ክትባት ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ከ8-12 #ወራት ሊወስድ ይችላል።

ቫይረሱ ቢጠቃ በክትባት ሊሸነፍ የሚችልበትን ቦታ ማግኘት ያስፈልጋል፤ ይሄ በላብራቶሪ ጥናት ከተደረገ በኃላ ለዛ ክትባት ተዘጋጅቶ በእንስሶች ውስጥ ሙከራ ማድረግ ይፈልጋል፣ ከዛም በሰዎች ላይ ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል፣ ከዛም ቁጥሩ በዛ ያለ ህዝብ ላይ ይሄ ክትባት ከበሽታው መከላከል መቻሉ ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ይሄ ሁሉ ሂደት ረጅም ጊዜ ይወስዳል።

አንዴ በጥናት ከተረጋገጠ በኃላ እንኳን ለብዙ ሰዎች እንዲሆን አድርጎ በስፋት ማምረት እንኳን ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ቢያንስ ቢያንስ ሁለትና ሶስት ወራት ሊወስድ ይችላል። ስለዚህ ክትባት ማግኘቱን ቀላል ነገር ተደርጎ ቢታሰብም ለግለሰቦች እንዲባዛ አድርጎ ማቅረቡ በጣም ጊዜ ይወስዳል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#REPOST

ለኮሮና ቫይረስ በፍጥነት ክትባት ይገኝለት ይሆን ?

በአሜሪካ የጤና ተቋም CDC በኃላፊነት የሚሰሩት ዶክተር ኤርሚያስ በላይ #ETHIOTUBE ላይ ቀርበው ይህን ተናግረዋል ፦

ክትባትን ለመፍጠር ብዙ ሰዎች በተለያዩ ሀገሮች ብዙ ስራ እየሰሩ ነው ያለው። ይሄ ክትባት ሊገኝ እንደሚችል ብዙ ተስፋ አለኝ። በቫይረስ ጥቃት ለሚመጡ በሽታዎች ክትባት ማግኘት በአብዛኛው ጊዜ ብዙ አይከብድም። የሚከብድባቸው ሆኔታዎችም ግን አሉ።

የኢንፉሌንዛ ቫይረስን ብንመለከት በተመሳሳይ ሁኔታ ነው የሚተላለፈው፤ ለኢንፉሌንዛ ቫይረስ ክትባት በየአመቱ ይሰራል። ለዚህኛውም ቫይረስ ክትባት እንደሚገኝለት #ተስፋ አደርጋለሁ። ግን ይሄን ክትባት ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ከ8-12 #ወራት ሊወስድ ይችላል።

ቫይረሱ ቢጠቃ በክትባት ሊሸነፍ የሚችልበትን ቦታ ማግኘት ያስፈልጋል፤ ይሄ በላብራቶሪ ጥናት ከተደረገ በኃላ ለዛ ክትባት ተዘጋጅቶ በእንስሶች ውስጥ ሙከራ ማድረግ ይፈልጋል፣ ከዛም በሰዎች ላይ ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል፣ ከዛም ቁጥሩ በዛ ያለ ህዝብ ላይ ይሄ ክትባት ከበሽታው መከላከል መቻሉ ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ይሄ ሁሉ ሂደት ረጅም ጊዜ ይወስዳል።

አንዴ በጥናት ከተረጋገጠ በኃላ እንኳን ለብዙ ሰዎች እንዲሆን አድርጎ በስፋት ማምረት እንኳን ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ቢያንስ ቢያንስ ሁለትና ሶስት ወራት ሊወስድ ይችላል። ስለዚህ ክትባት ማግኘቱን ቀላል ነገር ተደርጎ ቢታሰብም ለግለሰቦች እንዲባዛ አድርጎ ማቅረቡ በጣም ጊዜ ይወስዳል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
እንኳን አደረሳችሁ!

TIKVAH-ETHIOPIA እንኳን ለሲዳማ የፊቼ ጨምበላላ በዓል በሰላም አደረሰን ፤ አደረሳችሁ ለማለት ይወዳል። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ፣ የመተሳሰብ ይሆን ዘንድ እንመኛለን!

ይህን ዓለምን ያስጨነቀ ወረርሽኝን አሸንፈን የዓለም ቅርስ የሆነውን 'ፊቼ ጨምባላላ በዓል' በአደባባይ ተሰባስበን የምናከብርበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን #ተስፋ እናደርጋለን!!

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia