TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሱዳን

የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በወታደራዊ ሽግግር ምክር ቤት እና በነጻነት እና ለውጥ ኃይሎች መካከል ሲደረግ የነበረው ድርድር የሽግግር ሕገመንግስት እና የፓለቲካ ስምምነት በመፈራረም መጠናቀቁን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያ እና አፍሪካ ሕብረት ሁለቱን ወገኖች በማደራደር ላበረከቱት አስተዋጽኦና ለተጫወቱት ቁልፍ ሚና የምስጋና ፕሮግራም በማዘጋጀት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና ዳይሬክተር ጄኔራሎች በተገኙበት ሽልማት አበርክቷል። ሽልማቱ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሱዳን ልዩ ልዑክ አምባሳደር መሃሙድ ድሪር ፣ በሱዳን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሽፈራው ጃርሶ እና የአፍሪካ ሕብረት ልዩ ልዑክ መሃመድ ሃሳን ላባት የተበረከተ ሲሆን፣ የወታደራዊ ሽግግር ምክር ቤት የፓለቲካ ጉዳዮች ተጠሪ ጄኔራል ሸምሰዲን አል ካባሺ በተገኙበት የሱዳን ተጠባባቂ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ኦማር ዳሃብ ሽልማቱን አበርክተውላቸዋል።

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ካርቱም

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶክተር) የሚመሩት ልዑክ ካርቱም ገብቷል፡፡ በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በማኅበራዊ ገጹ እንዳስነበበው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት ልዑክ ዛሬ ወደ ሱዳን ያቀናው በሱዳን የሽግግር መንግሥትን በይፋ ለመመሥረት በሚከናወነው ሥነ-ሥርዓት ለመታደም ነው፡፡

የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሐሰን ኦማር አልበሽር መንግሥት የሦስት አስርት ዓመታት ቆይታው በሕዝባዊ ተቃውሞ ተናግቶ ወታደራዊ የሽግግር ምክር ቤት ሲመሠረት ሱዳን ወደ ቀውስ እንደምትገባ ብዙዎች ገምተው ነበር፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያና የአፍሪካ ሕብረት ባደረጉት ተከታታይ ጥረት ወታደራዊ የሽግግር ምክር ቤቱና ሲቪል የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉበት የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

በዚህም #ሱዳን ወደ #መረጋጋት እንደምትገባ ተስፋ ተጥሎበታል፡፡ የሽግግር መንግሥቱ ምሥረታ ላይ ለመገኘትም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶክተር) የሚመሩት ልዑክ ዛሬ ጠዋት ካርቱም ገብቷል፤ ደማቅ አቀባበልም ተደርጎለታል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሱዳን

የሱዳን ተቃዋሚ ሃይሎች አምስት ሲቪል የሉአላዊ ምክር ቤት አባላትን መምረጣቸው ተገለፀ። በሱዳን ተቃዋሚዎች ጥምረት የመረጧቸው የኡአላዊ ምክር ቤቱ አባላቱ በዛሬው እለት ቃለ መሃላ ይፈጽማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ተነግሯል። ከወታዳራዊ ሽግግር ምክር ቤት፤ መሪውን አብደል ፈታህ አልቡራን፣ ምክትላቸውን ሞሃመድ ሃማዳን ዳጋሎ እና የወታዳራዊ ሽግግር ምክር ቤት ቃል አቀባይ ሌተናል ጀኔራል ያሰር አል አታን ይጨምራል ነው የተባለው፡፡

Via #CGTN/#FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሱዳን

አብደላ ሃምዶክ #የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን በትናንትናው እለት ተሹመዋል። ሌተናል ጄነራል አብደል ፈታህ አብደልራህማን ቡርሃን አዲስ የተቋቋመው የሱዳን ሉአላዊ ምክር ቤት መሪ በመሆን መሾማቸውን ተከትሎ ነው አብደላ ሃምዶክ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን የተሾሙት።

እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2011 ጀምሮ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኢኮኖሚስት በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት አብደላ ሀምዶክ ከሚሰሩበት አዲስ አበባ ወደ ካርቱም በማቅናት በትናንትናው እለት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።

ምንጭ:- ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሱዳን_ያስተናገደቻቸው_ሰልፎች

በዳቦ ዋጋ መናር ምክንያት ፕሬዝዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር ከስልጣን እንዲነሱ ያደረገው የሱዳን አብዮት 2ተኛ ዓመቱ በተለያዩ ስሜቶች እየታሰበ ነው፡፡

ከዛሬ 2 ዓመት ወዲህ ፕሬዝዳንት አልበሽርን በመጣል አዲስ የሽግግር መንግስት የተቋቋመ ሲሆን ወታደሩንና ሲቪሉን የሚወክሉ መሪዎች ሀገሪቱን እያስተዳደሩ ነው፡፡

ዛሬ ካርቱምን ጨምሮ በሱዳን የተለያዩ ከተሞች በተካሔዱ ሰልፎች በአንድ ወገን አብዮቱን የሚደግፉ አካላት በሌላ በኩል ደግሞ ተቃዋሚዎችም ድምጻቸውን አሰምተዋል፡፡

አብዮቱን በመደገፍ ሰልፍ የወጡ ሰልፈኞች የአብዮቱ ዓላማ ግን መስመሩን መሳቱን በመጥቀስ ቁጣቸውን አሰምተዋል፡፡

የኑሮ ውድነት እና የኢኮኖሚ ቀውስን በመቃወም ከሁለት ዓመት በፊት አብዮት ቢፈነዳም እነዚህን ችግሮች ከመቅረፍ አንጻር አብዮቱ ምንም አልፈየደም በሚል የተቃውሞ ድምጾች ተስተጋብተዋል፡፡

በሱዳን ያለው የኑሮ ውድነት ፣ ከፍተኛ የዳቦ እጥረት እና የሀገሪሩ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እንደቀጠሉ ናቸው፡፡

ከአብዮቱ በተቃራኒ በመቆም የፕሬዝዳንት አልበሽርን መንግሥት በመደገፍ አደባባይ የወጡም አሉ፡፡ እነዚህ አካላት የአልበሽር ስርዓት እንዲመለስ የሚፈልጉ ናቸው፡፡

ያም ሆነ ይህ ታዲያ የሀገሪቱ ሉኣላዊየሽግግር መንግስት ሊቀ መንበር በአብዮቱ 2ኛ ዓመት ላይ ትኩረት ያደረጉ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል፡፡

የሀገሪቱ የጦር ኃይሎች ዋና አዛዥ እና የሉኣላዊ ሽግግር ምክር ቤት ሊቀ መንበር አብዱልፈታህ አል-ቡርሃን ፣ የአልበሽር አገዛዝ የተወገደበትን ሁለተኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ባስተላለፉት መልዕክት ሰራዊቱ በአብዮቱ የተገኙ ውጤቶችን እንደሚያስጠብቅ ተናግረዋል።

አል ቡርሃን በትዊተር ሱዳናውያንን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ አል ዓይን (AlAIN)

@titikvahethiopia
#Egypt #Ethiopia #Sudan

በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ መካከል የሚደረገው ድርድር በሚቀጥለው #እሁድ ታህሳስ 25 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚቀጥልም አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገልፀዋል።

አምባሳደሩ ይህን የገለፁት በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ላይ ነው።

ከታላቁ ህዳሴው ግድብ ድርድር ራሷን አግልላ የነበረችው #ሱዳን ወደ ድርድሩ እንደምትመለስ በቅርቡ ይፋ ማድረጓ ይታወቃል፡፡

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት መግለጫ ላይ ያነሷቸውን ሌሎች ጉዳዮች በዚህ ማግኘት ትችላላችሁ : telegra.ph/ALAIN-12-29 (መረጃውን አዘጋጅቶ ያሰራጨው አል ዓይን ኒውስ ነው)

@TIKVAHETHIOPIA @TIKVAHETHIOPIABOT
#GERD🇪🇹

"...የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምትገነባው ሙሌት አካሂዳ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ነው" - ፕ/ር ያዕቆብ አርሳኖ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እና የዓባይ ውሃ ጉዳይ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ፥ ኢትዮጵያ ታላቁን የህዳሴ ግድብ የምትገነባው ሙሌት አካሂዳ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት በመሆኑ የሙሌት ጉዳይ ብዙ የሚያነጋግር እንዳልሆነ ገለፁ።

ፕሮፌሰር ያዕቆብ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት ቃል፤ ሁለተኛው ዙር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ጉዳይ ኢትዮጵያውያን እና የዓለምን ፖለቲከኞች ቀልብ በእጅጉ የሳበ ክስተት ነው ብለዋል።

በተለይ ግብጽና ወደግብጽ ተለጥፋ ያልተገባ ጭቅጭቅ ውስጥ የምትገኘው #ሱዳን በተነዙ የሐሰት ፕሮፓጋንዳዎችና እና አሳሳች መግለጫዎች የተነሳ የህዳሴው ግድብ ሁለተኛው እርከን ሙሌት በተጋነነ ወሬ ውስጥ ነበር ሲሉ ገልፀዋል።

መታወቅ የነበረበትም ሆነ አሁንም መታወቅ ያለበት ጉዳይ #ኢትዮጵያ ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምትገነባው ሙሌት አካሂዳ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት መሆኑ ነው ሲሉ አስገንዝበዌ።

ይህ እንደሚሆን ደግሞ በኢትዮጵያ መንግስት ጥናት እና ዲዛይን ፣ በድርድሩ ሂደት ፣ በግድቡ ግንባታ ስራና በየጊዜው በሚወጡ በኢትዮጵያ መንግስት መግለጫዎች መገለጹን አስታውሰዋል።

#ኢፕድ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፌልትማን ዳግም ኢትዮጵያ ሊመጡ ነው። የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጄፍሪ ፌልትማን ነገ ለሁለት ቀናት ጉብኝት ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት አሳውቋል። የጉዞአቸው ዓለማ ሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄድ ያለው ግጭት አሳሳቢነቱ እየጨመረ በመምጣቱ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል። ፌልትማን ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ ሲመጡ ይህ ለሶስተኛ ጊዜ ነው የሚሆነው ከዚህ ቀደም…
ፎቶ ፦ ፌልትማን ኢትዮጵያ ገብተዋል።

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት ጄፍሪ ፌልትማን ዛሬ ኢትዮጵያ (አዲስ አበባ) ገብተዋል፤ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ በኃላም ከሙሳ ፋኪ ማሃመት ጋር ተገናኝተው መክረዋል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ፌልትማንን በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው ጄፍሪ ፌልትማንን በቢሯቸው ተቀብለው በ #ኢትዮጵያ እና #ሱዳን ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን አሳውቀዋል።

Credit : Moussa Faki Mahamat (Twitter)

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #SUDAN

ዛሬ #ኢትዮጵያ ሀገራችን ከጎረቤት ሀገር #ሱዳን ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታዋን እያደረገች ትገኛለች።

ይህ ጨዋታ እየተካሄደ የሚገኘው የሁለቱም ሀገራት ብሄራዊ ቡድኖች በአፍሪካ ዋንጫ ለመካፈል ባቀኑባት ካሜሮን ሀገር ነው።

የሀገራችን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከቀናት በፊት በትልቁ የአፍሪካ የእግር ኳስ ውድድር የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ ከውድድሩ ቀደም ብሎ ወደ ካሜሮን አቅንቷል።

ቡድናችን ካሜሮን ከደረሰ በኃላ በየዕለት ልምምድ እየሰራ ውድድሩ እስኪጀመር እየተጠባበቀ ይገኛል። ዛሬ አቋሙን የሚፈትሽበት ጨዋታ እያደረገ ነው።

ሀገራችን በተወከለችበት ትልቁ የአፍሪካ የእግር ኳስ ውድድር መድረክ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትም ወደ ስፍራው ከብሄራዊ ቡድኑ ጋር ያቀኑ ሲሆን በስፖርት ገፃችን ላይ መረጃዎችን ያካፍላሉ።

የቲክቫህ ስፖርት ገፅ ፦ https://publielectoral.lat/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport